Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
Photo
👉 ባለፉት ስምንት ወራት የኢትዮጵያ የውጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ደርሷል፣

👉 የጥራት መንደሩ በአመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን ጥራት ያረጋግጣል፣

👉 በኢትዮጵያ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ተጀምሯል፣
*****
(ኢ ፕ ድ)

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ በ2010 ዓም የኢትዮጵያ የውጪ ንግድ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የነበረ መሆኑን ጠቅሰው በስምንት ወራት የውጪ ንግድ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ደርሷል።

በ2017 በጀት ዓመት መጨረሻ ከ6 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግስት የንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪና ተገማች ለማድረግ በመስራት ላይ መሆኑን መሆኑን ጠቅሰው ንግዱ ቀጠናውን የሚያስተሳስር የንግድ ልውውጥ ለማድረግ መሆኑንም ገልጸዋል።

በሀገሪቱ የንግድ ፖሊሲ እንዳልነበረ በመግለጽ ከብዙ ጥረትና ድካም በኋላ ረቂቅ የንግድ ፖሊሲ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

ባለፉት ስምንት ወራት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የንግድ ማህበረሰብ አዲስ የንግድ ፈቃድ አውጥቷል። ከአንድ ሺህ 300 በላይ የቅዳሜና እሁድ ገብያዎችን በማደራጀት ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በንግዱ ዘርፉ ላይ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ ጠቅሰው የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የሚያስችል ተጨባጭ ተስፋ ታይቶበታል ያሉት ሚኒስትሩ የንግድ ፖሊሲው ሀገሪቱ ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።

ሀገሪቱ ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የጥራት መንደርን ከ8 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መገንባቱን ጠቅሰው በዓመት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን ቶን በላይ ወጪና ገቢ ምርቶችን የጥራት የማረጋገጥ ሥራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በማርቆስ በላይ

መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
👍51👏1
የኢትዮጵያ አየር መንገዱ ወደ ማካው ከተማ የመጀመሪያ የካርጎ በረራውን አደረገ
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቻይናዋ ማካው ከተማ የመጀመሪያ የካርጎ በረራውን በዛሬው ዕለት አድርጓል።

አየር መንገዱ በማካው ባስጀመረው የካርጎ አገልግሎት ስነ ስርዓት ላይ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው እንደገለፁት የአገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ የካርጎ ትስስሩን ለማስፋትና የዓለም ንግድን ለማሳለጥ ያለው ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አየር መንገዱ በቻይና የካርጎ መዳረሻውን ወደ 10 ከፍ ማድረጉን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
👍9👏1
ከለውጡ ወዲህ በቱሪዝሙ ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶች‼️

👉 225 ኢንቨስትመንቶች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል

👉 472 የአሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች ዘርፉን ተቀላቅለዋል፣

👉 ደረጃቸውን የጠበቁ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ብዛት ቀድሞ ከነበረበት ወደ አንድ ሺህ 573 አድጓል

👉 ከአራት ሚሊዮን 169 ሺ 646 የውጭ ቱሪስቶች ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል

👉 ከውጭ ጎብኚ15 ነጥብ 64 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፣

👉 የሀገር ውስጥ ቱሪዝም በፊት ከነበረበት 18 ሚሊዮን ወደ 58 ነጥብ 2 ሚሊዮን ጎብኚዎች አድጓል፣

የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን ለማነቃቀትና የጉብኝት ባህልን ለማጠናከር በተሰሩ የማስተዋወቅና ስርፀት ስራዎች ከለውጡ በፊት ከነበረበት 18 ሚሊዮን በአሁኑ ወቅት ወደ 58 ነጥብ 2 ሚሊዮን ማደጉን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አመላክቷል።

በመስከረም ሰይፉ

መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓም
👍10👎1
ወላጆች ለትምህርት ቤቶች ዕድሳት ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ በዓይነትና በገንዘብ ድጋፍ አደረጉ

👉 ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ 30 ሺህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተሰርተዋል

👉 ባለፉት ሦስት ዓመታት የተመዘገበው አነስተኛ ውጤት እንደ ሀገር የደረሰንበትን ውድቅት አሳይቶናል፣
*******
(ኢ ፕ ድ)

ወላጆች የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል "ትምህርት ለትውልድ" በሚል ሀሳብ ትምህርት ቤቶችን ለማሻሻል በተደረገ ንቅናቄ 40 ቢሊዮን ብር በዓይነትና በገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ።

ወላጆች በትምህርት ውጤት መስተካከል ላይ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በዚህም 7 ሺህ 500 አዲስ ትምህርት ቤቶች፤ ባለፉት ሁለት አመታት ብቻ 30 ሺህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተሰርተዋል፡፡ ነባር 22 ሺህ ትምህርት ቤቶች ተጠግነዋል፡፡ ቤተሰብ ገንዘብ ከማዋጣት አልፎ የልጆቹን የትምህርት ውሎ መከታተል ሲጀምር የተማሪዎች ውጤት የበለጠ እየተሻሻለ ይሄዳል ብለዋል፡፡

ባለፉት ሦስት ዓመታት የተመዘገበው አነስተኛ ውጤት እንደ ሀገር የደረሰንበትን ውድቅት አሳይቶናል፡፡ ውጤቱን የማስተካከል ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፤ ተማሪዎች ማለፍ የሚቻለው በስራ መሆኑን ሲገነዘቡ ይሰተካከላል።

ትምህርት በአቋራጭና በስርቆት አልፋለው ብሎ በሚያስብ ተማሪና ማህበረሰብ ውስጥ አስተማሪዎችን ብታስተካክል የትም አትደርስም ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ እውነታ ከዚህ የተለየ አለመሆኑን የገለፁት ሚኒስትሩ ባለፈው ዓመት 5 ነጥብ 2 በመቶ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን የተወሰነ ለውጥ መጥቷል፡፡

ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ተጨማሪ ሰዓት የድጋፍ ትምህርት መስጠት በመጀመራቸው የተወሰነ የውጤት መሻሻል ታይቷል፡፡ በስርዓት ማስተማር በመጀመራቸው ያለፈው አመት ውጤት መሻሻል ችሏል ብለዋል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ውጤት ዝቅተኛ የመሆን ምክንያቶችን አስመልክቶ ያጠናውን ጥናት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ማቅረቡ ይታወሳል።

በሞገስ ጸጋዬ

መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓም
👍7👏1
ፌደራል ፖሊስ ለዓባይ ግድብ ከ254 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ
***
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለዓባይ ግድብ ግንባታ ከ254 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አሰታወቀ።

ፌደራል ፖሊስ ቃል-አቀባይ ረዳት ኮሚሽነር መጎስ ቸኮል እንደገለፁት፣ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር በቦንድ ግዥ ከ254 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ አሰባስበው ገቢ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ፌደራል ፖሊስ በዘመናዊ ጀልባ የታገዘ የተጠናከረ ጥበቃ ለማድረግ ፖስታል ጋርድ ፖሊስ አደራጅቶ ወደ ተግባር ለመግባት ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓም
👍84😁2
ኢትዮጵያና ኡጋንዳ በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት አደረጉ
******
‎(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያና ኡጋንዳ በንግድ፣ በእንስሳትና አሳ ሀብት፣ በሲቪል አቪዬሽን፣ በአየር ትራንስፖርት፣ በኢንዱስትሪ፣ በኢነርጂ፣ በውሃ ሀብት ልማትና አስተዳደርና በሌሎች ስምንት ዘርፎች በጋራ ለመስራት ተስማሙ።

4ኛው የኢትዮ-ዩጋንዳ የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ ከተማ ተካሄደ።

‎በስምምነቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ስብሰባው በሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሙያዎች ደረጃ ሲካሄድ ቆይቷል። የጋራ ጥቅምና ፍላጎት የሚያንጸባርቅ፤ በቀጣናው ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በሚያስችሉ በርካታ ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉን ተናግረዋል።

‎በሁለቱ ሀገራት መካከል ከዚህ ቀደም የተደረጉ ስምምነቶች ያሉበት ደረጃ መገምገሙን ጠቁመው፤ በፖለቲካ፣ በፀጥታ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ አቪዬሽንና በሌሎችም ዘርፎች ከስምምነት መደረሱን ገልጸዋል።

‎ስምምነቱ በቀጣይም በሁለቱን ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

‎የኡጋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጀነራል ኦዶንጎ ጄጄ አቡበከር በበኩላቸው፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከርና ስምምነቶችን ለመፈፀም ኡጋንዳ ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።

የስምምነቱን ተግባራዊነት እንደሚከታተሉ ጠቅሰው ስብሰባ እንዲሳካ የኢትዮጵያ መንግስት ላደረገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርቧል።

5ኛው የኢትዮ-ዩጋንዳ የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ በኡጋንዳ ካምፓላ ከተማ እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

‎በቃልኪዳን አሳዬ

መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓም
👍1