ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👎2❤1👍1
ኢትዮጵያ በታሪክም ይሁን አሁናዊ ሁኔታ የባሕር በር ጥያቄዋ ተቀባይነት እንዳለው ያሳያል
****
(ኢ ፕ ድ)
..... በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ኤፍ ኤስ ኤስ በተባለች የጦር መርከብ ላይ ከ1977 እስከ 1983 ዓ.ም የመንግሥት ለውጥ ድረስ ሲያገለግሉ የቆዩት ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል አረጋ ገብረማርያም የባሕር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ደኅንነት የማስጠበቅ ጉዳይ ጭምር ነው ይላሉ።
ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል ለኢብድ በሰጡት ማብራሪያ፤ የባሕር በር ባለቤትነት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት። ብዙ ጊዜ ሲነሳ የምንሰማው የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ነው። ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ብትሆን የደኅንነት ዋስትና ያላት ሀገር እንድትሆንም ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
አንድ ሀገር የትኛውም አይነት የወደብ አማራጭ ቢኖረው ልክ በራሱ እንደሚተዳደር የባሕር በር ወይም ወደብ ያህል ደኅንነቱና ምስጢራዊነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ሊያገኝ አይችልም። የራስ የባሕር በር ካለ የሚወጣውም የሚገባውም ነገር ደኅንነትም ሆነ ምስጢራዊነት ለሌላ ወገን ሊተላለፍ አይችልም።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ እቃዎችም ይሁኑ ወደ ውጭ የሚላኩት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሌሎች ሀገራት ይሁንታንና ፍተሻን የሚያልፉ መሆናቸውን ይናገራሉ።
ይህም ሊጠበቁ የሚገባቸውን ምስጢሮች በማውጣት ሕዝብንና ሀገርን ለአደጋ የሚያጋልጥ ይሆናል። እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት ያላትና የፍላጎት ማደግ ባለባት ሀገር የሚያስከትለው ጉዳት የከፋ ይሆናል። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከ30 ዓመት በፊት እንደነበረችው ሁሉ አስፈላጊውንና ተገቢውን ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ በመጠቀም የባሕር በር ባለቤት እንድትሆን መሥራት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
‹‹የባሕር በር ጥያቄ መነሳት አዲስ የሚሆንባቸው ዜጎች እንዳሉ እያየን ነው›› ያሉት ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል፤ ይህ ሆን ተብሎ ትውልዱ ላይ ሲሠራበት የቆየ የማዘናጊያ አስተሳሰብ እንደሆነ ተናግረዋል።
የአሁኑ ትውልዱ ዓለም አቀፍ ሕጎችን በመጠቀምና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ፣ በሰጥቶ መቀበል መርሕ ኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤት ሊያደርግ የሚችልበት ዕድል........https://press.et/?p=147482
****
(ኢ ፕ ድ)
..... በኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ኤፍ ኤስ ኤስ በተባለች የጦር መርከብ ላይ ከ1977 እስከ 1983 ዓ.ም የመንግሥት ለውጥ ድረስ ሲያገለግሉ የቆዩት ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል አረጋ ገብረማርያም የባሕር በር ጥያቄ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ደኅንነት የማስጠበቅ ጉዳይ ጭምር ነው ይላሉ።
ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል ለኢብድ በሰጡት ማብራሪያ፤ የባሕር በር ባለቤትነት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት። ብዙ ጊዜ ሲነሳ የምንሰማው የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ነው። ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ብትሆን የደኅንነት ዋስትና ያላት ሀገር እንድትሆንም ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
አንድ ሀገር የትኛውም አይነት የወደብ አማራጭ ቢኖረው ልክ በራሱ እንደሚተዳደር የባሕር በር ወይም ወደብ ያህል ደኅንነቱና ምስጢራዊነቱ የተጠበቀ አገልግሎት ሊያገኝ አይችልም። የራስ የባሕር በር ካለ የሚወጣውም የሚገባውም ነገር ደኅንነትም ሆነ ምስጢራዊነት ለሌላ ወገን ሊተላለፍ አይችልም።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ እቃዎችም ይሁኑ ወደ ውጭ የሚላኩት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሌሎች ሀገራት ይሁንታንና ፍተሻን የሚያልፉ መሆናቸውን ይናገራሉ።
ይህም ሊጠበቁ የሚገባቸውን ምስጢሮች በማውጣት ሕዝብንና ሀገርን ለአደጋ የሚያጋልጥ ይሆናል። እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት ያላትና የፍላጎት ማደግ ባለባት ሀገር የሚያስከትለው ጉዳት የከፋ ይሆናል። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከ30 ዓመት በፊት እንደነበረችው ሁሉ አስፈላጊውንና ተገቢውን ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ በመጠቀም የባሕር በር ባለቤት እንድትሆን መሥራት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
‹‹የባሕር በር ጥያቄ መነሳት አዲስ የሚሆንባቸው ዜጎች እንዳሉ እያየን ነው›› ያሉት ፒቲ ኦፊሰር ሳሙኤል፤ ይህ ሆን ተብሎ ትውልዱ ላይ ሲሠራበት የቆየ የማዘናጊያ አስተሳሰብ እንደሆነ ተናግረዋል።
የአሁኑ ትውልዱ ዓለም አቀፍ ሕጎችን በመጠቀምና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ፣ በሰጥቶ መቀበል መርሕ ኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤት ሊያደርግ የሚችልበት ዕድል........https://press.et/?p=147482
👍8❤4
"የጣና ዳር ንግሥቷ፣ ባለዘንባባዋ ሙሽራ፣ የቱሪዝም አስኳሏ ባህር ዳር ስራ ላይ ነች"
- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሰገን ጥሩነህ
***
ፍፁም የሰላም አየር፣ የዓይንና የመንፈስ ማረፊያ ውብ ሥፍራ የታደለችው ባህር ዳር ከመዝናኛ እስከ ግዙፍ የንግድ ስፍራዎቿ በእንቅስቃሴ ተሞልተዋል፤ ሀገሬው ከጧት እስከ ማታ ሥራ ላይ ነው፡፡
የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ከልጅ እስከ አዋቂ በልዩ ልዩ ስፖርቶች ደምቀዋል፤ ከዚሁ ጎን ለጎን ግዙፉ የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ከተማዋን የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል የሚያደርጋት ይሆናል።
ሀገሬው በሥራ የደከመ አካሉንና አዕምሮውን ለማደስ ስፖርት ሲሠራ፣ በመዝናኛ ማዕከላት ሲዝናና፣ በዘንባባዋ ጥላ ስር አረፍ ሲል፣ በጣና ዳርቻ ሰብሰብ ብሎ ሲጫወት፣ በምሽት በእግር ሲንቀሳቀስ ማየት ልብን ሀሴት ያወርሳል።
ወቅቱ የዐቢይና የረመዳን አፅዋማት የሚፆሙበት ነው። የከተማዋ ምዕመን ሰርክ ወደ መስጂድና ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሲተምም ማየት መንፈሳዊ ኩራትን ይፈጥራል።
ውቧ ከተማ ልማቷን እያፋጠነች፣ ፍፁም የሰላም ድባብ፣ እረፍት አልባ የልማት ሥራ፣ ሞቅ ያለ የመዝናኛና የንግድ እንቅስቃሴ የሚታይባት ሆናለች።
ባየነው የሠላም ንፋስ የልማትና የሥራ ጥድፊያ እንዲሁም የቱሪዝም መነቃቃት ተደሰተናል። የተጀመሩ ስራዎችን ዓይናችንን ሳንነቅል በተገቢው ጥራት እንዲጠናቀቁ ክትትላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡
መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም
- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሰገን ጥሩነህ
***
ፍፁም የሰላም አየር፣ የዓይንና የመንፈስ ማረፊያ ውብ ሥፍራ የታደለችው ባህር ዳር ከመዝናኛ እስከ ግዙፍ የንግድ ስፍራዎቿ በእንቅስቃሴ ተሞልተዋል፤ ሀገሬው ከጧት እስከ ማታ ሥራ ላይ ነው፡፡
የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች ከልጅ እስከ አዋቂ በልዩ ልዩ ስፖርቶች ደምቀዋል፤ ከዚሁ ጎን ለጎን ግዙፉ የባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ከተማዋን የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል የሚያደርጋት ይሆናል።
ሀገሬው በሥራ የደከመ አካሉንና አዕምሮውን ለማደስ ስፖርት ሲሠራ፣ በመዝናኛ ማዕከላት ሲዝናና፣ በዘንባባዋ ጥላ ስር አረፍ ሲል፣ በጣና ዳርቻ ሰብሰብ ብሎ ሲጫወት፣ በምሽት በእግር ሲንቀሳቀስ ማየት ልብን ሀሴት ያወርሳል።
ወቅቱ የዐቢይና የረመዳን አፅዋማት የሚፆሙበት ነው። የከተማዋ ምዕመን ሰርክ ወደ መስጂድና ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሲተምም ማየት መንፈሳዊ ኩራትን ይፈጥራል።
ውቧ ከተማ ልማቷን እያፋጠነች፣ ፍፁም የሰላም ድባብ፣ እረፍት አልባ የልማት ሥራ፣ ሞቅ ያለ የመዝናኛና የንግድ እንቅስቃሴ የሚታይባት ሆናለች።
ባየነው የሠላም ንፋስ የልማትና የሥራ ጥድፊያ እንዲሁም የቱሪዝም መነቃቃት ተደሰተናል። የተጀመሩ ስራዎችን ዓይናችንን ሳንነቅል በተገቢው ጥራት እንዲጠናቀቁ ክትትላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡
መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም
👍7👏1
የባሕር በር ጥያቄ የመጪውን ትውልድ ሕልውና የሚወስን ነው
****
(ኢ ፕ ድ)
የባሕር በር ጉዳይ የመጪውን ትውልድ የመኖር እና ያለመኖር ሁኔታ የሚወስን ስለሆነ ከወዲሁ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ሲሉ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሃሳቡ ተስፋ ገለጹ፡፡
መምህር ሃሳቡ ተስፋ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በሚያስተዳድራት በራሷ መንግሥት ድጋፍ አድራጊነት የነበራትን የባሕር በር እንድታጣ መደረጓ ሁሌም የሚያስቆጭ ታሪካዊ ስህተት ነው፡፡ የባሕር በር ከሉዓላዊ ግዛትነቱም በላይ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ጥቅሙ የሕልውና ጉዳይ ያደርገዋል፡፡
አንድ ሀገር የባሕር በር አለው ማለት ሌሎች የባሕር በር ካላቸው የዓለም ሀገራት ጋር ይዋሰናል ማለት ነው ያሉት መምህሩ፤ ይህ ደግሞ ያለማንም ጣልቃ ገብነት የንግድ ልውውጥ እና ማኅበራዊ ትስስር ለመፍጠር ያስችላል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
እንደ መምህር ሃሳቡ ገለጻ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፤ በዚያው ልክ ፍላጎቱና የንግድ እንቅስቃሴውም አድጓል፤ ዓለም አቀፍ ግንኙነቱና ኢኮኖሚያዊ ትስስሩም ጨምሯል፡፡
እያደገ ከሚሄደው የሕዝብ ቁጥርና ፍላጎት አንጻር፤ የባሕር በር በተለይም የመጪውን ዘመን ትውልድ የመኖርና ያለመኖር ሁኔታ የሚወስን በመሆኑ ከወዲሁ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባዋል።
****
(ኢ ፕ ድ)
የባሕር በር ጉዳይ የመጪውን ትውልድ የመኖር እና ያለመኖር ሁኔታ የሚወስን ስለሆነ ከወዲሁ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባል ሲሉ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ሃሳቡ ተስፋ ገለጹ፡፡
መምህር ሃሳቡ ተስፋ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በሚያስተዳድራት በራሷ መንግሥት ድጋፍ አድራጊነት የነበራትን የባሕር በር እንድታጣ መደረጓ ሁሌም የሚያስቆጭ ታሪካዊ ስህተት ነው፡፡ የባሕር በር ከሉዓላዊ ግዛትነቱም በላይ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ጥቅሙ የሕልውና ጉዳይ ያደርገዋል፡፡
አንድ ሀገር የባሕር በር አለው ማለት ሌሎች የባሕር በር ካላቸው የዓለም ሀገራት ጋር ይዋሰናል ማለት ነው ያሉት መምህሩ፤ ይህ ደግሞ ያለማንም ጣልቃ ገብነት የንግድ ልውውጥ እና ማኅበራዊ ትስስር ለመፍጠር ያስችላል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
እንደ መምህር ሃሳቡ ገለጻ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፤ በዚያው ልክ ፍላጎቱና የንግድ እንቅስቃሴውም አድጓል፤ ዓለም አቀፍ ግንኙነቱና ኢኮኖሚያዊ ትስስሩም ጨምሯል፡፡
እያደገ ከሚሄደው የሕዝብ ቁጥርና ፍላጎት አንጻር፤ የባሕር በር በተለይም የመጪውን ዘመን ትውልድ የመኖርና ያለመኖር ሁኔታ የሚወስን በመሆኑ ከወዲሁ መፍትሔ ሊበጅለት ይገባዋል።
👍13👏2😢2
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኢትሃድ አየር መንገድ ስትራቴጂክ የቢዝነስ ስምምነት ተፈራረሙ
👉 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሀምሌ 8 ቀን 2017 ጀምሮ ከአዲስ አበባ አቡዳቢ በረራ ይጀምራል፣
👉 ኢታሃድ አየር መንገድ ከመስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከአቡዳቢ አዲስ አበባ ቀጥታ በራራ ይጀምራል፣
***
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድና ኢትሃድ አየር መንገድ የአየር ትራንስፖርት ትስስርን ለማጠናከርና በትብብር ለመስራት የሚስችላቸውን ስትራቴጂክ የቢዝነስ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ በኢትሀድ ኤርዌይስ በኩል የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንቶላዶ ኔቬስ ፈርመዋል።
ስምምነቱ ለደንበኞች የተቀላጠፈ የበረራ አማራጭ ለማቅረብ በሁለቱ አየር መንገዶች መካከል “የኮድ ሼር” አገልግሎት፣ በአዲስ አበባና አቡዳቢ መካከል የበረራ አገልግሎት መጀመርን ያካተተ ነው ተብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሀምሌ 8 ቀን 2017 ጀምሮ ከአዲስ አበባ አቡዳቢ በረራ ይጀምራል። ኢታሃድ አየር መንገድ ከመስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከአቡዳቢ አዲስ አበባ ቀጥታ የበራራ አገልግሎት ይጀምራል ተብሏል።
በስምምነት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ሌ/ጀነራል ይልማ መርዳሳ፣ የኢቲሃድ ኤርዌይስ ቦርድ ሰብሳቢ ሞሀመድ አሊን፣ የሁለቱ አየር መንገዶች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች መሳተፋቸውን የአየር መንገዱ መረጃ ያመለክታል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👉 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሀምሌ 8 ቀን 2017 ጀምሮ ከአዲስ አበባ አቡዳቢ በረራ ይጀምራል፣
👉 ኢታሃድ አየር መንገድ ከመስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከአቡዳቢ አዲስ አበባ ቀጥታ በራራ ይጀምራል፣
***
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድና ኢትሃድ አየር መንገድ የአየር ትራንስፖርት ትስስርን ለማጠናከርና በትብብር ለመስራት የሚስችላቸውን ስትራቴጂክ የቢዝነስ ስምምነት ዛሬ በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ በኢትሀድ ኤርዌይስ በኩል የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንቶላዶ ኔቬስ ፈርመዋል።
ስምምነቱ ለደንበኞች የተቀላጠፈ የበረራ አማራጭ ለማቅረብ በሁለቱ አየር መንገዶች መካከል “የኮድ ሼር” አገልግሎት፣ በአዲስ አበባና አቡዳቢ መካከል የበረራ አገልግሎት መጀመርን ያካተተ ነው ተብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሀምሌ 8 ቀን 2017 ጀምሮ ከአዲስ አበባ አቡዳቢ በረራ ይጀምራል። ኢታሃድ አየር መንገድ ከመስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከአቡዳቢ አዲስ አበባ ቀጥታ የበራራ አገልግሎት ይጀምራል ተብሏል።
በስምምነት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሰብሳቢ ሌ/ጀነራል ይልማ መርዳሳ፣ የኢቲሃድ ኤርዌይስ ቦርድ ሰብሳቢ ሞሀመድ አሊን፣ የሁለቱ አየር መንገዶች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች መሳተፋቸውን የአየር መንገዱ መረጃ ያመለክታል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
👍8❤2👏1
የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የተዳራደሪ ቡድን ስብሰባ በጄኔቫ መካሄድ ጀመረ
****
(ኢ ፕ ድ)
5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የስራ ቡድን አባላት ስብሰባ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄድ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ ቡድን መሪ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ኢትዮጵያ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ዝግጁ መሆኗን በመድረኩ አስረድቻለሁ ብለዋል፡፡
አባል ሀገራት የሁለትዮሽ የንግድ ድርድራቸውን ከወዲሁ እንዲያጠናቅቁ በመድረኩ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸው በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ከ19 ሀገራት በላይ የድጋፍ መልእክት በማስተላለፍ ኢትዮጵያን ማበረታታቸውን ገልፀዋል፡፡
መድረኩ በጥያቄና መልስ መርሐ-ግብር እስከምሽት እንደሚቀጥልም አመላክተዋል፡፡
መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የስራ ቡድን አባላት ስብሰባ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄድ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ ቡድን መሪ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ኢትዮጵያ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ዝግጁ መሆኗን በመድረኩ አስረድቻለሁ ብለዋል፡፡
አባል ሀገራት የሁለትዮሽ የንግድ ድርድራቸውን ከወዲሁ እንዲያጠናቅቁ በመድረኩ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸው በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ከ19 ሀገራት በላይ የድጋፍ መልእክት በማስተላለፍ ኢትዮጵያን ማበረታታቸውን ገልፀዋል፡፡
መድረኩ በጥያቄና መልስ መርሐ-ግብር እስከምሽት እንደሚቀጥልም አመላክተዋል፡፡
መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም
👍6👏1
ሀገር በቀል እውቀቶችን ከፋሽን ኢንዱስትሪው ጋር አስተሳስሮ የዜጎችን ተጠቃሚነትን ማላቅ ያሰፈልጋል
****
(ኢ ፕ ድ)
የማፊ ፋሽን ዲዛይን መሥራች ወ/ሮ ማህሌት አፈወርቅ ጋር በክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ ላይ በቅንጅት መሥራት በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
ሚኒስትሯ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት እያደገ የመጣው የፋሽን ኢንዱስትሪ ያለውን እምቅ አቅም አሟጦ ለመጠቀም የግሉ ዘርፍ ሚና የማይተካ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገር በቀል እውቀቶችን ከፋሽን ኢንዱስትሪው ጋር አሰናስሎ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማላቅ ሥነ-ምኅመዳሩን ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል ብለዋል።
የማፊ ፋሽን ዲዛይን መሥራች ወ/ሮ ማህሌት አፈወርቅ በመስኩ በትብብር በመሥራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማላቅ ላሳዩት ቁርጠንነትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የማፊ ፋሽን ዲዛይን መሥራች ወ/ሮ ማህሌት አፈወርቅ ጋር በክህሎት ልማትና ሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ ላይ በቅንጅት መሥራት በሚቻልበት ሁኔታዎች ላይ መወያየታቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
ሚኒስትሯ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት እያደገ የመጣው የፋሽን ኢንዱስትሪ ያለውን እምቅ አቅም አሟጦ ለመጠቀም የግሉ ዘርፍ ሚና የማይተካ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገር በቀል እውቀቶችን ከፋሽን ኢንዱስትሪው ጋር አሰናስሎ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማላቅ ሥነ-ምኅመዳሩን ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል ብለዋል።
የማፊ ፋሽን ዲዛይን መሥራች ወ/ሮ ማህሌት አፈወርቅ በመስኩ በትብብር በመሥራት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማላቅ ላሳዩት ቁርጠንነትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓም
👍11❤2👏2