Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በውሃ ላይ የሚያርፉ አውሮፕላኖች ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ነው
+++++++++++++++++++++++++

ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቱሪዝም አገልግሎት የሚውሉና በውሃ ላይ ማረፍ የሚችሉ አውሮፕላኖችን በቀጣይ ጥቂት ወራት ወደ ሀገር ውስጥ ሊያስገባ መሆኑን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለፁት፤ አየር መንገዱ የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግና በቂ የአውሮፕላን ማረፊያ በሌላቸው የቱሪስት መዳረሻዎች አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ በውሃ ላይ የሚያርፉ አውሮፕላኖችን በቅርቡ ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባል።

አውሮፕላኖቹ በመጋቢትና ሰኔ ወራት ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገቡና የሙከራ አገልግሎት እንደሚጀምሩም ገልጸዋል።

እነዚህ አውሮፕላኖች በውሃም ሆነ በመሬት ላይ ማረፍ የሚችሉ መሆናቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ በቅርቡ የሚጀመረው የሙከራ አገልግሎት ስኬታማ ከሆነ ተጨማሪ አውሮፕላኖች እንደሚታዘዙ አስረድተዋል።

ይህም ወደ ቱሪዝም መዳረሻዎች በአውሮፕላን ለመጓዝ ለሚፈልጉ መንገደኞች ትልቅ አማራጭ እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።

በክብረአብ በላቸው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #አየር_መንገድ #ቱሪዝም #አቪዬሽን
6👍3
ከአውድ ውጪ የተሰራጨ መረጃ
+++++++++++++
#የፕሬስ_መረጃ_ማጣሪያ- ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል መታወቂያ ይዘው የሚታዩበት ፎቶግራፍ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲዘዋወር ተመልክተናል። ይሁን እንጂ ይህ ትክክለኛ ፎቶግራፍ አለመሆኑን የኢፕድ የመረጃ ማጣሪያ አረጋግጧል። https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0k5kskAzdQifV2J7McFNfY9WcxogXbS7U9vMDrJaVVgFctNSzXkt1QCZrnQFmT44fl&id=61550238885521&sfnsn=mo

#fakeimages  #fakeNewsAlert  #የፕሬስ_መረጃ_ማጣሪያ
የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብያለሁ። ባለፈው አንድ አመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።

የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋትና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር።

-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
9
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ መሐሙድን ያደረጉት አቀባበል #PMOEthiopia
5
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው እለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አስጀምረናል።

ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር፤ በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች ናቸው።

እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው።

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

#DigitalEthiopia2030
5
“ኢትዮጵያ የማደግ ፍላጎትና አቅም ያላት ሀገር ናት። ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ ዲጂታል መርሃ ግብር ፈጠራ፣ ፍጥነትና እመርታን በማምጣት የማደግ ፍላጎታችንን ከአቅመችን ጋር እንዲናበብ እያደረገ ነው።

የዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በማስፋት ዘርፈ ብዙ ቱርፋቶች ተመዝግበውበታል።

በመንግስት አሰራር፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በፋይናንስ ተደራሽነት ላይም ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል። ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አሰጀምረናል።

በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ዘላቂ የዲጂታል እመርታ እንዲመዘገብ ይሰራል።

አቶ ተመስገን ጥሩነህ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክርቤት ሊቀመንብር

#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia
ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ሰው ተኮርና ለሁሉም ሴክተሮች ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት ይሆናል። በዲጂታል 2025 የተመዘገቡ የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋት ስራውን በተጨባጭ ውጤት የምናሳይበት ጭምር ነው።

ስትራቴጂው በግልጽ የአስተዳደር ስርዓት፣ በሚለካ ውጤትና በተጠያቂነት ላይ ተመስርቶ በቀጣይ አምስት ዓመታት ተግባራዊ ይሆናሉ። ለዚህ ደግሞ ሁሉም የሚመለከተው አካል የጋራ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅበታል።

ሚሪያም አሊ
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ

#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia