“የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው”- ዕምሩ ገመቹ (ዶ/ር)
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን፤ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካና ዓለም አቀፍ ግኑኙነት መምህር እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የሌላ ሀገር ወደብ መጠቀም ከድንገተኛ ቀውሶች ጋር በተያያዘ ዋስትና እንደማይኖረውም አስታውቀዋል።
እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ሀገሪቱ ያለችበት የቀይ ባሕርና የህንድ ውቂያኖስ አካባቢ ካለው ጂኦፖለቲካል ስትራቴጂክ አኳያ፤ በርካታ ሀገራት አካባቢውን የመቆጣጠር ፍላጎት አላቸው፤ ይህም እንደ ሀገር የደህንነት ስጋት ይዞ ሊመጣ የሚችል ነው።
ሀገሪቱ የባሕር በር ባለቤት ብትሆን ፤ ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ በተጓዳኝ የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚኖራት አበርክቶ ከፍ ያለ እንደሚሆን የጠቆሙት መምህሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረክ የሚኖራት ተደማጭነትን ይጨምራል።
የኢንቨስትመንት ስበት በመፍጠር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ እንዲያለሙ መደላድል ይፈጠራል፤ የተለያዩ ድጋፎችን እንድታገኝ ይረዳል፤ ይህም ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ አንጻር አስተዋጽኦ ይኖረዋል። https://press.et/?p=147260
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን፤ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካና ዓለም አቀፍ ግኑኙነት መምህር እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የሌላ ሀገር ወደብ መጠቀም ከድንገተኛ ቀውሶች ጋር በተያያዘ ዋስትና እንደማይኖረውም አስታውቀዋል።
እምሩ ገመቹ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ሀገሪቱ ያለችበት የቀይ ባሕርና የህንድ ውቂያኖስ አካባቢ ካለው ጂኦፖለቲካል ስትራቴጂክ አኳያ፤ በርካታ ሀገራት አካባቢውን የመቆጣጠር ፍላጎት አላቸው፤ ይህም እንደ ሀገር የደህንነት ስጋት ይዞ ሊመጣ የሚችል ነው።
ሀገሪቱ የባሕር በር ባለቤት ብትሆን ፤ ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ በተጓዳኝ የአካባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ የሚኖራት አበርክቶ ከፍ ያለ እንደሚሆን የጠቆሙት መምህሩ፤ በዓለም አቀፍ መድረክ የሚኖራት ተደማጭነትን ይጨምራል።
የኢንቨስትመንት ስበት በመፍጠር ባለሀብቶች በኢትዮጵያ እንዲያለሙ መደላድል ይፈጠራል፤ የተለያዩ ድጋፎችን እንድታገኝ ይረዳል፤ ይህም ብሄራዊ ጥቅሟን ከማስጠበቅ አንጻር አስተዋጽኦ ይኖረዋል። https://press.et/?p=147260
👎2👏2
"ዛሬ በምሥራቅ ሐረርጌ ቆላማ አካባቢዎች እየለማ የሚገኝ የበጋ ስንዴ ልማትን ተመልክተናል። መትጋት፥መሥራት፥ ማየት ከቻልን፣ ኢትዮጵያ ከመረዳት አልፋ ሌሎችን መርዳት ትችላለች። ይህንን ስራ አጠናክረን እንድንቀጥል አደራ እላለሁ"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👏2👍1
የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በ2017 በጀት ዓመት እስከ አሁን ከ500 ሺህ ኩንታል በላይ ስኳር አምርቷል
****
(ኢ ፕ ድ)
የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በ2017 በጀት ዓመት እስከ አሁን ከ500 ሺህ ኩንታል በላይ ስኳር ማምረቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ።
ፋብሪካው የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ(ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አወሉ አብዲ እና የተቋሙ አመራሮች የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
ጉብኝቱ የተቋሙን አፈጻጸም መገምገምና የመሰረተ ልማት አቅሙን መፈተሽ እንደሆነ ተገልጿል።
ፋብሪካው በበጀት ዓመቱ ማብቂያ ለማምረት ያቀደውን የአንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር እቅድ ለማሳካት በትክክለኛ መስመር ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ፋብሪካው ከዋና ምርቱ በተጓዳኝ የግብርና ምርቶችን በማምረት ለሰራተኞቹና ለአካባቢው ማህበረሰብ እንቁላል፣ አሳና አትክልቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አመራሮች ኩባንያው በግብርናው መስክ እያሳየ ያለው ለውጥ፣ የሜካናይዜሽን አጠቃቀምን በማሳደግ፣ የእርሻ ስራዎችን በማስፋፋት፣ በአቅም ግንባታ እና ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመጠቀም እያስመዘገበ ያለው ውጤት መልካም እንደሆነ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ መረጃ ያመለክታል።
#ወንጂሸዋ
መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በ2017 በጀት ዓመት እስከ አሁን ከ500 ሺህ ኩንታል በላይ ስኳር ማምረቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስታወቀ።
ፋብሪካው የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ(ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አወሉ አብዲ እና የተቋሙ አመራሮች የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።
ጉብኝቱ የተቋሙን አፈጻጸም መገምገምና የመሰረተ ልማት አቅሙን መፈተሽ እንደሆነ ተገልጿል።
ፋብሪካው በበጀት ዓመቱ ማብቂያ ለማምረት ያቀደውን የአንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር እቅድ ለማሳካት በትክክለኛ መስመር ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ፋብሪካው ከዋና ምርቱ በተጓዳኝ የግብርና ምርቶችን በማምረት ለሰራተኞቹና ለአካባቢው ማህበረሰብ እንቁላል፣ አሳና አትክልቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አመራሮች ኩባንያው በግብርናው መስክ እያሳየ ያለው ለውጥ፣ የሜካናይዜሽን አጠቃቀምን በማሳደግ፣ የእርሻ ስራዎችን በማስፋፋት፣ በአቅም ግንባታ እና ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በመጠቀም እያስመዘገበ ያለው ውጤት መልካም እንደሆነ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ መረጃ ያመለክታል።
#ወንጂሸዋ
መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓም
👍8👏1
ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት የመንገድ ደህንነት ፈንድ የቦርድ አባል ሆነው ተሾሙ
*****
(ኢ ፕ ድ)
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት የመንገድ ደህንነት ፈንድ (ዩኤንአርኤስኤፍ) የቦርድ አባል ሆነው ተሾመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሀገራዊ የመንገድ ደህንነት ስትራቴጂ በመቅረፅና የመንገድ ደህንነት ትምህርት በስርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት በማድረግ የወሰደችው እርምጃ የመንገድ ደህንነትን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን ለሚኒስትሩ በተፃፈው የሹመት ደብዳቤ ተገልጿል፡፡
በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ስራዎች የተገነቡ ምቹ የብስክሌትና የእግረኛ መንገዶች እንዲሁም የተሻሻሉ የመንገድ ትስስር ስራዎች እንደ ሀገር የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ቅንጅትን የሚያሳድጉ መሆናቸውም በደብዳቤው ተጠቁሟል፡፡
የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ኢትዮጵያ በመንገድ ደህንነት ላይ ያላትን ቁርጠኝነትና የምታደርገውን ጥረት በመገንዘብና እውቅና በመስጠት ዓለሙ ስሜን (ዶ/ር) በዩኤንአርኤስኤፍ ስር የባለአደራዎች ቦርድ የቦርድ አባል ሆነው መሾማቸውን አሳውቋል፡፡
የሚኒስትሩ በቦርድ አባልነት መሾም ኢትዮጵያ ልምዷን ለሌሎች ሀገራት እንድታጋራና ከመላው ዓለም በመንገድ ደህንነት ላይ የተሻሉ ተሞክሮዎችን እንድታገኝ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ነው ተብሏል።
ዩኤንአርኤስኤፍ በፈረንጆቹ 2018 ሚያዚያ ወር ላይ የተመሠረተ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታ ላላቸው ፕሮጀክቶች ተጨማሪ ገንዘብ የማሰባሰብ እና የመደገፍ ስራን የሚሰራ ተቋም እንደሆነም የትራስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት የመንገድ ደህንነት ፈንድ (ዩኤንአርኤስኤፍ) የቦርድ አባል ሆነው ተሾመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሀገራዊ የመንገድ ደህንነት ስትራቴጂ በመቅረፅና የመንገድ ደህንነት ትምህርት በስርዓተ ትምህርት ውስጥ እንዲካተት በማድረግ የወሰደችው እርምጃ የመንገድ ደህንነትን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን ለሚኒስትሩ በተፃፈው የሹመት ደብዳቤ ተገልጿል፡፡
በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ስራዎች የተገነቡ ምቹ የብስክሌትና የእግረኛ መንገዶች እንዲሁም የተሻሻሉ የመንገድ ትስስር ስራዎች እንደ ሀገር የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ቅንጅትን የሚያሳድጉ መሆናቸውም በደብዳቤው ተጠቁሟል፡፡
የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ኢትዮጵያ በመንገድ ደህንነት ላይ ያላትን ቁርጠኝነትና የምታደርገውን ጥረት በመገንዘብና እውቅና በመስጠት ዓለሙ ስሜን (ዶ/ር) በዩኤንአርኤስኤፍ ስር የባለአደራዎች ቦርድ የቦርድ አባል ሆነው መሾማቸውን አሳውቋል፡፡
የሚኒስትሩ በቦርድ አባልነት መሾም ኢትዮጵያ ልምዷን ለሌሎች ሀገራት እንድታጋራና ከመላው ዓለም በመንገድ ደህንነት ላይ የተሻሉ ተሞክሮዎችን እንድታገኝ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ነው ተብሏል።
ዩኤንአርኤስኤፍ በፈረንጆቹ 2018 ሚያዚያ ወር ላይ የተመሠረተ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ጠቀሜታ ላላቸው ፕሮጀክቶች ተጨማሪ ገንዘብ የማሰባሰብ እና የመደገፍ ስራን የሚሰራ ተቋም እንደሆነም የትራስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓም
👍3👏2