Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ብሬነሽ ደሴ ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድርን አሸነፈች
****
(ኢ ፕ ድ)

የ2017 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሜ ሩጫ ውድድር ብሬነሽ ደሴ ከግሎባል ስፖርት በአንደኝነት አጠናቀቀች።

በግሏ የተወዳደረችው አብዙ ከበደ 2ኛ ደረጃን ይዛ የብር ሜዳልያ አሸናፊ ሆናለች። መቅደስ ሽመልስ ደግሞ 3ኛ በመሆን የነሀስ ሜዳሊያ ተሻላሚ ሆናለች። ለአሸናፊዎቹ ከ50 ሺህ ብር ጀምሮ ሽልማትም ተበርክቶላቸዋል።

ከ25 በላይ በተለያዩ የሙያ መስኮች የተሰማሩ ተምሳሌት ሴቶች፣ ሴት አምባሳደሮች፣ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚሰሩ ሴት ኃላፊዎች የተሳተፉበት የ2017 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሜ ሩጫ ውድድር ተካሂዷል።

መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓም
👍8
የአካባቢን ጸጋ ለይቶ፣ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃን መተግበር የሀገርን ብልጽግና የማረጋገጫ አንዱ መንገድ ነው። ይህን ርዕይ ወደ ተግባር እየቀየሩ ከሚገኙ አካባቢዎች የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ አንዱ ነው፡፡

በአካባቢው እየተከናወኑ የሚገኙ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችና የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ይበል የሚያሰኙ ናቸው።

- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
👍4👏1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በብሔራዊ ቤተመንግሥት በተደረገው ሁለተኛው የኢፍጣር ምሽት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ 200 የሚሆኑ ስደተኞች ተስተናግደዋል። ተሳታፊዎችም ብሔራዊ ቤተመንግሥት ጎብኝተዋል።
👏148👍5