ጣና ነሽ ጀልባ ከ3 ወራት በኋላ ጎርጎራ ትደርሳለች
*****
(ኢ ፕ ድ)
ጣና ነሽ ጀልባ ከጂቡቲ ዶራሌ ፈርጀ-ብዙ ወደብ ወደ አገር ቤት ዛሬ ጠዋት ጉዞ ጀምራለች። በአማካኝ ከ3 ወራት በኋላ ጎርጎራ ትደርሳለች ተብሎ ይጠበቃል።
የጣና ነሽ ጀልባ 150 ሜትሪክ ቶን ክብደት የምትመዝን፣ 38 ሜትር ርዝመት ያላት እና 200 ተሳፋሪ የመያዝ አቅም ያላት ሲሆን ለመዝናኛ አገልግሎት በመጠቀም እያደገ ያለው የቱሪዝም ዘርፍ ላይ ትልቅ አስተዋጾ የምታበረክት ይሆናል።
ጀልባዋ ከጅቡቲ ተነስታ በዲኪል-ካላፊ መንገድ የምትንቀሳቀስ ሲሆን፣ በአማካይ ከ7 ቀናት በኋላ ኮሪደሩን ታቋርጣለች ተብሎ ይጠበቃል። ለጉዞ የሚሆን የዝቅተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የሃይል ተሸካሚ መስመሮች በኮሪደሩ የሚቋረጡና ተለዋጭ መንገድ የተዘጋጀላቸው ሲሆን፣ ሁለት ተጨማሪ ጎታች ተሽከርካሪዎችና የቴክኒክ ባለሙያዎች ተመድቦ ከጀልባዋ ጋር ጉዞ ጀምሯል።
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ጣና ነሽ ጀልባ ከጂቡቲ ዶራሌ ፈርጀ-ብዙ ወደብ ወደ አገር ቤት ዛሬ ጠዋት ጉዞ ጀምራለች። በአማካኝ ከ3 ወራት በኋላ ጎርጎራ ትደርሳለች ተብሎ ይጠበቃል።
የጣና ነሽ ጀልባ 150 ሜትሪክ ቶን ክብደት የምትመዝን፣ 38 ሜትር ርዝመት ያላት እና 200 ተሳፋሪ የመያዝ አቅም ያላት ሲሆን ለመዝናኛ አገልግሎት በመጠቀም እያደገ ያለው የቱሪዝም ዘርፍ ላይ ትልቅ አስተዋጾ የምታበረክት ይሆናል።
ጀልባዋ ከጅቡቲ ተነስታ በዲኪል-ካላፊ መንገድ የምትንቀሳቀስ ሲሆን፣ በአማካይ ከ7 ቀናት በኋላ ኮሪደሩን ታቋርጣለች ተብሎ ይጠበቃል። ለጉዞ የሚሆን የዝቅተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የሃይል ተሸካሚ መስመሮች በኮሪደሩ የሚቋረጡና ተለዋጭ መንገድ የተዘጋጀላቸው ሲሆን፣ ሁለት ተጨማሪ ጎታች ተሽከርካሪዎችና የቴክኒክ ባለሙያዎች ተመድቦ ከጀልባዋ ጋር ጉዞ ጀምሯል።
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
👍6❤4
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን ተረከቡ
**
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ አቶ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን በዛሬው ዕለት ተረከቡ።
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ባለፋት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው ማገልገላቸው ይታወሳል።
ዛሬ በሰላማዊ መንገድ በአዲስ ባህል የሥልጣን ሽግግርና ቅብብሎሹን ለማካሄድ የተዘጋጀ ፕሮግራምም ተከናውኗል።
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
**
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ አቶ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን በዛሬው ዕለት ተረከቡ።
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ባለፋት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው ማገልገላቸው ይታወሳል።
ዛሬ በሰላማዊ መንገድ በአዲስ ባህል የሥልጣን ሽግግርና ቅብብሎሹን ለማካሄድ የተዘጋጀ ፕሮግራምም ተከናውኗል።
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
👍8👏1
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን ሲረከቡ የፈረሙት የትግራይ ክልል አካታች ጊዜያዊ አስተዳደር የተልዕኮ አፈጻጸም የቃል ኪዳን ሰነድ‼️
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
👍6
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት‼️
ባለፈው አንድ ወር ገደማ የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት፣ የፕሪቶርያን ስምምነትና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡን ምክር በማከል ሰፊ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል። የአቶ ጌታቸው የሥልጣን ዘመን በሕጉ መሠረት ሲያበቃ የሚቀሩ ቁልፍ ሥራዎችን የሚያከናውን አካል፣ ጊዜያዊ መንግሥቱ መቀጠለ አለበት የሚል ድምዳሜ ከተያዘ በኋላ፣ ይሄንን ሽግግር ማን መርቶ ከግብ ሊያደርስ ይችላል? የሚሉ ውይይቶችን ስናደርግ ቆይተናል።
ዛሬ በሰላማዊ መንገድ በአዲስ ባህል የሥልጣን ሽግግሩንና ቅብብሎሹን ለማካሄድ የተዘጋጀ ፕሮግራም አከናውነናል።
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ባለፋት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው ያገለገሉ ሰው ናችው። ባለፋት ሁለት ዓመታት የነበሩ ድካሞችንና ጥንካሬዎችን በግልጽ የሚገነዘቡ ሰው ናቸው።
አሁን ትግራይ ውስጥ ያለውን ክፍተት ሞልተው ወደ ፊት ሊወስዱ ይችላሉ የሚል እምንት በብዙ አካላት የታመነ ነው። የትግራይ ሕዝብ የጠማውን ሰላምና ልማት፣ እንደ ሌሎች ወንድሞቹ ወጥቶ የመግባት መሻት ስናሳካ፣ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካም እጅግ ጠቃሚ የሆነ ነገር ሠርቶ ለማለፍ ታሪክ የሰጣቸውን ዕድል እንደሚጠቀሙበት ተስፋ አደርጋለሁ።
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
ባለፈው አንድ ወር ገደማ የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት፣ የፕሪቶርያን ስምምነትና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡን ምክር በማከል ሰፊ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል። የአቶ ጌታቸው የሥልጣን ዘመን በሕጉ መሠረት ሲያበቃ የሚቀሩ ቁልፍ ሥራዎችን የሚያከናውን አካል፣ ጊዜያዊ መንግሥቱ መቀጠለ አለበት የሚል ድምዳሜ ከተያዘ በኋላ፣ ይሄንን ሽግግር ማን መርቶ ከግብ ሊያደርስ ይችላል? የሚሉ ውይይቶችን ስናደርግ ቆይተናል።
ዛሬ በሰላማዊ መንገድ በአዲስ ባህል የሥልጣን ሽግግሩንና ቅብብሎሹን ለማካሄድ የተዘጋጀ ፕሮግራም አከናውነናል።
ሌ/ጄኔራል ታደሰ ባለፋት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው ያገለገሉ ሰው ናችው። ባለፋት ሁለት ዓመታት የነበሩ ድካሞችንና ጥንካሬዎችን በግልጽ የሚገነዘቡ ሰው ናቸው።
አሁን ትግራይ ውስጥ ያለውን ክፍተት ሞልተው ወደ ፊት ሊወስዱ ይችላሉ የሚል እምንት በብዙ አካላት የታመነ ነው። የትግራይ ሕዝብ የጠማውን ሰላምና ልማት፣ እንደ ሌሎች ወንድሞቹ ወጥቶ የመግባት መሻት ስናሳካ፣ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካም እጅግ ጠቃሚ የሆነ ነገር ሠርቶ ለማለፍ ታሪክ የሰጣቸውን ዕድል እንደሚጠቀሙበት ተስፋ አደርጋለሁ።
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
👍12
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሃሙድ አሊ ዩሱፍ ጋር ያደረጉት ቆይታ‼️
❤5👏2👍1
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
******
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ስብሰባው አራት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
በዚህም መሰረት፤-
1ኛ. በፕላንና ልማት ቢሮ እና በትምህርት ሚኒስቴር በጋራ ተጠንቶ የቀረበዉን ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር በመሆን በአካባቢዉ ያሉትን አገልግሎቶች አካቶ የትምህርት፣ የምርምር፣ የእውቀትና የባህል ልህቀትን በከተማዋ ለማሳደግ በሚያስችል አግባብ የቀረበ በመሆኑ፤ ካቢኔዉ ተወያይቶ የመንደር ምስረታውን ዉሳኔ አፅድቋል፡፡
2ኛ. የምግብ ስርዓትና ኒዉትሪሽን ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል።
3ኛ. የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤትና የአደጋ ዝግጁነት ፈንድ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡
4ኛ. በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቀረበዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች፤ የመሬት ምደባ ጥያቄዎች አስመልክቶ ካቢኔዉ ተወያይቶ ዉሳኔ ማሳለፉን ከከንቲባ ፅሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ስብሰባው አራት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
በዚህም መሰረት፤-
1ኛ. በፕላንና ልማት ቢሮ እና በትምህርት ሚኒስቴር በጋራ ተጠንቶ የቀረበዉን ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር በመሆን በአካባቢዉ ያሉትን አገልግሎቶች አካቶ የትምህርት፣ የምርምር፣ የእውቀትና የባህል ልህቀትን በከተማዋ ለማሳደግ በሚያስችል አግባብ የቀረበ በመሆኑ፤ ካቢኔዉ ተወያይቶ የመንደር ምስረታውን ዉሳኔ አፅድቋል፡፡
2ኛ. የምግብ ስርዓትና ኒዉትሪሽን ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል።
3ኛ. የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤትና የአደጋ ዝግጁነት ፈንድ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡
4ኛ. በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቀረበዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች፤ የመሬት ምደባ ጥያቄዎች አስመልክቶ ካቢኔዉ ተወያይቶ ዉሳኔ ማሳለፉን ከከንቲባ ፅሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም
👍5