Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ላውረንስ ዎንግ በእድገትና አመራር ልምዶቻቸውን ለመለዋወጥ ለእሳት ዳር ወግ ተቀምጠዋል። #PMOEthiopia
❤5👍3
በማርበርግ ቫይረስ እስካሁን የ6 ሰዎች ሕይዎት አልፏል
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በማርበርግ ቫይረስ የ6 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ ወቅታዊውን ሁኔታን በሚመለከት ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።
የጤና ሚኒስትር መቅደስ ዳባ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ጤና ሚኒስቴር የማርበርግ በሽታ ካሳወቀበት ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ቫይረሱን ለመግታት በርካታ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛል።
ቫይረሱ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ እሰከ ዛሬ ጠዋት ድረስ 73 ላብራቶሪ ተሰርቶ በ11 ግለሰቦች ላይ ቫይረሱ መኖሩ ተረጋግጧል ብለዋል።
ቫይረሱ ከተገኘባቸው 11 ሰዎች የ6 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና 5 ሰዎች በህክምና ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
በሕክምና ላይ ካሉት ሰዎች መካከል ደግሞ አንዱ ጽኑ ህሙም እንደሆነ አመላክተዋል።
በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 349 ሰዎች ተለይተው ክትትል ሲደረግ መቆየቱን ገልጸው፤ 119 የክትትል ጊዜ ገድብ ጨርሰው ወጥተዋል ብለዋል።
ምልክት ከታየባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ ሲኖር እራስን መለየት፣ እጅን በሳሙና መታጠብ እና ሌሎች የጥንቃቄ ስራዎችን መስራት ከሁሉም እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
በሄለን ወንድምነው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ጤና #ኢትዮጵያ #ማርበርግ #ቫይረስ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በማርበርግ ቫይረስ የ6 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ ወቅታዊውን ሁኔታን በሚመለከት ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።
የጤና ሚኒስትር መቅደስ ዳባ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ጤና ሚኒስቴር የማርበርግ በሽታ ካሳወቀበት ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ቫይረሱን ለመግታት በርካታ ስራዎችን እየሰሩ ይገኛል።
ቫይረሱ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ እሰከ ዛሬ ጠዋት ድረስ 73 ላብራቶሪ ተሰርቶ በ11 ግለሰቦች ላይ ቫይረሱ መኖሩ ተረጋግጧል ብለዋል።
ቫይረሱ ከተገኘባቸው 11 ሰዎች የ6 ሰዎች ሕይዎት ማለፉን እና 5 ሰዎች በህክምና ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
በሕክምና ላይ ካሉት ሰዎች መካከል ደግሞ አንዱ ጽኑ ህሙም እንደሆነ አመላክተዋል።
በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 349 ሰዎች ተለይተው ክትትል ሲደረግ መቆየቱን ገልጸው፤ 119 የክትትል ጊዜ ገድብ ጨርሰው ወጥተዋል ብለዋል።
ምልክት ከታየባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ ሲኖር እራስን መለየት፣ እጅን በሳሙና መታጠብ እና ሌሎች የጥንቃቄ ስራዎችን መስራት ከሁሉም እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
በሄለን ወንድምነው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ጤና #ኢትዮጵያ #ማርበርግ #ቫይረስ
❤14
አፍሪካውያን ተጽእኖ ፈጣሪ ሴቶች
+++++++++++++++
ዘርፈ-ብዙ ተፅእኖዎችን በመስበር እና ሌሎች ዕድሎችን በመፍጠር ከታሪክ አኳያ ተደማጭነትን ያተረፉ፣ በጦረኝነት እና በአመራር ብቃት ኃያላን ንግሥት የነበሩ፣ በፖለቲካ፣ በንግድ፣ በሰብዓዊ መብት ተሟጋችነት፣ በጥብቅና ሥራ ስኬትን ያገኙ እና ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ያገኙ በርካታ አፍሪካዊ ሴቶችን መጥቀስ ይቻለል፡፡
ከእነዚህ መካከል በንግሥና ዘመናቸው ብርቱና ቆራጥ አመራር የሰጡ፣ ጎበዝ ዲፕሎማትና ወታደራዊ ስትራቴጂስት የነበሩ፣ ከቅኝ ገዢዎች ጋር በመታገል የመንግሥታቸውን እና የሕዝባቸውን ነፃነት ያስጠበቁ፣ የ17ኛው ክፍለ ዘመኗን የአንጎላዋ ንግሥት ንዚንጋ፣ የናይጀሪያዋ የዛዛው መንግሥት አሚና፣ ደቡብ አፍሪካዊቷ ዊኒ ማዲኪዜላ ማንዴላ፣ የጋናዋ ያአ አሳንቴዋ እና የእኛዋ ንግሥት ጣይቱ ብጡል ይጠቀሳሉ።
ሙሉ ጽሑፉ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ በመጫን ያገኙታል https://press.et/am-digital-content/share/am-stories/40vj94a53qpdg5ms91511z5h41
+++++++++++++++
ዘርፈ-ብዙ ተፅእኖዎችን በመስበር እና ሌሎች ዕድሎችን በመፍጠር ከታሪክ አኳያ ተደማጭነትን ያተረፉ፣ በጦረኝነት እና በአመራር ብቃት ኃያላን ንግሥት የነበሩ፣ በፖለቲካ፣ በንግድ፣ በሰብዓዊ መብት ተሟጋችነት፣ በጥብቅና ሥራ ስኬትን ያገኙ እና ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ያገኙ በርካታ አፍሪካዊ ሴቶችን መጥቀስ ይቻለል፡፡
ከእነዚህ መካከል በንግሥና ዘመናቸው ብርቱና ቆራጥ አመራር የሰጡ፣ ጎበዝ ዲፕሎማትና ወታደራዊ ስትራቴጂስት የነበሩ፣ ከቅኝ ገዢዎች ጋር በመታገል የመንግሥታቸውን እና የሕዝባቸውን ነፃነት ያስጠበቁ፣ የ17ኛው ክፍለ ዘመኗን የአንጎላዋ ንግሥት ንዚንጋ፣ የናይጀሪያዋ የዛዛው መንግሥት አሚና፣ ደቡብ አፍሪካዊቷ ዊኒ ማዲኪዜላ ማንዴላ፣ የጋናዋ ያአ አሳንቴዋ እና የእኛዋ ንግሥት ጣይቱ ብጡል ይጠቀሳሉ።
ሙሉ ጽሑፉ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ በመጫን ያገኙታል https://press.et/am-digital-content/share/am-stories/40vj94a53qpdg5ms91511z5h41
❤6
ኮፕ 32 ቁልፍ የዝግጅት ተግባራትን ለማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ ተደረገ
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - በትናንትናው ዕለት የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዚዳንት መሰየምን ተከትሎ ዛሬ ጠዋት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ቁልፍ የዝግጅት ተግባራትን ለማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ ተደርጓል።
ስብሰባው ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ስታስተናግድ አካታችና በሚገባ የተሰናዳ ጉባኤ እንድታሳካ ለማረጋገጥ መንግሥት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት እንደነበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል። #PMO
#PMOEthiopia #COP32 #G20
++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - በትናንትናው ዕለት የኮፕ 32 ተወካይ ፕሬዚዳንት መሰየምን ተከትሎ ዛሬ ጠዋት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ቁልፍ የዝግጅት ተግባራትን ለማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ ተደርጓል።
ስብሰባው ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ስታስተናግድ አካታችና በሚገባ የተሰናዳ ጉባኤ እንድታሳካ ለማረጋገጥ መንግሥት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት እንደነበር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል። #PMO
#PMOEthiopia #COP32 #G20
❤3👍1
የመንግሥት ሠራተኞች የጤና መድን ተጠቃሚ ሊሆኑ ነው
++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የመንግሥት ሠራተኞች በቀጣዩ 2019 ዓ.ም የጤና መድን አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ወርቁ እንደገለጹት፤ መደበኛ በሆኑ የሥራ መስኮች የተሰማሩ ዜጎች የጤና መድን አገልግሎት እንዲያገኙ ታስቦ የተዘጋጀው የማኅበራዊ ጤና መድን አገልግሎት በአዋጅና ደንብ ከጸደቀ 14 ዓመታትን አስቆጥሯል።
አዋጁ ሠራተኛው ከደመወዙ ሦስት በመቶው እንዲቆረጥና የፌዴራልና የክልል መንግሥታትም ለቀጠሩት ሠራተኛ ሦስት በመቶውን እንዲሸፍኑ ይደነግጋል።
ሆኖም ግን ባለፉት ዓመታት በመንግሥት በኩል በቂ ገንዘብ ባለመኖሩና በኑሮ ዉድነት አማካኝነት ሳይተገበር ቢቆይም በዘንድሮዉ ዓመት ግን የተሻለ ተስፋ ታይቷል ብለዋል።
በዘንድሮው ዓመት በጤናው ዘርፍ የተሰማሩ ከ500 ሺህ በላይ ሠራተኞች ለአገልግሎቱ መመዝገባቸውን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፤ ከገንዘብ ሚኒስቴርም 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር መጽደቁን ተናግረዋል።
በሚቀጥለው ዓመትም ሁሉም የመንግሥት ሠራተኛ ተጠቃሚ እንዲሆን የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት በጀት ይይዛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
መስከረም ሰይፉ
#ጋዜጣ_ፕላስ #gazetteplus #ጤና_መድን #ጤና #ኢትዮጵያ
++++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | የመንግሥት ሠራተኞች በቀጣዩ 2019 ዓ.ም የጤና መድን አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ወርቁ እንደገለጹት፤ መደበኛ በሆኑ የሥራ መስኮች የተሰማሩ ዜጎች የጤና መድን አገልግሎት እንዲያገኙ ታስቦ የተዘጋጀው የማኅበራዊ ጤና መድን አገልግሎት በአዋጅና ደንብ ከጸደቀ 14 ዓመታትን አስቆጥሯል።
አዋጁ ሠራተኛው ከደመወዙ ሦስት በመቶው እንዲቆረጥና የፌዴራልና የክልል መንግሥታትም ለቀጠሩት ሠራተኛ ሦስት በመቶውን እንዲሸፍኑ ይደነግጋል።
ሆኖም ግን ባለፉት ዓመታት በመንግሥት በኩል በቂ ገንዘብ ባለመኖሩና በኑሮ ዉድነት አማካኝነት ሳይተገበር ቢቆይም በዘንድሮዉ ዓመት ግን የተሻለ ተስፋ ታይቷል ብለዋል።
በዘንድሮው ዓመት በጤናው ዘርፍ የተሰማሩ ከ500 ሺህ በላይ ሠራተኞች ለአገልግሎቱ መመዝገባቸውን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፤ ከገንዘብ ሚኒስቴርም 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር መጽደቁን ተናግረዋል።
በሚቀጥለው ዓመትም ሁሉም የመንግሥት ሠራተኛ ተጠቃሚ እንዲሆን የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት በጀት ይይዛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
መስከረም ሰይፉ
#ጋዜጣ_ፕላስ #gazetteplus #ጤና_መድን #ጤና #ኢትዮጵያ
❤11👍3