"ኢትዮጵያ ከአይ ኤም ኤፍ /IMF/ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት አጠናክራ ትቀጥላለች"
- አህመድ ሺዴ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ ከአይ ኤም ኤፍ /IMF/ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት አጠናክራ ታስቀጥላለች ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ገለጹ።
የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ሊቀመንበር ናይጄል ክላርክ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ሊቀመንበር ናይጄል ክላርክ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ እንደገለጹት፤ መንግስት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ በማጠናከር ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማረጋገጥ የሚሰሩ ስራዎችን አጠናክሮ ያስቀጥላል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፋይናንስ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በሌሎች ዘርፎች ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
የማሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በዓለም ደረጃ ጥሩ ግምት የሚሰጠው ውጤት እያስገኘ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ከአይ ኤም ኤፍ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነትም አጠናክራ ለማስቀጠል ያላትን ፍላጎት አፅንኦት ሰጥተዋል።
የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ዳይሬክተር ናይጄል ክላርክ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ያላትን እድገት አድንቀዋል።
በማሻሻያው የዋጋ ግሽበት መቀነሱን፣ የውጭ ምንዛሪ ክምችት መጨመሩን ፣ የመንግስት ፋይናንስ መጠናከሩን እና የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መጠናከሩን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም በርካታ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
አይ ኤም ኤፍ ለሀገሪቱ እና ለህዝቦቿ ኢኮኖሚውን የበለጠ ለማጠናከር በተራዘመ ብድር ኢትዮጵያን ለመደገፍ ቁርጠኛ ሆኖ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
የአይኤምኤፍ ምክትል ሊቀመንበር ናይጄል ክላርክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ባሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ በአይኤምኤፍ ድጋፍ እና የቀጣይ ትብብር ላይ ውይይት አድርገዋል።
በተጨማሪም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን፣ ኮይሻን እና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
በሄለን ወንድምነው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #አይኤምኤፍ
- አህመድ ሺዴ
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ ከአይ ኤም ኤፍ /IMF/ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት አጠናክራ ታስቀጥላለች ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ገለጹ።
የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ሊቀመንበር ናይጄል ክላርክ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ሊቀመንበር ናይጄል ክላርክ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ እንደገለጹት፤ መንግስት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ በማጠናከር ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማረጋገጥ የሚሰሩ ስራዎችን አጠናክሮ ያስቀጥላል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፋይናንስ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በሌሎች ዘርፎች ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
የማሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በዓለም ደረጃ ጥሩ ግምት የሚሰጠው ውጤት እያስገኘ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ከአይ ኤም ኤፍ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነትም አጠናክራ ለማስቀጠል ያላትን ፍላጎት አፅንኦት ሰጥተዋል።
የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ዳይሬክተር ናይጄል ክላርክ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ያላትን እድገት አድንቀዋል።
በማሻሻያው የዋጋ ግሽበት መቀነሱን፣ የውጭ ምንዛሪ ክምችት መጨመሩን ፣ የመንግስት ፋይናንስ መጠናከሩን እና የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መጠናከሩን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም በርካታ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
አይ ኤም ኤፍ ለሀገሪቱ እና ለህዝቦቿ ኢኮኖሚውን የበለጠ ለማጠናከር በተራዘመ ብድር ኢትዮጵያን ለመደገፍ ቁርጠኛ ሆኖ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
የአይኤምኤፍ ምክትል ሊቀመንበር ናይጄል ክላርክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ባሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ በአይኤምኤፍ ድጋፍ እና የቀጣይ ትብብር ላይ ውይይት አድርገዋል።
በተጨማሪም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን፣ ኮይሻን እና ሌሎች ሜጋ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
በሄለን ወንድምነው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #አይኤምኤፍ
❤4👍2
"መምህራን በደመወዝ ይበልጠናል የሚሉት ‘ሴክተር’ የለም"
- ሽመልስ አበበ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ ፕላስ | በአሁኑ ጊዜ መምህራን በደመወዝ ይበልጠናል የሚሉት ‘ሴክተር’ የለም ሲሉ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አበበ ገለጹ።
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አበበ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ባለፉት ጊዜያት የመምህራን ደመወዝ ከሌላው ሴክተር በብዙ መንገድ የተጎዳ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከሲቪል ሰርቪስ እና ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በሚገባ በአጋርነት በመሰራቱ መምህራን አሁን ላይ በደመወዝ ይበልጠናል የሚሉት ሴክተር የላቸውም ሲሉ አስታውቀዋል።
መምህራን የተሻለ ደመወዝ ላይ ቢሆኑም፤ በሀገሪቱ ያለው የዋጋ ንረት ላይ መንግሥት ትኩረት ማድረግ ይገባዋል ብለዋል።
በሄለን ወንድምነው
++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #መምህራን #ኢትዮጵያ #መምህር
- ሽመልስ አበበ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ ፕላስ | በአሁኑ ጊዜ መምህራን በደመወዝ ይበልጠናል የሚሉት ‘ሴክተር’ የለም ሲሉ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አበበ ገለጹ።
የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አበበ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ባለፉት ጊዜያት የመምህራን ደመወዝ ከሌላው ሴክተር በብዙ መንገድ የተጎዳ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከሲቪል ሰርቪስ እና ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በሚገባ በአጋርነት በመሰራቱ መምህራን አሁን ላይ በደመወዝ ይበልጠናል የሚሉት ሴክተር የላቸውም ሲሉ አስታውቀዋል።
መምህራን የተሻለ ደመወዝ ላይ ቢሆኑም፤ በሀገሪቱ ያለው የዋጋ ንረት ላይ መንግሥት ትኩረት ማድረግ ይገባዋል ብለዋል።
በሄለን ወንድምነው
++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ #መምህራን #ኢትዮጵያ #መምህር
❤11👍5👎2
የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት ከክልሉ መንግስት ጋር ያደረገው የሰላም ስምምነት የያዛቸው ዋና ዋና ነጥቦች
+++++++++
✍️ የአማራ ህዝብ በማንነቱ እንዳይገደል፣ እንዳይሳደድ እና እንዳይፈናቀል፤
✍️ የተፈናቀሉ ዜጎች እንዲመለሱ ማድረግ፤
✍️ የአማራ ክልል እኩል የመልማትና የመጠቀም መብት እንዲኖረው ማድረግ፤
✍️ በፋኖ ስም በፌደራልም ሆነ በክልል ማረሚያ ቤት ያሉ አባላት እንዲፈቱ፤
✍️ የቆሰሉ ሰዎችን መልሶ የማቋቋም ስራ እንዲሰራ፤
✍️ አቅምና እውቀት ያላቸው አባላት እንዲሁም የወታደር ቁመና ያላቸው የጸጥታ ሃይሉን እንዲሁም ማህበረሰቡን እንዲቀላቀሉ ማስቻል፤
✍️ የመንግስት ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱና የቀረባቸው ጥቅማ ጥቅም እንዲከፈላቸው፤
✍️ ትምህርታቸውን ያቋረጡ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የሚሉ ጉዳዮች ላይ ከመግባባት ተደርሷል፤
ምንጭ:- ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የውጪ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ
+++++++++
✍️ የአማራ ህዝብ በማንነቱ እንዳይገደል፣ እንዳይሳደድ እና እንዳይፈናቀል፤
✍️ የተፈናቀሉ ዜጎች እንዲመለሱ ማድረግ፤
✍️ የአማራ ክልል እኩል የመልማትና የመጠቀም መብት እንዲኖረው ማድረግ፤
✍️ በፋኖ ስም በፌደራልም ሆነ በክልል ማረሚያ ቤት ያሉ አባላት እንዲፈቱ፤
✍️ የቆሰሉ ሰዎችን መልሶ የማቋቋም ስራ እንዲሰራ፤
✍️ አቅምና እውቀት ያላቸው አባላት እንዲሁም የወታደር ቁመና ያላቸው የጸጥታ ሃይሉን እንዲሁም ማህበረሰቡን እንዲቀላቀሉ ማስቻል፤
✍️ የመንግስት ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱና የቀረባቸው ጥቅማ ጥቅም እንዲከፈላቸው፤
✍️ ትምህርታቸውን ያቋረጡ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ የሚሉ ጉዳዮች ላይ ከመግባባት ተደርሷል፤
ምንጭ:- ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ
የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የውጪ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ
❤25👏4
20ኛው የኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን
"ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት"
የ20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ታዳሚዎች - ሆሳዕና
"ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት"
የ20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል ታዳሚዎች - ሆሳዕና
❤1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
'ብሄራዊ ጥቅም' የምንፈልገው ፣ የምንሞትለትና የምንታገልለት ጉዳይ ነው- ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ
👉 https://youtu.be/ayTJYUFkmYM?si=YO-2yPTpz8ldvffQ
👉 https://youtu.be/ayTJYUFkmYM?si=YO-2yPTpz8ldvffQ
❤2
ጅማ ከተማ 21ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እንድታዘጋጅ ተመረጠች
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ጅማ ከተማ 21ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እንድታዘጋጅ ተመረጠች።
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት፣ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
በዚሁ መርሃግብር ላይ ጅማ ከተማ በቀጣይ ዓመት 21ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እንድታዘጋጅ ተመርጣለች።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#Gazetteplus #ጋዜጣፕላስ #ጅማ
+++++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ጅማ ከተማ 21ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እንድታዘጋጅ ተመረጠች።
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት፣ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው።
በዚሁ መርሃግብር ላይ ጅማ ከተማ በቀጣይ ዓመት 21ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እንድታዘጋጅ ተመርጣለች።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#Gazetteplus #ጋዜጣፕላስ #ጅማ
❤5
“ማንኛውም ትንኮሳና ፈተና ኢትዮጵያን ከብልጽግና ጉዞ ማስቆም አይችልም”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ማንኛውም ትንኮሳና ፈተና ኢትዮጵያን ከብልጽግና ጉዞ ማቆም አይችልም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማንኛውም ፈተና፣ ትንኮሳና ክፉ ሃሳብ ኢትዮጵያን ከብልጽግና ማቆም አይችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ጠላቶች አንድ በአንድ እናራግፋለን ብለዋል።
ከአባቶቻችን በደም የወረስነውን ነጻነት በብልጽግና ማጽናት ከዚህ ትውልድ እንደሚጠበቅ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኑን ገልጸዋል።
ብልጽግናን ማሳካት ፈታኝ መሆኑን በመግለጽ፤ የወረስነውን ነጻነት ብቻ ሳይሆን የተሸከምነውን የትውልድ አደራ ማሰብ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ማየት አለብን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ትውልድ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ፍልፍሎ የማየትና የማውጣት ብቃት አለው ብለዋል።
ከኢትዮጵያ መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትም እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ የጸናች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊነት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአገርን መሻትና የባዳን ክፋት መለየት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ፤ ኢትዮጵያዊያን ለባዳ ፍላጎት መሳሪያ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያዊያን ቀልብ ገዝተን ሰላማችንን እናጽና ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የአገርን ክብርና የዜጎችን ጥቅም እናስከብር ብለዋል።
ኢትዮጵያ በብዙ ተስፋ የተመላች አገር መሆኑኗን ጠቅሰው፤ አስደናቂ ጅማሮና ውጤት እያሳየች መሆኑንም ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ብሔርብሔረሰቦች #በዓል #ሆሳዕና #ዐቢይ_አሕመድ
#ጠቅላይ_ሚኒስትር
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ማንኛውም ትንኮሳና ፈተና ኢትዮጵያን ከብልጽግና ጉዞ ማቆም አይችልም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ20ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ማንኛውም ፈተና፣ ትንኮሳና ክፉ ሃሳብ ኢትዮጵያን ከብልጽግና ማቆም አይችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያን ጠላቶች አንድ በአንድ እናራግፋለን ብለዋል።
ከአባቶቻችን በደም የወረስነውን ነጻነት በብልጽግና ማጽናት ከዚህ ትውልድ እንደሚጠበቅ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ከጨለማ ወደ ንጋት እየተሸጋገረች መሆኑን ገልጸዋል።
ብልጽግናን ማሳካት ፈታኝ መሆኑን በመግለጽ፤ የወረስነውን ነጻነት ብቻ ሳይሆን የተሸከምነውን የትውልድ አደራ ማሰብ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ማየት አለብን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ትውልድ ችግሯን ብቻ ሳይሆን አቅሟን ፍልፍሎ የማየትና የማውጣት ብቃት አለው ብለዋል።
ከኢትዮጵያ መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትም እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ የጸናች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊነት ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
የአገርን መሻትና የባዳን ክፋት መለየት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ፤ ኢትዮጵያዊያን ለባዳ ፍላጎት መሳሪያ መሆን እንደሌለባቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያዊያን ቀልብ ገዝተን ሰላማችንን እናጽና ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የአገርን ክብርና የዜጎችን ጥቅም እናስከብር ብለዋል።
ኢትዮጵያ በብዙ ተስፋ የተመላች አገር መሆኑኗን ጠቅሰው፤ አስደናቂ ጅማሮና ውጤት እያሳየች መሆኑንም ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ብሔርብሔረሰቦች #በዓል #ሆሳዕና #ዐቢይ_አሕመድ
#ጠቅላይ_ሚኒስትር
👍8❤5👏1
ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በጄኔቫ ስዊዘርላንድ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ድርጅታዊ ስብሰባ ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የቢሮ አባል በመሆን ተመርጣለች።
በዚህም ኢትዮጵያ አፍሪካን በመወከል ለአንድ ዓመት ያህል በመሪነት ሚና እንደምታገለግል ተመላክቷል።
የኢትዮጵያን መመረጥ ተከትሎ በተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋብ ክበበው ዳካ እና በስዊዘርላንድ የሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው እንደሚያገለግሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
በአማን ረሺድ
++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | በጄኔቫ ስዊዘርላንድ በተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ድርጅታዊ ስብሰባ ኢትዮጵያ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የቢሮ አባል በመሆን ተመርጣለች።
በዚህም ኢትዮጵያ አፍሪካን በመወከል ለአንድ ዓመት ያህል በመሪነት ሚና እንደምታገለግል ተመላክቷል።
የኢትዮጵያን መመረጥ ተከትሎ በተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ፀጋብ ክበበው ዳካ እና በስዊዘርላንድ የሚገኙ ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው እንደሚያገለግሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
በአማን ረሺድ
❤4👎1👏1