የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብያለሁ። ባለፈው አንድ አመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋትና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር።
-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋትና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር።
-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
❤9
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ መሐሙድን ያደረጉት አቀባበል #PMOEthiopia
❤5
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው እለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አስጀምረናል።
ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር፤ በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች ናቸው።
እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#DigitalEthiopia2030
ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር፤ በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች ናቸው።
እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል። በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ ናቸው።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#DigitalEthiopia2030
❤5
“ኢትዮጵያ የማደግ ፍላጎትና አቅም ያላት ሀገር ናት። ከዚህ አኳያ የኢትዮጵያ ዲጂታል መርሃ ግብር ፈጠራ፣ ፍጥነትና እመርታን በማምጣት የማደግ ፍላጎታችንን ከአቅመችን ጋር እንዲናበብ እያደረገ ነው።
የዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በማስፋት ዘርፈ ብዙ ቱርፋቶች ተመዝግበውበታል።
በመንግስት አሰራር፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በፋይናንስ ተደራሽነት ላይም ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል። ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አሰጀምረናል።
በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ዘላቂ የዲጂታል እመርታ እንዲመዘገብ ይሰራል።
አቶ ተመስገን ጥሩነህ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክርቤት ሊቀመንብር
#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia
የዲጂታል 2025 ስትራቴጂ በኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በማስፋት ዘርፈ ብዙ ቱርፋቶች ተመዝግበውበታል።
በመንግስት አሰራር፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በፋይናንስ ተደራሽነት ላይም ከፍተኛ ለውጥ መጥቷል። ዛሬ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አሰጀምረናል።
በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ዘላቂ የዲጂታል እመርታ እንዲመዘገብ ይሰራል።
አቶ ተመስገን ጥሩነህ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክርቤት ሊቀመንብር
#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia
ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ሰው ተኮርና ለሁሉም ሴክተሮች ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት ይሆናል። በዲጂታል 2025 የተመዘገቡ የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋት ስራውን በተጨባጭ ውጤት የምናሳይበት ጭምር ነው።
ስትራቴጂው በግልጽ የአስተዳደር ስርዓት፣ በሚለካ ውጤትና በተጠያቂነት ላይ ተመስርቶ በቀጣይ አምስት ዓመታት ተግባራዊ ይሆናሉ። ለዚህ ደግሞ ሁሉም የሚመለከተው አካል የጋራ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅበታል።
ሚሪያም አሊ
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ
#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia
ስትራቴጂው በግልጽ የአስተዳደር ስርዓት፣ በሚለካ ውጤትና በተጠያቂነት ላይ ተመስርቶ በቀጣይ አምስት ዓመታት ተግባራዊ ይሆናሉ። ለዚህ ደግሞ ሁሉም የሚመለከተው አካል የጋራ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅበታል።
ሚሪያም አሊ
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ
#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia
“ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ ላይ ቁልፍ ጉዳይ ሆኖ ተተግብሯል። አሁን ላይ 30 ሚሊዮን ዜጎች ፋይዳ መታወቂያ ተመዝግበዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ላይም ፋይዳ ስትራቴጂካዊ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን ሙሉ ለሙሉ ተደራሽ የማድረግ ስራም ይሰራል።
በተለይ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ አገልግሎቶችን ከፋይዳ ጋር በማስተሳሰር በስትራቴጂው የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል። ለዚህ ደግሞ ሁሉም በትብብር ሊሰራ ይገባል።
ዮዳሄ አርአያስለሴ
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ
#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia #fayda
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ላይም ፋይዳ ስትራቴጂካዊ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን ሙሉ ለሙሉ ተደራሽ የማድረግ ስራም ይሰራል።
በተለይ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ያሉ አገልግሎቶችን ከፋይዳ ጋር በማስተሳሰር በስትራቴጂው የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት ይሰራል። ለዚህ ደግሞ ሁሉም በትብብር ሊሰራ ይገባል።
ዮዳሄ አርአያስለሴ
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ
#DigitalEthiopia2030
#PMOEthiopia #fayda
❤5