አትሌት ወርቅነሽ ኢዴሳ የኦሳካ ማራቶን ውድድርን አሸነፈች
*
(ኢ ፕ ድ)
አትሌት ወርቅነሽ ኢዴሳ በጃፓን ኦሳካ በተካሄደ የሴቶች ማራቶን ውድድር አሸናፊ ሆነች።
አትሌት ወርቅነሽ ኢዴሳ ርቀቱን 2 ሰዓት 20 ደቂቃ 59 ሰከንድ በመግባት አንደኛ በመውጣት አሸንፋለች ።
በተያያዘ በስፔን ሚጃ ቴራሳ ግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸንፏል ።
በወንዶች አትሌት ሚኪያስ ባረጋ 1 ሰዓት ከ02 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ በመግባት አሸንፏል ።
አትሌት ሚኪያስ ባረጋ የገባበት ሰዓት የቦታው ክብረወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
በሴቶች አትሌት ኪሮስ ሙዑዝ በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ አትሌት ገነት ሳህለ ሁለተኛ ወጥታለች ።
ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም
*
(ኢ ፕ ድ)
አትሌት ወርቅነሽ ኢዴሳ በጃፓን ኦሳካ በተካሄደ የሴቶች ማራቶን ውድድር አሸናፊ ሆነች።
አትሌት ወርቅነሽ ኢዴሳ ርቀቱን 2 ሰዓት 20 ደቂቃ 59 ሰከንድ በመግባት አንደኛ በመውጣት አሸንፋለች ።
በተያያዘ በስፔን ሚጃ ቴራሳ ግማሽ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸንፏል ።
በወንዶች አትሌት ሚኪያስ ባረጋ 1 ሰዓት ከ02 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ በመግባት አሸንፏል ።
አትሌት ሚኪያስ ባረጋ የገባበት ሰዓት የቦታው ክብረወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።
በሴቶች አትሌት ኪሮስ ሙዑዝ በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ አትሌት ገነት ሳህለ ሁለተኛ ወጥታለች ።
ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም
👍6👏1
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔዎችን አሳለፈ
***
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው የ4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በዚሁም መሰረት ካቢኔው የሀገሪቱን ዲፕሎማሲ ታሳቢ ያደረገ የኤምባሲዎች የመሬት ጥያቄንና የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅቃሴ ለሚያጎለብቱ፣ ሰፊ የስራ እድል እየፈጠሩ ላሉ፣ የዉጭ ምንዛሬ እያስገኙ ላሉ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረቻ ማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎችን መርምሮ ውሳኔ አሳልፏል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
***
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው የ4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
በዚሁም መሰረት ካቢኔው የሀገሪቱን ዲፕሎማሲ ታሳቢ ያደረገ የኤምባሲዎች የመሬት ጥያቄንና የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅቃሴ ለሚያጎለብቱ፣ ሰፊ የስራ እድል እየፈጠሩ ላሉ፣ የዉጭ ምንዛሬ እያስገኙ ላሉ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረቻ ማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎችን መርምሮ ውሳኔ አሳልፏል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍9👏1
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 23 እስከ 25 ድረስ ይካሄዳል
👉 የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ በሶስት ምክንያቶች ዓለም አቀፍ ትኩረት ይስባል
******
(ኢ ፕ ድ)
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 23 እስክ 25 ቀን 2017 ዓም "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሐሳብ እንደሚካሄድ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አደም ፋራህ አስታወቁ።
የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ በሶስት ምክንያቶች ዓለም አቀፍ ትኩረት ይስባል ሲሉም ልጸዋል።
አንደኛ ምክንያት ብልጽግና ፓርቲ ትልቅ ሕዝብ ትልቅ ታሪክ ያላት ታላቅ አገር የሚመራ ገዥ ፓርቲ በመሆኑ ነው። ጉባኤ የሚወሰኑና የሚቀመጡ አቅጣጫዎች ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተጽዕኖ የሚፈጥር በመሆኑ ነው፡፡
ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የብልጽግና ፓርቲ በራሱ ግዙፍ ፓርቲ በመሆኑ ነው፡፡ ፓርቲው መለያውን አካታችነትን፣ ሚዛናዊነትን እና አገር በቀል እሳቤን አድርጎ ትልቅ ሕልምና ርዕይ አንግቦ የሚንቀሳቀስ ግዙፍ ፓርቲ በመሆኑም ጭምር እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ በሁሉም ዘርፎች ፓርቲው ስኬታማ ጉዞ እያደረገ በብዙዎች ዘንድ ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት እንደሚያደርግ የሚጠበቅ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ፓርቲ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
ፓርቲው በሚቀጥሉት ዓመታት ሊያያሳካቸው ያሰባቸውን ስኬቶች በተመለከተ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበትና እስከቀጣዩ ጉባኤ ድረስ ፓርቲውን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች የሚመረጡበት ወሳኝ መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል።
በጉባኤው የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች፣ ከውጭ ሀገራት 15 እህት ፓርቲዎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
በጉባኤው ባለፈው መደበኛ ጉባኤው የተላለፉ ውሳኔዎችና ፓርቲው ያሰቀመጣቸው አቅጣጫዎች ይገመገሙበታል። በቀጣይም ሊሰሩ የሚገባቸው አቅጣጫና ውሳኔ ይተላለፍበታል ተብሏል።
ፓርቲው በአሁኑ ወቅት 15 ነጥብ 7 ሚሊየን አባላት ያሉት እንደሆነ ይታወቃል።
በአስቴር ኤልያስ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👉 የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ በሶስት ምክንያቶች ዓለም አቀፍ ትኩረት ይስባል
******
(ኢ ፕ ድ)
የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 23 እስክ 25 ቀን 2017 ዓም "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሐሳብ እንደሚካሄድ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አደም ፋራህ አስታወቁ።
የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ በሶስት ምክንያቶች ዓለም አቀፍ ትኩረት ይስባል ሲሉም ልጸዋል።
አንደኛ ምክንያት ብልጽግና ፓርቲ ትልቅ ሕዝብ ትልቅ ታሪክ ያላት ታላቅ አገር የሚመራ ገዥ ፓርቲ በመሆኑ ነው። ጉባኤ የሚወሰኑና የሚቀመጡ አቅጣጫዎች ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተጽዕኖ የሚፈጥር በመሆኑ ነው፡፡
ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የብልጽግና ፓርቲ በራሱ ግዙፍ ፓርቲ በመሆኑ ነው፡፡ ፓርቲው መለያውን አካታችነትን፣ ሚዛናዊነትን እና አገር በቀል እሳቤን አድርጎ ትልቅ ሕልምና ርዕይ አንግቦ የሚንቀሳቀስ ግዙፍ ፓርቲ በመሆኑም ጭምር እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ በሁሉም ዘርፎች ፓርቲው ስኬታማ ጉዞ እያደረገ በብዙዎች ዘንድ ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት እንደሚያደርግ የሚጠበቅ ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ፓርቲ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
ፓርቲው በሚቀጥሉት ዓመታት ሊያያሳካቸው ያሰባቸውን ስኬቶች በተመለከተ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበትና እስከቀጣዩ ጉባኤ ድረስ ፓርቲውን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች የሚመረጡበት ወሳኝ መድረክ እንደሆነ ገልጸዋል።
በጉባኤው የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች፣ ከውጭ ሀገራት 15 እህት ፓርቲዎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
በጉባኤው ባለፈው መደበኛ ጉባኤው የተላለፉ ውሳኔዎችና ፓርቲው ያሰቀመጣቸው አቅጣጫዎች ይገመገሙበታል። በቀጣይም ሊሰሩ የሚገባቸው አቅጣጫና ውሳኔ ይተላለፍበታል ተብሏል።
ፓርቲው በአሁኑ ወቅት 15 ነጥብ 7 ሚሊየን አባላት ያሉት እንደሆነ ይታወቃል።
በአስቴር ኤልያስ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍13👎2😁1
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
በብዙ የማህበራዊ ስራዎች ላይ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የሚገኘው MNRC ለኮሪደር ልማት ስራችን ግልጋሎት የሚውል ሶስት የከርብ ስቶን መስሪያ ማሽኖችን በድጋፍ አበርክቶልናል።
ይህ ድጋፍ የነበረውን የከርብ ስቶን ማሽን ችግር በማቃለል የተሻለ ጥራት ያለዉ ስራ በፍጥነት መስራት ያስችለናል።
የMNRC ባለቤት ወ/ሮ ማህደር ገ/መድን ላደረጉልን ድጋፍ በከተማ አስተዳደራችን ስም ላመሰግናቸው እወዳለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
በብዙ የማህበራዊ ስራዎች ላይ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የሚገኘው MNRC ለኮሪደር ልማት ስራችን ግልጋሎት የሚውል ሶስት የከርብ ስቶን መስሪያ ማሽኖችን በድጋፍ አበርክቶልናል።
ይህ ድጋፍ የነበረውን የከርብ ስቶን ማሽን ችግር በማቃለል የተሻለ ጥራት ያለዉ ስራ በፍጥነት መስራት ያስችለናል።
የMNRC ባለቤት ወ/ሮ ማህደር ገ/መድን ላደረጉልን ድጋፍ በከተማ አስተዳደራችን ስም ላመሰግናቸው እወዳለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
❤6👍5👏1
ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በብሪክስ ማዕቀፍ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ
****
(ኢ ፕ ድ)
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲን ጋር በሁለትዮሽና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባም ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው፣ አፍሪካ ኀብረትን ጨምሮ በበርካታ ባለብዙ መድረኮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲ በበኩላቸው ግንኙነቱን ለማሳደግ እንደሚሠሩ ገልፀው፤ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በአፍሪከ ህብረት፣ በብሪክስ ማዕቀፍና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ መድረኮች የጋራ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል።
በመጪው ወር ለሚካሄደው ለ38ኛ የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትም በትብብር እንደሚሰሩ መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲን ጋር በሁለትዮሽና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባም ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው፣ አፍሪካ ኀብረትን ጨምሮ በበርካታ ባለብዙ መድረኮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲ በበኩላቸው ግንኙነቱን ለማሳደግ እንደሚሠሩ ገልፀው፤ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በአፍሪከ ህብረት፣ በብሪክስ ማዕቀፍና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ መድረኮች የጋራ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል።
በመጪው ወር ለሚካሄደው ለ38ኛ የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትም በትብብር እንደሚሰሩ መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍2👏1
ባለፉት 6 ወራት ከ590 ሚሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉ ተገለጸ
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት 6 ወራት 597 ሚሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና መግባታቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ፤ ከ80 በላይ ኢንቨስትመንቶች ኮርፖሬሽኑ ወደ ሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች መሳባቸውን ገልጸዋል።
በተሳቡት ኢንቨስትመንቶች 14 የማምረቻ ሼድና ከ70 ሄክታር በላይ የለማ መሬት ለባለሃብቶቹ ተላልፏል።
ኢንቨስትመንቶቹ በመቐለ፣ ቦሌ ለሚ፣ ቂሊንጦ፣ ኮምቦልቻ፣ ድሬዳዋ ልዩ ነፃ ንግድ ቀጠና፣ ጅማና ሰመራ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሰማሩ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተመሰረተበትን 10ኛ ዓመትና የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ ተካሂዷል፡፡
#ኢንቨስትመንት #ልዩ_የኢኮኖሚ_ዞኖ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት 6 ወራት 597 ሚሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና መግባታቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ፤ ከ80 በላይ ኢንቨስትመንቶች ኮርፖሬሽኑ ወደ ሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች መሳባቸውን ገልጸዋል።
በተሳቡት ኢንቨስትመንቶች 14 የማምረቻ ሼድና ከ70 ሄክታር በላይ የለማ መሬት ለባለሃብቶቹ ተላልፏል።
ኢንቨስትመንቶቹ በመቐለ፣ ቦሌ ለሚ፣ ቂሊንጦ፣ ኮምቦልቻ፣ ድሬዳዋ ልዩ ነፃ ንግድ ቀጠና፣ ጅማና ሰመራ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሰማሩ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተመሰረተበትን 10ኛ ዓመትና የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ ተካሂዷል፡፡
#ኢንቨስትመንት #ልዩ_የኢኮኖሚ_ዞኖ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍3❤1👏1
ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሰረት የጣሉ ተግባራት ተከናውነዋል- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሰረት የጣሉ ተግባራት ተከናውነዋል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ዛሬ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እና ውጥኖችን የተመለከተ ኤግዚቢሽንና ዐውደ ጥናት አካሂደናል ብለዋል።
መንግሥት ከለውጡ ማግሥት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ሀገራችን የቴክኖሎጂ ዕድገት ዕድሎችን እንድትጠቀም የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማት በመሥፋፋቱ የፋይናንስና የክፍያ ስርዓት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።
የመንግሥት አገልግሎቶችን የማዘመንና ወደ ዲጂታል የማሸጋገር እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ መጨመሩንም ገልጸዋል።
የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራዎች የተቀናጁ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ የሃብት ብክነትን የማያስከትሉ፣ የዜጎቻችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ፈጣን ለውጥ የሚያመጡ እንዲሆኑ መንግሥት የጀመረውን ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
የመጀመሪያውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ እያጠናቀቅን በመሆኑም በቀጣይ 5 ዓመታት ስራ ላይ የሚውል የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዝግጅት እያጠናቀቅን እንገኛለን ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሰረት የጣሉ ተግባራት ተከናውነዋል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ዛሬ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እና ውጥኖችን የተመለከተ ኤግዚቢሽንና ዐውደ ጥናት አካሂደናል ብለዋል።
መንግሥት ከለውጡ ማግሥት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ሀገራችን የቴክኖሎጂ ዕድገት ዕድሎችን እንድትጠቀም የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማት በመሥፋፋቱ የፋይናንስና የክፍያ ስርዓት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።
የመንግሥት አገልግሎቶችን የማዘመንና ወደ ዲጂታል የማሸጋገር እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ መጨመሩንም ገልጸዋል።
የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራዎች የተቀናጁ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ የሃብት ብክነትን የማያስከትሉ፣ የዜጎቻችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ፈጣን ለውጥ የሚያመጡ እንዲሆኑ መንግሥት የጀመረውን ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
የመጀመሪያውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ እያጠናቀቅን በመሆኑም በቀጣይ 5 ዓመታት ስራ ላይ የሚውል የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዝግጅት እያጠናቀቅን እንገኛለን ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍5👏1
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው ሀገራት ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀመጠች
*******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ባለፉት አምስት አመታት ውስጥ የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሞሮኮንና ግብጽን በማስከተል የጎብኝዎች ቁጥር ከነበረበት መጠን በ40 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
ከዓለም ኳታርን፣ ኤል ሳልቫዶርን፣ አልቤንያን፣ ሳዑዲዓረቢያንና ኩራካዎን በመከተል ስድስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
እአአ ከ2019 ወዲህ ባስመዘገበችው የቱሪስት ፍሰት መጠን ኢትዮጵያ ከአለም ሃገራት ስድስተኛ፤ ከአፍሪካ ደግሞ ሞሮኮና ግብፅን በማስከተል ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
#ምድረቀደምት #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ቱሪስት
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ባለፉት አምስት አመታት ውስጥ የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሞሮኮንና ግብጽን በማስከተል የጎብኝዎች ቁጥር ከነበረበት መጠን በ40 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
ከዓለም ኳታርን፣ ኤል ሳልቫዶርን፣ አልቤንያን፣ ሳዑዲዓረቢያንና ኩራካዎን በመከተል ስድስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
እአአ ከ2019 ወዲህ ባስመዘገበችው የቱሪስት ፍሰት መጠን ኢትዮጵያ ከአለም ሃገራት ስድስተኛ፤ ከአፍሪካ ደግሞ ሞሮኮና ግብፅን በማስከተል ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
#ምድረቀደምት #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ቱሪስት
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍16😁2👏1
በህገ-ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ2 ሺህ ሊትር በላይ ቤንዚን ተያዘ
*****
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በህገ-ወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚን ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡
መንግስት የነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለቱ በህጋዊ መንገድ እንዲደረግና ግብይቱም በቴሌ ብር ብቻ እንዲሆን ከማድረግ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ፖሊስ ባደረገው ክትትል በህገወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚል ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህብረተሰቡ በመሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦችን ሲመለከት ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት አዋጅን ማፅደቁ ይታወሳል።
አዋጁ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ከአስመጪው ጀምሮ እስከ መጨረሻው ተጠቃሚ ድረስ ቴክኖሎጂ የተደገፈ፤ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ እየታዩ ያሉ ሕገ-ወጥ ተግዳሮቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችልና ሕጋዊ የነዳጅ ውጤቶች የግብይት ሥርዓትን ለማስፈን ያስችላል ተብሏል።
#አዋጅ #የነዳጅ_ውጤቶች #የችርቻሮ_መሸጫ_ዋጋ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
*****
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በህገ-ወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚን ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡
መንግስት የነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለቱ በህጋዊ መንገድ እንዲደረግና ግብይቱም በቴሌ ብር ብቻ እንዲሆን ከማድረግ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ፖሊስ ባደረገው ክትትል በህገወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚል ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህብረተሰቡ በመሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦችን ሲመለከት ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት አዋጅን ማፅደቁ ይታወሳል።
አዋጁ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ከአስመጪው ጀምሮ እስከ መጨረሻው ተጠቃሚ ድረስ ቴክኖሎጂ የተደገፈ፤ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ እየታዩ ያሉ ሕገ-ወጥ ተግዳሮቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችልና ሕጋዊ የነዳጅ ውጤቶች የግብይት ሥርዓትን ለማስፈን ያስችላል ተብሏል።
#አዋጅ #የነዳጅ_ውጤቶች #የችርቻሮ_መሸጫ_ዋጋ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍6👏1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የአፍሪካ ኢነርጂ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ዳሬ ሰላም ገቡ
****
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የሚሳተፉበት የኢነርጂ ጉባዔ በነገው ዕለት በታንዛኒያ ይካሄዳል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብተዋል። ዳሬ ሰላም ጁሊየስ ኒዬሬሬ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጉባዔው እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ለ300 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በሚደረግበት መንገድ ላይ እንደሚመክር ኢቢሲ ዘግቧል።
ለ600 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ አለመሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የሚሳተፉበት የኢነርጂ ጉባዔ በነገው ዕለት በታንዛኒያ ይካሄዳል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብተዋል። ዳሬ ሰላም ጁሊየስ ኒዬሬሬ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጉባዔው እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ለ300 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በሚደረግበት መንገድ ላይ እንደሚመክር ኢቢሲ ዘግቧል።
ለ600 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ አለመሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍16👏1