Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ከወርቅ ወጪ ንግድ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ሥድስት ወራት ከወርቅ ወጪ ንግድ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

#ኢትዮጵያ ባላት መልከዓ ምድር ምቹ የአየር ንብረት ብዝሃ-ምርቶችን አምርታ ለዓለም የማቅረብ ዕምቅ አቅም አላት፡፡

ከማዕድን ባለፉት ስድስት ወራት #ከወርቅ ብቻ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ አግኝተናል። አቅማችንን አጎልብተን ወደ ገቢራዊ ውጤት መቀየርና ማስተዋወቅ ያስፈልጋል ብለዋል።

የቡና፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች፣ ሰብሎች፣ ቅመማቅመም፣ አትክልትና ፍርፍሬ፣ ማዕድንና ሌሎች ምርቶቻችንን በጥራት አምርተን በውጪ ንግድ የዓለም ገበያ ያለን ድርሻ እያሻሻልን ከሄድን ከዘርፉ የምናገኘው ገቢ በብዙ እጥፍ እንደሚጨምር ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያና የጃፓን የንግድና ኢንቨስትመንት ሲምፖዚየም ተሳታፊዎች በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ አውደርዕይ ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

ጥር 14 ቀን 2017 ዓም
👍3
በአገልግሎትና አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን በመሰረታዊነት ለመፍታት የተጀመሩ የሪፎርም ትግበራና የዝግጅት ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም አመራር ዐቢይ ኮሚቴ ሦስተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂደናል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው እንዳስታወቁት፣ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንና በመጀመሪያ ዙር የተመረጡ ተቋማት ያከናወኗቸውን የሪፎርም ሥራዎች ተገምግመዋል።

የሪፎርም አስተዳደራዊ ሥራዎች፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሥርዓትን መዘርጋት፣ #ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ በመገንባት አገልግሎቶችንና ውሳኔዎችን ማቀላጠፍ ላይ ጥሩ ጅምሮች አሉ ብለዋል።

በሪፎርሙ የታቀፉ ተቋማት ያላቸውን ልምዶች የሚቀያየሩበት እና በጋራ የሚሰሩበትን አውድ መፍጠር ተችሏል፡፡

ተቋማት ያከናወኗቸውን ተግባራት በዝርዝር በመቃኘት ጥንካሬዎችንን ውስንነቶችን የለየን ሲሆን በቀጣይ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች ላይም አቅጣጫ አስቀምጠናልም ብለዋል።

ጥር 14 ቀን 2017 ዓም
👍4
ዛሬ በባሕርዳር ከተማ በጣና ሀይቅ ላይ የታንኳ ቀዘፋ ውድድር ይካሄዳል
***
(ኢ ፕ ድ)

ዛሬ በባሕርዳር ከተማ ከቀኑ 7 ሠዓት ጀምሮ በጣና ሀይቅ ላይ የታንኳ ቀዘፋ ውድድር፣ የጀልባ ትርዒትና ሽርሽር ይካሄዳል።

በጥር ወር በአማራ ክልል የቱሪስት መስኅብ የሆኑ ዝግጅቶች በተለያዩ አካባቢዎች ይደረጋሉ፤ የዛሬው የታንኳ ቀዘፋ ውድድር፣ የጀልባ ትርዒትና ሽርሽርም አንዱ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

#ባህርዳር #ቱሪዝም #ቱሪስት

ጥር 15 ቀን 2017 ዓም
👍94
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ
****
(ኢ ፕ ድ)

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 16ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ሹመቶችን አጽድቋል።

1. ወ/ሮ ስመኝ ውቤ የኢትዮጵያ ህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕምባ ጠባቂ

2. ዶ/ር የኔነህ ስመኝ የኢትዮጵያ ህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ምክትል ዋና ዕምባ ጠባቂ

3. አቶ አባይነህ አዴቶ የኢትዮጵያ ህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም የዘርፍ ዕምባ ጠባቂ ሆነው ተሹመዋል።

ምክር ቤቱ #ኢትዮጵያ ህዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም ዕጩ አቅራቢ ኮሚቴ አቋቁሞ ሲሰራ መቆየቱን አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በወቅቱ ተናግረዋል።

በዳግማዊት አበበ

ጥር 15 ቀን 2017 ዓም
👍21
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️

👉 ለአምራች ኢንዱስትሪዎች 369 ሚሊየን 110 ሺህ ዶላር የውጭ ምንዛሬ ቀርቧል፣

👉 ከሁለት ቢሊየን በላይ የአሜሪካን ዶላር የገቢ ምርት መተካት ተችሏል፣

👉 አማካኝ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም አጠቃቀም 61 ነጥብ 2 በመቶ ደርሷል፣

👉 በወጪ ንግድ 95 ሺህ 167 ቶን ምርት ወደ ውጭ ተልኳል፣

👉 ከዘርፉ 149 ሚሊዮን 334 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፣

👉 ለቆዳና ቆዳ ውጤቶች አምራች ኢንዱስትሪዎች 10 ሚሊዮን 400 ሺህ ቶን ማቅረብ ተችሏል፣

👉በጨርቃጨርቅ፣ በምግብና መጠጥ፣ በኬሚካልና ኮንስትራክሽን ዘርፍ 9 ሚሊየን 527 ሺህ ቶን ግብዓት ቀርቧል፣

👉 ለአምራች ኢንዱስትሪዎች 61ሺህ የሰለጠነ የሰው ሃይል ማቅረብ ተችሏል

👉 ለከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች 24 ቢሊየን 870 ሚሊየን ብር ብር ቀርቧል፣

👉ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የሥራ ማስኬጃ 5,365,455,942 ብር ፣

👉 ለአነስተኛናመካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ለሊዝ ፋይናንስ 2,490,604,769 ብር ማቅረብ ተችሏል፣

👉 350 ሺህ 600 ኪሎዋት ሀይል ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ማቅረብ ተችሏል፣

👉 ለቆዳና ለሌሎች ኢንዱስትሪዎች 269 ሺህ ኩንታል ጨው ማቅረብ ቀርቧል፣

👉 በኢንዱስትሪዎች መካከል 110,058 ቶን የግብዓት ትስስር ተፈጥሯል፣

👉 የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተሻለ የዉጭ ምንዛሬ ክምችትና አቅርቦት እንዲኖር ከፍተኛ እገዛ አድርጓል፣

#ኢትዮጵያ_ታምርት #አምራች_ዘርፍ #ኢንዱስትሪ
👍121🖕1
ኢትዮጵያ ከናሚቢያ እና ሲሸልስ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለፀ
*****
(ኢ ፕ ድ)

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከናሚቢያና ሲሼልስ አምባሳደሮች ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮቾ ላይ መክረዋል።

በኢትዮጵያ የናሚቢያ አምባሳደር ምባፔዋ ሙቫንጓ ጋር ባደረጉት ውይይት በንግድ፣ ኢንቨስትመንትና #አቪዬሽን የትብብር መስኮች ማጠናከር እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በኢትዮጵያ ከሲሼልስ አምባሳደር ኮንራድ ቪንሴንት ሜድሪች ጋር በነበራቸው ውይይት #ኢትዮጵያ ከሲሸልስ ሁለትዮሽ ግንኙነት አህጉር አቀፍ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ለመስራት እንደምትሻ መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ጥር 15 ቀን 2017 ዓም
👍1
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በካሳንቺስ አያት የመኖሪያ መንደር የ13 ሺህ 752 መኖሪያ ቤቶች ግንባታን አስጀመሩ
***
(ኢ ፕ ድ)

በካሳንቺስ በ18 ወራት ተገንብተው የሚጠናቀቁ 13 ሺህ 752 የመኖሪያ ቤቶች በመንግስትና በግል አጋርነት ሊገነቡ ነው።

መኖሪያ ቤቶቹ ከአያት አክሲዮን ማህበር ጋር በትብብር የሚገነባ "የካሳንቺስ አያት መኖሪያ መንደር" መሆኑ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስትና በግል አጋርነት የሚስራ መኖሪያ ቤቶች የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሄዷል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፤ መኖሪያ ቤት አንገብጋቢ ጉዳይ ነው። ይህንን ለመመለስ የህግ ማሻሻያ ተደርጓል።

በዚህም ቤቶችን ለመገንባት በአራት አማራጮች በመንግስት፣ በመንግስትና በግል፣ በማህበርና በሪል ስቴት በርካታ ቤቶች እንዲገነቡ ማድረግ ነው ብለዋል።

በእነዚህ አማራጮች እስከ አሁን 270 ሺህ ቤቾች መገንባታቸውን የጠቆሙት ከንቲባ አዳነች፤ የቤት አቅርቦት በማስፋት አብዛኛውን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።

የአያት አክሲዮን ማህበር የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዐቢይ ማሞ፤ "የካሳንቺስ አያት መኖሪያ መንደር" 13 ሺህ 752 የመኖሪያ ቤቶች በውስጡ እንዳሉት ገልፀዋል።

መኖረያ ቤቶች፣ ንግድ ማዕከላት፣ የህዝብ መሰብሰቢያ ፕላዛዎች፣ የልጆች መጫወቻና የስፖርት ማዘውተርያዎችን፣ መዋለ ህጻናቶች፣ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የጤና ተቋማት፣ የህዝብ መጸዳጃ ቤቶችን፣ የመኪና ቻርጂንግ እስቴሽኖች፣ የመኪና እና የብስክሌት ፓርኪንግን አካቶ በከፍተኛ ጥራትና ፍጥነት የሚገነባ ይሆናል ብለዋል።

በሳሙኤል ወንደሰን
👍9🖕1
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍4
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን ተረከበ
******
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና አለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

አየር መንገዱ በዛሬው ዕለት #ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላንም ተረክቧል። ይህም እያደገ የመጣውን የካርጎ አገልግሎት ለማስተናገድ የራሱ አስተዋፅዖ ይኖረዋል ብሏል።

ይህ አዲስ የካርጎ #አውሮፕላን አየር መንገዱ ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችን ወደ ሀገር ማምጣቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍14
ባለፉት ስድስት ወራት 202 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶችን መሳብ ተችሏል
**
(
ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት 202 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶችን መሳብ መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ ።

አቶ መላኩ እንደገለፁት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ባላት መልካም የውጪ ግንኙነትና የብሪክስ አባል ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅሟ እየጨመረ መጥቷል።

በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት 202 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶችን መሳብ ተችሏል። ከዚህም ከ49 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያሰመዘገቡ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ በአምራች ኢንዱስትሪው ላይ የተንሰራፉትን ችግሮች በቅንጅትና ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ በመፍታት ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አበረታች ውጤት አምጥቷል።

በተለይም ተግባራዊ የሆነው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተኪ ምርትና የኤክስፖርት ምርቶችን በተፈለገው መጠንና ጥራት እንዲመረት በማስቻል በኢኮኖሚው ውስጥ ሊፈጠር የሚችለውን ጫና ከመቀነስ አልፎ ሀገራዊ ምርትን እንዲያሳድግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

መንግስት ባለፉት ሶስት ዓመታት ያደረጋቸው የፖሊሲ ማሻሻያዎች በኢንዱስትሪ ዘርፉ ትልቅ እድል ነው። የኑሮ ውድነትን የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ከኢኮኖሚ ማሻሻያው ባለፈ የምርት መጠንን ማሳደግ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።

በዳግማዊት አበበ

ጥር 16 ቀን 2017 ዓም

#ኢትዮጵያ_ታምርት #አምራች_ኢንዱስትሪ #ኢንቨስትመንት #ብሪክስ
👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ከኢፕድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ያነሷቸው ነጥቦች‼️

👉ፋሲለደስ ለዘመናት የተረሳ ቦታ ነበር፣ አሁን ግን ብርሃን አይቷል፣

👉 ዕድሳቱ የተከናወነው ታሪኩን በሚመጥን መልኩ ነው፣

👉 ዕድሳቱ እየጠፋ ያለውን ታሪክ መመለስ አስችሏል፣

👉 ዕድሳቱና የኮርደር ልማቱ የቱሪስት ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ እንዲጨምር አድርጓል፣

👉 የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር መፅሐፍ ሽያጭ ለዕድሳቱ እንዲውል ተደርጓል፣

#መደመር #ጎንደር #ፋሲለደስ #ቱሪዝም #የቅርሶች_ዕድሳት
👍6
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍3