Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
"የእስካሁኑ ጥፋት ይብቃ፤ ከአሁን በኋላ ችግሮቻችንን በምክክር እንፍታ" - ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
እስካሁን የጠፋው ጥፋት ይብቃ ከአሁን በኋላ ችግሮቻችንን በምክክርና በውይይት እንፍታ ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ ገለፁ። ተቀዳሚ ሙፍቲው አገርን ለማስቀጠል የአገራዊ ምክክሩ ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነም ተናግረዋል።
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ እስካሁን የጠፋው ጥፋት ይበቃል በማለት ፊትን ወደ ሰላም ማዞር ይገባል።
አገርን ለማስቀጠል የአገራዊ ምክክሩ ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነ የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ምክክሩ እኩልነት በሰፈነበት፤ በእውነትና በአንድነት መንገድ የሚከወን ከሆነ ለአገራችን አወንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
መመካከርና መወያየት የቆየ የኢትዮጵያውያን ትወፊት እንደሆነ ያወሱት ሃጂ ዑመር፤ በመመካከርና በመወያየት ችግራችንን ልንፈታ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
ተቀዳሚ ሙፍቲው አገራዊ ምክክሩ ወደታች ወርዶ ተፈፃሚ እንዲሆን እንዲሁም አገር ወደ ሰላማዊ ሁኔታዋ እንድትመለስ ከመንግሥትና ከኅብረተሰቡ ብዙ ይጠበቃል ብለዋል።
ሕዝቡ ጥፋተኛን ለይቶ በማውጣትና የጥፋት መንገዶችን በመዝጋት....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70676
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
"አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂዩማን ራይትስዎች ያወጡት ሪፖርት ከመረጃ አሰባሰቡ እስከ ውጤቱ ለአንድ ወገን ያደላ ነው" -አምባሳደር ዲና ሙፍቲ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ከሰሞኑ አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂዩማን ራይትስ ዎች በጋራ በመሆን ኢትዮጵያን በሚመለከት ያወጡት ሪፖርት ከመረጃ አሰባሰቡ እስከ ውጤቱ ለአንድ ወገን ያደላ መሆኑን የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለፁ።
አምባሳደር ዲና በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፣ ተቋማቱ መሬት ላይ የሚታዩና በርካታ መረጃዎችና ሁኔታዎችን በተገቢው ሁኔታ ሳይከታተሉ እንዲሁም ተገቢውን የማጣራት ሂደት ሳይከተሉ ለአንድ ወገን በማድላት ሌላኛውን ደግሞ በመኮነን ሪፖርት አውጥተዋል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂዩማን ራይትስ ዎች በጋራ በመሆን ያወጡት ሪፖርት ወገንተኛነታቸውንና ጭፍን አቋማቸውን ያራመዱበት ሪፖርት ትክክል አለመሆኑን የተናገሩት አምባሳደር ዲና፣ የአማራ ክልል መንግሥት ይህን በሚመለከት ያወጣው መግለጫ ተገቢነት ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ በክልሉም ሆነ በፌዴራሉ መንግሥት ጉዳዩን በገለልተኛ አካል ለማጣራት ቀደም ተብሎ የታቀደና አቋም የተወሰደበት፤ በዚህም ወደ ተግባር ተገብቶ የጥናት ውጤቶች ይፋ እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና በኢትዮጵያ በኩል የሚመለከታቸው አካላት በጋራ በመሆን ባደረጉት ምርመራ በወጣው.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70674
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
በእስራኤል በአምስት ከተሞች ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የድጋፍ ማሰባሰብ ዝግጅት ተካሄደ
******************
(ኢ ፕ ድ)

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ የተጣለበትን 11ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በእስራኤል በአምስት የተለያዩ ከተሞች የድጋፍ ማሰባሰቢያና ግንዛቤ መፍጠሪያ መርሃ ግብሮች በኤምባሲው አስተባባሪነት ተካሄደዋል።

በቴል- አቪቭ፣ እየሩሳሌም፣ሃይፋና አካባቢው፣ በናታኒያና በቂሪያት ጋት ከተሞች ነው የተካሄደው።

አምባሳደር ረታ ዓለሙ ባስተላለፉት መልዕክት በእስራኤል የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንና ኢትዮጵያዊያን የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ እስካሁን ድረስ ከአንድ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ በቦንድ ግዥና በስጦታ ድጋፍ አድርገዋል።

ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ወደፊትም ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በአጠቃላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በቦንድ ግዥና በስጦታ ከ11 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ከመደረጉ ባሻገር፤ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል።

በየከተሞች በነበሩት ዝግጅቶች አስተባባሪ አካላት መርሐ ግብሩ እንዲሳካ አስተዎፆኦ አበርክተዋል።

በቢኒ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው በአባይ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥን ፊልምና ሌሎች የኪነጥበብ ሥራዎች ለታዳሚዎች መቅረቡን ኤምባሲው አሰታውቋል።
«ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የሰላም ሂደት የማይተካ ሚና እየተጫወተች ነው» - አምባሳደር ጄምስ ፒቲአ ሞርጋን
******
(ኢ ፕ ድ)

ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የሰላምና መረጋጋት ሂደት መሳካት የማይተካ ሚና እየተጫወተች ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጄምስ ፒቲአ ሞርጋን አስታወቁ።

የአገራቱ ግንኙነት መጠናከር ጠቀሜታው ለምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ጭምር መሆኑን አምባሳደሩ ገልጸዋል።

ጄምስ ፒቲአ ሞርጋን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለደቡብ ሱዳን የሰላምና መረጋጋት ሂደት መሳካት እያበረከተችው ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው።

የደቡብ ሱዳን መረጋጋት የኢትዮጵያም መረጋጋት ነው ከሚል እሳቤ የመነጨው ድጋፍ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና እንዲረጋጋ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ያሉት አምባሳደሩ፤ ይህ የኢትዮጵያ አቋም ለደቡብ ሱዳናውያን ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የደቡብ ሱዳናውያን ችግር በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የሚያደርጉት ጥረት የሚደነቅ ነው፤ ይህ ወንድማዊ አካሄዳቸውም ኢትዮጵያ ምንጊዜም ከደቡብ ሱዳን ጎን እንድትቆም የሚያደርጋት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን እ.አ.አ. በ2018 በአዲስ አበባ የተፈራረሙት ስምምነት

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70719
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
አቮካዶን ከአገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየተሠራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ
*****
(ኢ ፕ ድ)

ከቅርብ አመታት ወዲህ የአቮካዶ ተክልን በማስፋትና ምርታማነትን በመጨመር ከአገር ፍጆታ አልፎ ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየተሠራ መሆኑ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በግብርና ሚኒስቴር የሆልቲ ካልቸር ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር አቶ አብደላ ነጋሽ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ አርሶ አደሩ ጥራት ያለው፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነትና ተፈላጊነት ያላቸው የአቮካዶ ዝርያዎችን እንዲያገኝ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው። የአቮካዶ ምርትን ወደ ውጭ ለመላክ በአሁኑ ሰዓት የሀስ ዝርያ በከፍተኛ ሁኔታ እየተባዛ መሆኑን አብራርተዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ሥራዎች እየተሠሩ ነው። በአምስት የችግኝ ማባዣ ማዕከሎች የአቮካዶ ችግኞች እየተባዙ ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ ሲደረግ ቆይቷል። ነገር ግን የሕዝቡ ፍላጎት በመጨመሩ ውስን የነበሩ የችግኝ ማባዣ ማዕከላትን በማስፋት የአቮካዶ ችግኝ እንደ አገር በስፋት እንዲዳረስ እየተሠራ ስለመሆኑ ገልጸዋል።

በአሁኑ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ 50 በሚደርሱ የችግኝ ጣቢያ ማዕከላት...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70682

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
"ፍራንኮ ቫሉታን መፈቀዱ የዋጋ ግሽበቱን ለመቀነስና የምርት አቅርቦትን ለመጨመር ይረዳል"
- አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ
*******
(ኢ ፕ ድ)

መንግሥት በመሠረታዊ የምግብ ፍጆታዎች ላይ ፍራንኮ ቫሉታን መፍቀዱ የዋጋ ግሽበቱን ለመቀነስና የምርት አቅርቦትን ለመጨመር እንደሚረዳ የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ገለጹ።

አቶ ዘመዴነህ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ መንግሥት መሠረታዊ የምግብ ፍጆታን ለማስገባት በማሰብ ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ የዋጋ ግሽበቱን ይቀንሳል። በተመሳሳይ የአገር ውስጥ አቅርቦትን እንዲጨምር ያግዛል።

መሠረታዊ ፍጆታዎችን በባንኮች የገንዘብ አቅም ብቻ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ እጥረት አለ ያሉት ባለሙያው፤ ይህም የምርት እጥረት አስከትሏል። እጥረቱን ለመቀነስ ፍራንኮ ቫሉታው መፈቀዱ ሰዎች በእራሳቸው የውጭ ምንዛሬ አቅም መሠረታዊ ፍጆታዎችን እንዲያስገቡ ይረዳል ብለዋል።

ይህም የአገር ውስጥ ፍላጎትና አቅርቦትም አለመመጣጠን በማስተካከል፤ የዋጋ ንረትን ለማረጋጋትና የምርት እጥረትን ለመቅረፍ ጥሩ መፍትሄ ተደርጎ እንደሚታይም ነው አቶ ዘመዴነህ የተናገሩት።

ኅብረተሰቡ በየቀኑ የሚጠቀማቸው የምግብ ግብዓቶች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ እሙን ነው። ለዚህም የውጭ ምንዛሬ ሂደት ውስጥ ሳይገባ ምንጩ የታወቀ ዶላር በውጭ አገራት.....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70694

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
ሕዝብና መንግሥት በቅንጅት በሠሩባቸው አካባቢዎች በሸኔ ላይ ድል መገኘቱን የኦሮሚያ ክልል አስታወቀ
******
(ኢ ፕ ድ)
ሕዝቡ ተደራጅቶ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በተሠራባቸው አባቢዎች በሸኔ ላይ ሰፊ ድል መገኘቱንና በተቃራኒው የሕዝብ ድጋፍ በቀዘቀዘባቸው አካባቢዎች ክፍተት መታየቱን ኦሮሚያ ክልል መንግሥት አስታወቀ።

የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ፣ የክልሉ መንግሥት ከመጋቢት 30 እስከ ሚያዝያ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ያካሄደውን የ3ኛ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። ኃላፊው በመግለጫቸው እንዳሉት የሸኔን አረመኔነት በመረዳት ሕዝቡ ከመንግሥት ጎን በመቆም ቡድኑን ለማጥፋት በቆረጡ አካባቢዎች አንጸባራቂ ድሎች ተገኝተዋል።

የቡድኑን አደገኛነት ባለመረዳት ድጋፉ በተቀዛቀዘባቸው አካባቢዎች ክፍተት መታየቱንና በቀጣይ ሕዝቡን በማሳመንና በማንቀሳቀስ በሸኔ ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70677

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ