ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በብሪክስ ማዕቀፍ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ
****
(ኢ ፕ ድ)
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲን ጋር በሁለትዮሽና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባም ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው፣ አፍሪካ ኀብረትን ጨምሮ በበርካታ ባለብዙ መድረኮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲ በበኩላቸው ግንኙነቱን ለማሳደግ እንደሚሠሩ ገልፀው፤ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በአፍሪከ ህብረት፣ በብሪክስ ማዕቀፍና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ መድረኮች የጋራ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል።
በመጪው ወር ለሚካሄደው ለ38ኛ የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትም በትብብር እንደሚሰሩ መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲን ጋር በሁለትዮሽና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባም ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ ጠንካራ የሁለትዮሽ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው፣ አፍሪካ ኀብረትን ጨምሮ በበርካታ ባለብዙ መድረኮች ላይም በትብብር እንደሚሰሩ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኢኖንሴባ ሎሲ በበኩላቸው ግንኙነቱን ለማሳደግ እንደሚሠሩ ገልፀው፤ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በአፍሪከ ህብረት፣ በብሪክስ ማዕቀፍና በሌሎች ዓለም ዓቀፍ መድረኮች የጋራ ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል።
በመጪው ወር ለሚካሄደው ለ38ኛ የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬትም በትብብር እንደሚሰሩ መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍2👏1
ባለፉት 6 ወራት ከ590 ሚሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉ ተገለጸ
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት 6 ወራት 597 ሚሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና መግባታቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ፤ ከ80 በላይ ኢንቨስትመንቶች ኮርፖሬሽኑ ወደ ሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች መሳባቸውን ገልጸዋል።
በተሳቡት ኢንቨስትመንቶች 14 የማምረቻ ሼድና ከ70 ሄክታር በላይ የለማ መሬት ለባለሃብቶቹ ተላልፏል።
ኢንቨስትመንቶቹ በመቐለ፣ ቦሌ ለሚ፣ ቂሊንጦ፣ ኮምቦልቻ፣ ድሬዳዋ ልዩ ነፃ ንግድ ቀጠና፣ ጅማና ሰመራ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሰማሩ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተመሰረተበትን 10ኛ ዓመትና የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ ተካሂዷል፡፡
#ኢንቨስትመንት #ልዩ_የኢኮኖሚ_ዞኖ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት 6 ወራት 597 ሚሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና መግባታቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ፤ ከ80 በላይ ኢንቨስትመንቶች ኮርፖሬሽኑ ወደ ሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች መሳባቸውን ገልጸዋል።
በተሳቡት ኢንቨስትመንቶች 14 የማምረቻ ሼድና ከ70 ሄክታር በላይ የለማ መሬት ለባለሃብቶቹ ተላልፏል።
ኢንቨስትመንቶቹ በመቐለ፣ ቦሌ ለሚ፣ ቂሊንጦ፣ ኮምቦልቻ፣ ድሬዳዋ ልዩ ነፃ ንግድ ቀጠና፣ ጅማና ሰመራ ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሰማሩ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተመሰረተበትን 10ኛ ዓመትና የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ ተካሂዷል፡፡
#ኢንቨስትመንት #ልዩ_የኢኮኖሚ_ዞኖ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍3❤1👏1
ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሰረት የጣሉ ተግባራት ተከናውነዋል- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሰረት የጣሉ ተግባራት ተከናውነዋል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ዛሬ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እና ውጥኖችን የተመለከተ ኤግዚቢሽንና ዐውደ ጥናት አካሂደናል ብለዋል።
መንግሥት ከለውጡ ማግሥት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ሀገራችን የቴክኖሎጂ ዕድገት ዕድሎችን እንድትጠቀም የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማት በመሥፋፋቱ የፋይናንስና የክፍያ ስርዓት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።
የመንግሥት አገልግሎቶችን የማዘመንና ወደ ዲጂታል የማሸጋገር እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ መጨመሩንም ገልጸዋል።
የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራዎች የተቀናጁ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ የሃብት ብክነትን የማያስከትሉ፣ የዜጎቻችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ፈጣን ለውጥ የሚያመጡ እንዲሆኑ መንግሥት የጀመረውን ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
የመጀመሪያውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ እያጠናቀቅን በመሆኑም በቀጣይ 5 ዓመታት ስራ ላይ የሚውል የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዝግጅት እያጠናቀቅን እንገኛለን ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሰረት የጣሉ ተግባራት ተከናውነዋል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ዛሬ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ እና ውጥኖችን የተመለከተ ኤግዚቢሽንና ዐውደ ጥናት አካሂደናል ብለዋል።
መንግሥት ከለውጡ ማግሥት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ሀገራችን የቴክኖሎጂ ዕድገት ዕድሎችን እንድትጠቀም የሚያስችሉ ተግባራትን አከናውኗል ብለዋል።
የዲጂታል መሠረተ ልማት በመሥፋፋቱ የፋይናንስና የክፍያ ስርዓት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ተናግረዋል።
የመንግሥት አገልግሎቶችን የማዘመንና ወደ ዲጂታል የማሸጋገር እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ መጨመሩንም ገልጸዋል።
የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራዎች የተቀናጁ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ የሃብት ብክነትን የማያስከትሉ፣ የዜጎቻችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ፈጣን ለውጥ የሚያመጡ እንዲሆኑ መንግሥት የጀመረውን ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
የመጀመሪያውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ትግበራ እያጠናቀቅን በመሆኑም በቀጣይ 5 ዓመታት ስራ ላይ የሚውል የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዝግጅት እያጠናቀቅን እንገኛለን ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍5👏1
ኢትዮጵያ በአፍሪካ የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው ሀገራት ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀመጠች
*******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ባለፉት አምስት አመታት ውስጥ የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሞሮኮንና ግብጽን በማስከተል የጎብኝዎች ቁጥር ከነበረበት መጠን በ40 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
ከዓለም ኳታርን፣ ኤል ሳልቫዶርን፣ አልቤንያን፣ ሳዑዲዓረቢያንና ኩራካዎን በመከተል ስድስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
እአአ ከ2019 ወዲህ ባስመዘገበችው የቱሪስት ፍሰት መጠን ኢትዮጵያ ከአለም ሃገራት ስድስተኛ፤ ከአፍሪካ ደግሞ ሞሮኮና ግብፅን በማስከተል ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
#ምድረቀደምት #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ቱሪስት
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ባለፉት አምስት አመታት ውስጥ የጎብኚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት መረጃ አመልክቷል።
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሞሮኮንና ግብጽን በማስከተል የጎብኝዎች ቁጥር ከነበረበት መጠን በ40 በመቶ ዕድገት አሳይቷል።
ከዓለም ኳታርን፣ ኤል ሳልቫዶርን፣ አልቤንያን፣ ሳዑዲዓረቢያንና ኩራካዎን በመከተል ስድስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
እአአ ከ2019 ወዲህ ባስመዘገበችው የቱሪስት ፍሰት መጠን ኢትዮጵያ ከአለም ሃገራት ስድስተኛ፤ ከአፍሪካ ደግሞ ሞሮኮና ግብፅን በማስከተል ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
#ምድረቀደምት #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ቱሪስት
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍16😁2👏1
በህገ-ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ2 ሺህ ሊትር በላይ ቤንዚን ተያዘ
*****
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በህገ-ወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚን ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡
መንግስት የነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለቱ በህጋዊ መንገድ እንዲደረግና ግብይቱም በቴሌ ብር ብቻ እንዲሆን ከማድረግ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ፖሊስ ባደረገው ክትትል በህገወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚል ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህብረተሰቡ በመሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦችን ሲመለከት ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት አዋጅን ማፅደቁ ይታወሳል።
አዋጁ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ከአስመጪው ጀምሮ እስከ መጨረሻው ተጠቃሚ ድረስ ቴክኖሎጂ የተደገፈ፤ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ እየታዩ ያሉ ሕገ-ወጥ ተግዳሮቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችልና ሕጋዊ የነዳጅ ውጤቶች የግብይት ሥርዓትን ለማስፈን ያስችላል ተብሏል።
#አዋጅ #የነዳጅ_ውጤቶች #የችርቻሮ_መሸጫ_ዋጋ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
*****
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በህገ-ወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚን ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡
መንግስት የነዳጅ አቅርቦት ሰንሰለቱ በህጋዊ መንገድ እንዲደረግና ግብይቱም በቴሌ ብር ብቻ እንዲሆን ከማድረግ ጀምሮ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ፖሊስ ባደረገው ክትትል በህገወጥ መንገድ በአንድ ኮንቴነር ውስጥ በጀሪካን ተሸሽጎ የነበረ 2 ሺህ 360 ሊትር ቤንዚል ከሁለት ግለሰቦች ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህብረተሰቡ በመሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦችን ሲመለከት ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት አዋጅን ማፅደቁ ይታወሳል።
አዋጁ የነዳጅ ውጤቶች ግብይት ከአስመጪው ጀምሮ እስከ መጨረሻው ተጠቃሚ ድረስ ቴክኖሎጂ የተደገፈ፤ የግብይት ሰንሰለት ውስጥ እየታዩ ያሉ ሕገ-ወጥ ተግዳሮቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችልና ሕጋዊ የነዳጅ ውጤቶች የግብይት ሥርዓትን ለማስፈን ያስችላል ተብሏል።
#አዋጅ #የነዳጅ_ውጤቶች #የችርቻሮ_መሸጫ_ዋጋ
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍6👏1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የአፍሪካ ኢነርጂ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ዳሬ ሰላም ገቡ
****
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የሚሳተፉበት የኢነርጂ ጉባዔ በነገው ዕለት በታንዛኒያ ይካሄዳል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብተዋል። ዳሬ ሰላም ጁሊየስ ኒዬሬሬ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጉባዔው እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ለ300 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በሚደረግበት መንገድ ላይ እንደሚመክር ኢቢሲ ዘግቧል።
ለ600 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ አለመሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የሚሳተፉበት የኢነርጂ ጉባዔ በነገው ዕለት በታንዛኒያ ይካሄዳል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ታንዛኒያ ዳሬ ሰላም ገብተዋል። ዳሬ ሰላም ጁሊየስ ኒዬሬሬ አየር ማረፊያ ሲደርሱ በሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጉባዔው እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ ለ300 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በሚደረግበት መንገድ ላይ እንደሚመክር ኢቢሲ ዘግቧል።
ለ600 ሚሊዮን አፍሪካውያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ አለመሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጥር 19 ቀን 2017 ዓም
👍16👏1
ህይወት ፋና ሪፈራል ሆስፒታል ከ300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የካንሰር ህክምና እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለጸ
******
(ኢ ፕ ድ)
ህይወት ፋና ሪፈራል ሆስፒታል ከ300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የካንሰር ህክምና እየሰጠ እንደሚገኝ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይስሐቅ የሱፍ ገለፁ።
የካንሰር ህክምና ማዕከሉ ለምስራቁ የሀገሪቷ ክፍል አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይስሐቅ የሱፍ ለኢፕድ እንደገለፁት ከ300 እስከ 400 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ታማሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ሶማሊያ እና ጅቡቲ ሀገራት የካንሰር ታማሚዎች በሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን አብራርተዋል።
በሆስፒታሉ የኬሞ ቴራፒና የጨረር ህክምና አገልግሎት ለካንሰር ታካሚዎች እየተሰጠ ነው ያሉት ዶክተር ይስሐቅ፤ የህክምና አገልግሎት አሰጣጡ እንዲሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ከጤና ዘርፍ ባለፈ የማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በአማን ረሺድ
ጥር 20 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ህይወት ፋና ሪፈራል ሆስፒታል ከ300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የካንሰር ህክምና እየሰጠ እንደሚገኝ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይስሐቅ የሱፍ ገለፁ።
የካንሰር ህክምና ማዕከሉ ለምስራቁ የሀገሪቷ ክፍል አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ይስሐቅ የሱፍ ለኢፕድ እንደገለፁት ከ300 እስከ 400 ለሚሆኑ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ታማሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ሶማሊያ እና ጅቡቲ ሀገራት የካንሰር ታማሚዎች በሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን አብራርተዋል።
በሆስፒታሉ የኬሞ ቴራፒና የጨረር ህክምና አገልግሎት ለካንሰር ታካሚዎች እየተሰጠ ነው ያሉት ዶክተር ይስሐቅ፤ የህክምና አገልግሎት አሰጣጡ እንዲሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ከጤና ዘርፍ ባለፈ የማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በአማን ረሺድ
ጥር 20 ቀን 2017 ዓም
👍12
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ ዶ/ር ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️
👉 ከቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም 913 ሚሊዮን ዶላር፤ ከአበባ አትክልትና ፍራፍሬ 263 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፣
👉 ከእንስሳትና እንስሳት ተዋፅዖ 54 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፣
👉 አንድ ነጥብ 92 ሚሊዮን ላሞችን ማዳቀል ተችሏል፣
👉 የወተት ምርት 7 ቢሊዮን ሊትር ወተት ማምረት ተችሏል፣
👉 የእንቁላል ምርትን 4 ቢሊዮን ለማምረት ታቅዶ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ተገኝቷል፣
👉 116 ሺህ ቶን የዶሮ ሥጋ ለማምረት ታቅዶ 105 ሺህ ቶን ማምረት ተችሏል፣
👉 102 ሺህ ቶን የዓሣ ምርት ለማምረት ታቅዶ 91 ሺህ ቶን የዓሣ ምርት ማምረት ተችሏል፣
👉 የአንድ ቀን ጫጩት 61 ነጥብ 5 ሚሊዮን፤ የዓሣ ጫጩት 3 ነጥብ 91 ሚሊዮን ተሰራጭቷል፣
👉 የአንድ ቀን ጫጩት አቅርቦት ለመጨመር የቅድመ ወላጅ ዶሮ ማባዥ ማዕከል ተቋቁሟል፣
👉 ከሁሉም የእንስሳት መኖ ምንጮች 135 ሚሊዮን ቶን ለማምረት ታቅዶ 129 ሚሊዮን ቶን ማከናወን ተችሏል፣
👉 167 ሚሊዮን እንስሳት ለመከተብ ታቅዶ 180 ሚሊዮን እንስሳት መከተብ ተችሏል፣
በአጠቃላይ ከቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ከአበባ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ከእንስሳትና እንስሳት ተዋፅዖ 1.23 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል። በሌሎች ተቋማት ክትትል የሚደረግባቸውን ወጭ የግብርና ምርቶችን ጨምሮ አንድ ነጥብ 61 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ብለዋል::
መንግስት የወሰደው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ ለወጭ የግብርና ምርቶች አፈፃፀም ዕድገት አስተዋዖ አድርጓል።
#በሌማት_ትሩፋት #የዓሣ_ሀብት #ቡና
👉 ከቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም 913 ሚሊዮን ዶላር፤ ከአበባ አትክልትና ፍራፍሬ 263 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፣
👉 ከእንስሳትና እንስሳት ተዋፅዖ 54 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፣
👉 አንድ ነጥብ 92 ሚሊዮን ላሞችን ማዳቀል ተችሏል፣
👉 የወተት ምርት 7 ቢሊዮን ሊትር ወተት ማምረት ተችሏል፣
👉 የእንቁላል ምርትን 4 ቢሊዮን ለማምረት ታቅዶ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ተገኝቷል፣
👉 116 ሺህ ቶን የዶሮ ሥጋ ለማምረት ታቅዶ 105 ሺህ ቶን ማምረት ተችሏል፣
👉 102 ሺህ ቶን የዓሣ ምርት ለማምረት ታቅዶ 91 ሺህ ቶን የዓሣ ምርት ማምረት ተችሏል፣
👉 የአንድ ቀን ጫጩት 61 ነጥብ 5 ሚሊዮን፤ የዓሣ ጫጩት 3 ነጥብ 91 ሚሊዮን ተሰራጭቷል፣
👉 የአንድ ቀን ጫጩት አቅርቦት ለመጨመር የቅድመ ወላጅ ዶሮ ማባዥ ማዕከል ተቋቁሟል፣
👉 ከሁሉም የእንስሳት መኖ ምንጮች 135 ሚሊዮን ቶን ለማምረት ታቅዶ 129 ሚሊዮን ቶን ማከናወን ተችሏል፣
👉 167 ሚሊዮን እንስሳት ለመከተብ ታቅዶ 180 ሚሊዮን እንስሳት መከተብ ተችሏል፣
በአጠቃላይ ከቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ከአበባ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ከእንስሳትና እንስሳት ተዋፅዖ 1.23 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል። በሌሎች ተቋማት ክትትል የሚደረግባቸውን ወጭ የግብርና ምርቶችን ጨምሮ አንድ ነጥብ 61 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ብለዋል::
መንግስት የወሰደው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ ለወጭ የግብርና ምርቶች አፈፃፀም ዕድገት አስተዋዖ አድርጓል።
#በሌማት_ትሩፋት #የዓሣ_ሀብት #ቡና
👍12
በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር ደርሷል
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር መድረሱን የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ገለጹ።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር ደርሷል። የሀገሪቱ ባንኮች ከዓመት ዓመት በተቀማጭ ገንዘብ፣ አጠቃላይ ባላቸው የፋይናንስ እሴት ለውጥ እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በቅርቡ የውጭ ባንኮች ሀገር ቤት ገብተው እንዲሠሩ የጸደቀው አዋጅ በዋናነት የውጭ ባለሀብቶች በባንክ መስክ ተሰማርተው ለኢኮኖሚው አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ነው ያሉት አቶ ማሞ፤ የዘርፉን ተወዳዳሪነት በማሻሻል ባንኮች በኢኮኖሚው ውስጥ የሚጫወቱትን ሚና ከፍ ለማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል።
የባንክ ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ማለት የኢትዮጵያ ባንኮች ችግር ላይ ይወድቃሉ ማለት አይደለም። የሀገር ውስጥ ባንኮች አዳዲስ አሠራርና አገልግሎት ተምረው ለኢኮኖሚ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ይጨምራል።
#ባንኮች #የውጭ_ባንኮች #ፋይናንስ #የውጭ_ባለሀብቶች
https://press.et/?p=144629
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር መድረሱን የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ገለጹ።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፉ ተቀማጭ ገንዘብ ሁለት ነጥብ 74 ትሪሊዮን ብር ደርሷል። የሀገሪቱ ባንኮች ከዓመት ዓመት በተቀማጭ ገንዘብ፣ አጠቃላይ ባላቸው የፋይናንስ እሴት ለውጥ እያመጡ መሆኑን ገልጸዋል።
በቅርቡ የውጭ ባንኮች ሀገር ቤት ገብተው እንዲሠሩ የጸደቀው አዋጅ በዋናነት የውጭ ባለሀብቶች በባንክ መስክ ተሰማርተው ለኢኮኖሚው አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ነው ያሉት አቶ ማሞ፤ የዘርፉን ተወዳዳሪነት በማሻሻል ባንኮች በኢኮኖሚው ውስጥ የሚጫወቱትን ሚና ከፍ ለማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል።
የባንክ ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ ማለት የኢትዮጵያ ባንኮች ችግር ላይ ይወድቃሉ ማለት አይደለም። የሀገር ውስጥ ባንኮች አዳዲስ አሠራርና አገልግሎት ተምረው ለኢኮኖሚ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ ይጨምራል።
#ባንኮች #የውጭ_ባንኮች #ፋይናንስ #የውጭ_ባለሀብቶች
https://press.et/?p=144629
👍8❤1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍10❤1