Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
"በዓላቶቻችን ትናንትን ያኖሩን፤ ዛሬን ያስተሳሰሩንና ነገ ላይ የሚያደርሱን ዕሴቶች ናቸው"
– ኑረዲን ቃሲም (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)

ዒድ አልፈጥርንና መሰል በዓላቶቻችን ትናንትን ያኖሩን፤ ዛሬን ያስተሳሰሩንና ነገ ላይ የሚያደርሱን ዕሴቶች መሆናቸውን ዓለም አቀፍ የቁርዓን ዳኛ ኑረዲን ቃሲም (ዶ/ር) አስታወቁ።

ኑረዲን (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደተናሩት፤ ዒድ አልፈጥር በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ዘንድ ትልቅ የበረከትና የተቸገሩ ሳይቀሩ ተደስተው እንዲውሉ የሚደረግበት ልዩ ጊዜ ነው። በዚህም ሙስሊሙ ይህንን የእምነቱን አስተምሮ ተግባራዊ ሲያደርግ በዓሉን በተለያየ አግባብ እንዲመለከተውና ነገውን እንዲሠራ ያስችለዋል።

በመረዳዳት ውስጥ፤ በአብሮነት ውስጥ ያለውን ታላቅነት እንዲረዳው ያግዘዋል ብለዋል።

በዓላቶቻችን እምነታችንን በተግባር እንድንኖረው የሚያስችሉን ናቸውም የሚሉት ኑረዲን (ዶ/ር)፤ በዒድ ጊዜ የሚደረገው ሰዎችን የማገዝ ተግባር አንዱ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በዓሉ አንድም ሰው ወደ ልመና እንዳይወጣ በማገዝ አብሮነታችንን ማሳየት እንደሚገባ አመልክተው፤ ኢትዮጵያውያን ለበዓላት ልዩ ትርጉም የሚሰጡበት ዋነኛ ምክንያት በበዓላቶቻችን ውስጥ ትናንትን ማሰብ፤ ዛሬን መተሳሰርና ነገን አሻግሮ ማየት ስላለ መሆኑን ገልጸዋል።

በዓላቶቻችን ትናንትን በፍቅርና በደስታ አቆይተው ዛሬን አሳይተውናል። ዛሬን አስተሳስረው ደግሞ ነጋችን መልካም እንደሚሆን ይነግሩናል። ሁሌ ቅንና ለሰዎች የምንጨነቅም እንድንሆን መልካም ሥነምግባርን ያላብሱናል።
👏5👍3
1ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል አከባበር በሶማሌ ክልል #ጅግጅጋ ከተማ‼️

#ዒድአልፈጥር
👍1
ጎንደር ከተማ አባቶቻችን ያለልዩነት የሰሯት ከተማ ናት"- ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው
*****
(ኢ ፕ ድ)

1ሺህ 446ኛ የዒድ አልፈጥር በዓል በጎንደር ከተማ አጼ ፋሲለደስ ስቴዲየም በድምቀት ተከብሯል።

በመርሐ ግብሩ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው እንደገለፁት፣በጎንደር ታሪክ የስልምና ታሪክ በአፄ ፋሲለደስ የንግስና ዘመን ትልቅ ቦታ ነበረው። በጎንደር ወርቃማ ዘመን ነጋድረስ የከተማዋን የንግድ ስርዓት በማሳደግ ድርሻው ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሰዋል።

ዛሬም እኛ ፖለቲከኞች ሰላምን እንዘምራለን፤ የሀይማኖት አባቶች ለሀገራቱ ሰላም ሊያግዙን ይገባል ብለዋል።

ጎንደርን አባቶቻችን ያለ ልዩነት የሰሯት ከተማ ናት ያሉት ከንቲባው የሙስሊሙ ማህበረሰብ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን በማገዝ እያደረጉት ላለው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

#ዒድሙባረክ #ዒድአልፈጥር #ኢድ #ጎንደር

መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓም
👍3👏1
ከንቲባ አዳነች የዒድ አል ፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ
****
(ኢ ፕ ድ)

1446ኛውን የኢድ አል-ፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ በተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላቶቻችን ከአቅመ ደካሞችና ከሀገር ባለውለታዎች ጋር ማዕድ ተጋርተናል። በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ"

- የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

#ኢድሙባረክ #ዒድአልፈጥር #ኢድ
4👍3👎1👏1
“በረመዳን ወር የምንተገብራቸውን መልካም ዕሴቶች የሕይወታችን ልምዶች ልናደርጋቸው ይገባል”
-ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ
*******
(ኢ ፕ ድ)

በረመዳን ወር የምንተገብራቸው የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና መሰል መልካም እሴቶችን ሁልጊዜም የሕይወታችን ልምዶች ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ ገለጹ፡፡

ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ረመዳን መሠረታዊ እሴት በሰዎች ልብ ውስጥ የፈጣሪ ፍራቻ፣ መተዛዘን፣ ስለሌሎች መኖርን፣ መደጋገፍንና ማሰብን የሕይወታችን አካል እንድናደርግ ለ11 ወራት የሚሆን ስንቅ የሚይዝበት ወር ነው።

በመሆኑም በረመዳን ወር የምንተገብራቸውን የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና ለሌሎች መልካም እሴቶች ሁልጊዜም የሕይወታችን ልምዶች አካል ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል።

ረመዳን አንዱ ስለሌላው የሚኖርበት ስለሆነ መልካም ተግባራት በስፋት የሚከናወኑበት ወር መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህ ተግባር ደግሞ ሰዎች ዘወትር ሊኖራቸው የሚገባ ባሕሪ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።

እኛ ዋጋ ለማግኘት ብለን በፈቃዳችን ስንፆም ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻችንን ማሰብና አለኝታነታችንን ማሳየት ይገባናል ብለዋል።
👍114👎1👏1
👉 ኢትዮጵያ ታሪካዊ የቀይ ባሕር ተዋሳኝነቷን መልሳ ማግኘት አለባት፣

👉 ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን ልታጣ የቻለችበት ውጤት ራሱን የቻለ የኋላ ታሪክ አለው፣

👉 ቀይ ባሕርን እንድናጣ ያደረገው በወቅቱ የተመድ ውስጥ ይሠራ የነበረ አንድ ግብጻዊ ዲፕሎማት ነው፣

👉 የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ገዢ ፓርቲዎች ውሳኔዎችን አሳለፉ እንጂ በሁለቱም ወገን ያሉ ሕዝቦች አልተወያዩበትም፣

👉 በሰላማዊ መንገድ እነሱም እኛም ተጠቃሚ መሆን የምንችልበትን መንገድ መፍጠር አለብን፣

👉 የዓለም ሀገራት ኢትዮጵያ በአካባቢው መኖሯ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ያደርጋል የሚል አመኔታ አድሮባቸዋል፣

👉 ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር ያላትን ግንኙነት በቱርክ አደራዳሪነት መልሳ ማስተካከል ችላለች

👉 ኢትዮጵያ የዓባይን ግድብ በማጠናቀቋ ታላቅ ድል ነው

👉 በራሷ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክትን ማሳካት የምትችል ታላቅ ሀገር መሆኗን ለዓለም አሳይታለች፣

👉 ግድቡን ለመገንባት ያሳየነውን ሕብረትና አንድነት ከድህነት መውጣት እንደምንችል ያየንበት ፕሮጀክት ነው፣

👉 አሁን ካለንበት ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር እንደ ሕዝብ ሰላም መረጋጋት አንድነትን ማምጣት ይጠበቅብናል፣

ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=148451
👍54