ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
❤3👍1
"ኢትዮጵያ ወደ ሞንጎሊያና ቻይና የተቀቀለ ሥጋ መላክ መጀመሯ ትልቅ ስኬት ነው" – አምባሳደር ድሪባ ኩማ
*****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ወደ ቻይና እና ሞንጎሊያ ጥራቱና ደኅንነቱ የተረጋገጠ የተቀቀለ ሥጋ መላክ መጀመሯን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ አስታወቁ፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት ከሚሌ ኳራንታይን 400 ሺህ የቁም እንስሳት ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ከ28 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል።
አምባሳደር ድሪባ ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ባለሥልጣኑ በጀት ዓመቱ የስድስት ወር ግምገማ ከያዛቸው እቅዶች 96 በመቶውን ማሳካት ችሏል። ከእነዚህ ሥራዎችም ኢትዮጵያ ጥራቱና ደኅንነቱ የተጠበቀ የተቀቀለ ሥጋ ወደ ቻይና መላክ መጀመሯ ይጠቀሳል። ወደ ቻይና ብቻ ሳይሆን ወደ ሞንጎሊያም መላክ ጀምራለች ብለዋል፡፡
ትልቁ ስኬት ነው ብለን የምንለው የሥጋ ምርታችን ወደ ቻይና እንዲገባ ማድረግ ተችሏል። ከዚሁ ከሥጋ ምርት ጋር በተያያዘ የቻይና ኤክስፐርቶች ያለውን ሁኔታ አይተው ማስተካከል የሚገባንን ምክረ ሃሳብ ሰጥተውናል ብለዋል፡፡
“ቻይና በምትፈልገው የሥጋ ንግድ ሥርዓት መሠረት በመቃኘታችን ቻይናውያን ተቀብለው ውል መፈራረም ችለናል፤ በመሆኑም በአሁኑ ጊዜ ሥጋ ወደ ቻይና መግባት ጀምሯል”....https://press.et/?p=148915
*****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ወደ ቻይና እና ሞንጎሊያ ጥራቱና ደኅንነቱ የተረጋገጠ የተቀቀለ ሥጋ መላክ መጀመሯን የኢትዮጵያ ግብርና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ አስታወቁ፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት ከሚሌ ኳራንታይን 400 ሺህ የቁም እንስሳት ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ከ28 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል።
አምባሳደር ድሪባ ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ባለሥልጣኑ በጀት ዓመቱ የስድስት ወር ግምገማ ከያዛቸው እቅዶች 96 በመቶውን ማሳካት ችሏል። ከእነዚህ ሥራዎችም ኢትዮጵያ ጥራቱና ደኅንነቱ የተጠበቀ የተቀቀለ ሥጋ ወደ ቻይና መላክ መጀመሯ ይጠቀሳል። ወደ ቻይና ብቻ ሳይሆን ወደ ሞንጎሊያም መላክ ጀምራለች ብለዋል፡፡
ትልቁ ስኬት ነው ብለን የምንለው የሥጋ ምርታችን ወደ ቻይና እንዲገባ ማድረግ ተችሏል። ከዚሁ ከሥጋ ምርት ጋር በተያያዘ የቻይና ኤክስፐርቶች ያለውን ሁኔታ አይተው ማስተካከል የሚገባንን ምክረ ሃሳብ ሰጥተውናል ብለዋል፡፡
“ቻይና በምትፈልገው የሥጋ ንግድ ሥርዓት መሠረት በመቃኘታችን ቻይናውያን ተቀብለው ውል መፈራረም ችለናል፤ በመሆኑም በአሁኑ ጊዜ ሥጋ ወደ ቻይና መግባት ጀምሯል”....https://press.et/?p=148915
👍10👏1😁1
ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ለሹዋሊድ ባህላዊ በዓል የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት አሰተላለፉ
****
(ኢ ፕ ድ)
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ለሹዋሊድ ባህላዊ በዓል የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት አሰተላፉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ድህረገፃቸው ላይ ባሰፈሩት የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት የሹዋሊድ በዓል የሀረሪ ህዝብ ባህላዊ በዓልን በ2016 ዓ.ም ሀገራችን ኢትዮዽያ በዩኔስኮ የአለም ቅርስነት አስመዝግባዋለች ብለዋል።
ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የሹዋሊድ በአል የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማጎልበት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችል መልኩ እየተከበረ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ሹዋሊድ የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት በኩልም ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው እና በበዩኔስኮ የአለም ቅርስነት የተመዘገበ አንዱ የለውጡ ፍሬአችን ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልፀዋል።
መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ለሹዋሊድ ባህላዊ በዓል የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት አሰተላፉ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ድህረገፃቸው ላይ ባሰፈሩት የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት የሹዋሊድ በዓል የሀረሪ ህዝብ ባህላዊ በዓልን በ2016 ዓ.ም ሀገራችን ኢትዮዽያ በዩኔስኮ የአለም ቅርስነት አስመዝግባዋለች ብለዋል።
ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የሹዋሊድ በአል የህዝብ ለህዝብ ትስስርን ለማጎልበት እና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችል መልኩ እየተከበረ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ሹዋሊድ የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት በኩልም ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው እና በበዩኔስኮ የአለም ቅርስነት የተመዘገበ አንዱ የለውጡ ፍሬአችን ነው ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልፀዋል።
መጋቢት 27 ቀን 2017 ዓም
❤2
በሲዳማ ክልል የቱሪስት መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ሁለት ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኘ
******
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 በበጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የቱሪስት መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ መደረጉን የሲዳማ ክልል ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አበበ ማሪሞ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሁለት ሚሊዮን 400 ሺህ ቱሪስቶች በክልሉ የተለያዩ የቱሪስት መደረሻዎች ጎብኝተዋል።
ከጎበኙት ቱሪስቶች ሁለት ሚሊዮን 300 ሺህ የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ሲሆኑ፤ አንድ መቶ ሺህ ያህሉ የውጭ ቱሪስቶች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ከዚህም ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ ተደርጓል ብለዋል።
አቶ አበበ እንደተናገሩት፤ እንደ ሀገር ሆነ፤ እንደ ሲዳማ ክልልም በደረሰኝ ገንዘብ የምንቀበልበት የቱሪስት መዳረሻ ስለሌለ፤ በዘርፉ ከሚገኘው አጠቃላይ ገቢ 99 በመቶ የሚሆነው ለንግድ ተቋማት ገቢ የሆነ ነው።
የቱሪዝም ዘርፍ ገቢ በሁለት መንገድ ገቢ ይደረጋል። አንደኛው የንግድ ተቋማት ማለትም ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች፤ ትራንስፖርት እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚገኙት ገቢ መሆኑን ገልጸዋል።https://press.et/?p=148985
******
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 በበጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የቱሪስት መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ መደረጉን የሲዳማ ክልል ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አበበ ማሪሞ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሁለት ሚሊዮን 400 ሺህ ቱሪስቶች በክልሉ የተለያዩ የቱሪስት መደረሻዎች ጎብኝተዋል።
ከጎበኙት ቱሪስቶች ሁለት ሚሊዮን 300 ሺህ የሚሆኑት የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ሲሆኑ፤ አንድ መቶ ሺህ ያህሉ የውጭ ቱሪስቶች መሆናቸውን ጠቁመው፤ ከዚህም ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ ተደርጓል ብለዋል።
አቶ አበበ እንደተናገሩት፤ እንደ ሀገር ሆነ፤ እንደ ሲዳማ ክልልም በደረሰኝ ገንዘብ የምንቀበልበት የቱሪስት መዳረሻ ስለሌለ፤ በዘርፉ ከሚገኘው አጠቃላይ ገቢ 99 በመቶ የሚሆነው ለንግድ ተቋማት ገቢ የሆነ ነው።
የቱሪዝም ዘርፍ ገቢ በሁለት መንገድ ገቢ ይደረጋል። አንደኛው የንግድ ተቋማት ማለትም ሆቴሎች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች፤ ትራንስፖርት እና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚገኙት ገቢ መሆኑን ገልጸዋል።https://press.et/?p=148985
👍18😁2
የኦሮሚያ ክልል አንድ ሺህ 402 የግብርና ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች አስረከበ
****
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አንድ ሺህ 402 የግብርና ትራክተሮችን ከነመለዋወጫው ለአርሶ አደሮች፣ ለህብረት ስራ ማህበራት እና ዩኒየኖች በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ አስረክቧል።
ርክክቡ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሰራ ኃላፊዎች በተገኙበት መከናወኑን ከፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻና ጠቅላላ ንግድ ሀላፊነቱ የተወሰነ ድርጅት በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ ናቸው።
የክልሉ መንግስት ምርትና ምርታማነትን ለማሳድግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡ ትራክተሮቹ የክልሉ መንግስት የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት ለያዘው ውጥን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አንድ ሺህ 402 የግብርና ትራክተሮችን ከነመለዋወጫው ለአርሶ አደሮች፣ ለህብረት ስራ ማህበራት እና ዩኒየኖች በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ አስረክቧል።
ርክክቡ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሰራ ኃላፊዎች በተገኙበት መከናወኑን ከፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ኬኛ የግብርና መሳሪያዎች ማምረቻና ጠቅላላ ንግድ ሀላፊነቱ የተወሰነ ድርጅት በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ ናቸው።
የክልሉ መንግስት ምርትና ምርታማነትን ለማሳድግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡ ትራክተሮቹ የክልሉ መንግስት የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት ለያዘው ውጥን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም
❤5👍2👏1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍3❤2
"ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
*****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት ቤንጃሚን ቦል ሜል ከወንድሜ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ይዘውት የመጡትን መልእክት ተቀብያለሁ ብለዋል።
ከምክትል ፕሬዚዳንቱ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን ወቅታዊውን የጸጥታና የፖለቲካ ችግሮች ለመፍታት፣ ሁሉን አቀፍ ቀጣናዊ አካሄድ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉም ገልጸዋል።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ ከደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት ቤንጃሚን ቦል ሜል ከወንድሜ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ይዘውት የመጡትን መልእክት ተቀብያለሁ ብለዋል።
ከምክትል ፕሬዚዳንቱ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በደቡብ ሱዳን ወቅታዊውን የጸጥታና የፖለቲካ ችግሮች ለመፍታት፣ ሁሉን አቀፍ ቀጣናዊ አካሄድ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን ህዝቦች ያላትን የድጋፍ ቁርጠኝነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉም ገልጸዋል።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም
👍8❤1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
በኢፌዴሪ ህገመንግስት 62 (9)፣ በአዋጅ 359/1995 አንቀጽ 15(3) እና ደንብ ቁጥር 533/2015 እና በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት ሁለት ዓመታት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ላበረከቱት፣ በተለይ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ለነበራቸው ከፍተኛ ጥንቄቄና አመራር የፌዴራል መንግስት እውቅና እንዳለውና በቀጣይ ስራዎችም ተቀራርበን እንደምንሰራ እያረጋገጥኩ ለነበራቸው ቆይታ አመሰግናለሁ።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም
በኢፌዴሪ ህገመንግስት 62 (9)፣ በአዋጅ 359/1995 አንቀጽ 15(3) እና ደንብ ቁጥር 533/2015 እና በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት ሁለት ዓመታት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ላበረከቱት፣ በተለይ የተገኘውን ሰላም ለማፅናት ለነበራቸው ከፍተኛ ጥንቄቄና አመራር የፌዴራል መንግስት እውቅና እንዳለውና በቀጣይ ስራዎችም ተቀራርበን እንደምንሰራ እያረጋገጥኩ ለነበራቸው ቆይታ አመሰግናለሁ።
መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓም
👍17😁7❤5
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የአማራጭ ሳይሆን ምርጫ የሌለው የህልውና ጉዳይ ነው
****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚነቷን ቀደም ሲል በተፈጠረ የፖለቲካ ችግርና የዲፕሎማሲ አያያዝ ምክንያት ብታጣም
አሁን ላይ የቀረበው ጥያቄ የአማራጭ ሳይሆን ምርጫ የሌለው የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ ሌተናል ጀነራል ዮሐንስ ገብረመስቀል ተናገሩ።
ሌተናል ጀነራል ዮሐንስ ለኢፕድ እንደገለፁት፣ ትውልዱ የባሕር በር ጥያቄ በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት ይገባል።
የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ሁሉም ወገን በበጎ መልኩና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ሊመለከተው ይገባል ያሉት ሌተናል ጀነራሉ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ ብትሆን ጥቅሙ ለጎረቤት ሀገራትም ጭምር እንደሆነ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ሳትጠቀም ከ30 ዓመታት በላይ አሳልፋች። ይህ በዝምታ የሚታለፍ ጉዳይ እንዳልሆነ ገልጸው፤ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላምና በሰጥቶ መቀበል መርህ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ተናግረዋል።
ሁሉም የባሕር በር ተጠቃሚ ሀገራት በፍትሃዊ መንገድ ቢጠቀሙ ሁሉንም አትራፊ ያደርጋል ያሉት ሌተናል ጀነራሉ፤ የባሕር በር ጉዳይ ገበያ የሚፈጥር፣ ደህንነትን የሚያረጋግጥና ለኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት በመሆኑ የትውልዱ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው ብለዋል።
የባሕር በር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሰላማዊ መንገድ እስከ መጨረሻው ድረስ መሄድ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህ ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አመላክተዋል... https://press.et/?p=149038
****
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚነቷን ቀደም ሲል በተፈጠረ የፖለቲካ ችግርና የዲፕሎማሲ አያያዝ ምክንያት ብታጣም
አሁን ላይ የቀረበው ጥያቄ የአማራጭ ሳይሆን ምርጫ የሌለው የህልውና ጉዳይ ነው ሲሉ ሌተናል ጀነራል ዮሐንስ ገብረመስቀል ተናገሩ።
ሌተናል ጀነራል ዮሐንስ ለኢፕድ እንደገለፁት፣ ትውልዱ የባሕር በር ጥያቄ በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ እንዲያገኝ መስራት ይገባል።
የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ሁሉም ወገን በበጎ መልኩና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ሊመለከተው ይገባል ያሉት ሌተናል ጀነራሉ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚ ብትሆን ጥቅሙ ለጎረቤት ሀገራትም ጭምር እንደሆነ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ሳትጠቀም ከ30 ዓመታት በላይ አሳልፋች። ይህ በዝምታ የሚታለፍ ጉዳይ እንዳልሆነ ገልጸው፤ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላምና በሰጥቶ መቀበል መርህ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ተናግረዋል።
ሁሉም የባሕር በር ተጠቃሚ ሀገራት በፍትሃዊ መንገድ ቢጠቀሙ ሁሉንም አትራፊ ያደርጋል ያሉት ሌተናል ጀነራሉ፤ የባሕር በር ጉዳይ ገበያ የሚፈጥር፣ ደህንነትን የሚያረጋግጥና ለኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት በመሆኑ የትውልዱ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው ብለዋል።
የባሕር በር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በሰላማዊ መንገድ እስከ መጨረሻው ድረስ መሄድ እንዳለበት ጠቁመው፤ ይህ ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አመላክተዋል... https://press.et/?p=149038
👍11