ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን አሰታወቀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ወደ ውጭ ከላካቸው ምርቶች ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ 11 ሸዶችን ይዞ ስራ ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን አሁን ላይ አምስት ኩባንያዎች በአቮካዶ ዘይት፣ በማር፣ ወተትና ቡና ምርቶች ላይ ተሰማርተው ለውጭ ገበያ በማቅረብ ገቢ በማስገኘት ላይ ናቸው።
በፓርኩ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መምሩ ሞኬ፤ ፓርኩ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ እስካሁን ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን ገልጸዋል።
ገቢው በፓርኩ በሚሰሩ ሁለት የአቮካዶ ዘይት አምራች ኩባንያዎች ከተላኩ ምርቶች የተገኘ መሆኑንም አብራርተዋል።
ኢንዱስትሪዎችን ከገበሬዎች እና ህብረት ስራ ማህበራት ጋር በቀጥታ በማስተሳሰር የጥሬ እቃ ግብዓትና የምርት የግብይት ሰንሰለት መፈጠር መቻሉንና በፓርኩ ውስጥ ከሚገኙ ሁለት ፋብሪካዎች ጋር በተፈጠረ የገበያ ትስስር ከ135 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይ ፓርኩ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት ትኩረት እንደሚያደርግ ገልጸው፤ እሴት ተጨምሮባቸው ወደ አገር የሚገቡ የቡና እና የወተት ምርቶችን ለማስቀረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተሟላ መሰረተ ልማት ያላቸውና አንድ መቶ ሃምሳ ኩባንያዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሼዶች ተዘጋጅተው ባለሃብቶችን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውንም ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል።
ለፋብሪካው ግብአት የሚሆኑ የግብርና ምርቶች በስፋት ስለሚመረቱ፤ በርካታ የሰው ሃይል እና አስተማማኝ ሰላም ያለበት አካባቢ በመሆኑ ባለሃብቶች በፓርኩ ተጨማሪ ስራዎችን እንዲጀምሩም ጥሪ አቅርበዋል።
በሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ስር የሚተዳደረው የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ወደ ስራ የገባው መጋቢት 4 ቀን 2013 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ወደ ውጭ ከላካቸው ምርቶች ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ።
የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ 11 ሸዶችን ይዞ ስራ ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን አሁን ላይ አምስት ኩባንያዎች በአቮካዶ ዘይት፣ በማር፣ ወተትና ቡና ምርቶች ላይ ተሰማርተው ለውጭ ገበያ በማቅረብ ገቢ በማስገኘት ላይ ናቸው።
በፓርኩ ዙሪያ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መምሩ ሞኬ፤ ፓርኩ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ እስካሁን ከ4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማስገኘቱን ገልጸዋል።
ገቢው በፓርኩ በሚሰሩ ሁለት የአቮካዶ ዘይት አምራች ኩባንያዎች ከተላኩ ምርቶች የተገኘ መሆኑንም አብራርተዋል።
ኢንዱስትሪዎችን ከገበሬዎች እና ህብረት ስራ ማህበራት ጋር በቀጥታ በማስተሳሰር የጥሬ እቃ ግብዓትና የምርት የግብይት ሰንሰለት መፈጠር መቻሉንና በፓርኩ ውስጥ ከሚገኙ ሁለት ፋብሪካዎች ጋር በተፈጠረ የገበያ ትስስር ከ135 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይ ፓርኩ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት ትኩረት እንደሚያደርግ ገልጸው፤ እሴት ተጨምሮባቸው ወደ አገር የሚገቡ የቡና እና የወተት ምርቶችን ለማስቀረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተሟላ መሰረተ ልማት ያላቸውና አንድ መቶ ሃምሳ ኩባንያዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ሼዶች ተዘጋጅተው ባለሃብቶችን በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውንም ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል።
ለፋብሪካው ግብአት የሚሆኑ የግብርና ምርቶች በስፋት ስለሚመረቱ፤ በርካታ የሰው ሃይል እና አስተማማኝ ሰላም ያለበት አካባቢ በመሆኑ ባለሃብቶች በፓርኩ ተጨማሪ ስራዎችን እንዲጀምሩም ጥሪ አቅርበዋል።
በሲዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ስር የሚተዳደረው የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ወደ ስራ የገባው መጋቢት 4 ቀን 2013 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል።
በአፋር በደረሰ የእሳት አደጋ መኖሪያ ቤቶች እና ሱቆች ከበርካታ ሀብት ጋር ወድመዋል
****************
(ኢ ፕ ድ)
ትናንት ከሰአት 11 ሰአት ገደማ በሰሙሮቢ ወረዳ ኮማሚ ቀበሌ በተነሳው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በርካታ ንብረት በመውደሙ ለህብረተሰቡ አስቸኳይ እርዳታ እንዲደረግ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀሰን ሀንድዬ ጥሪ አቀረቡ።
ለህብረተሰቡ አልባሳት፣ ምግብ ነክ ነገሮች፣ መጠለያና የመጠጥ ውሃ በአፋጣኝ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
የእሳት ቃጠሎው በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አድርሷል። 80 የንግድ ቤቶች ውስጥ የነበሩ 500 ሺህ ብር በላይ ሸቀጣ ሸቀጥና ጥሬ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን በ80 መኖሪያ ቤቶችም የነበሩ እቃዎችና ጥሬ ገንዘብ እያንዳንዳቸው 200 ሺህ ብር ገደማ መውደሙን ተናግረዋል።
በንብረት ላይ ማለትም የቤቶችን ግምት ሳያካትት በቤት ውስጥ የነበረ ሸቀጣ ሸቀጥ፣ እቃዎችና ጥሬ ብር የደረሰው አደጋ 56 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ እንደሆነ አቶ ሀሰን ገልጸዋል።
በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን ተናግረዋል።
በአቅራቢያቸው በሚገኙት ሸዋሮቢትም ሆነ ደብረብረሃን ከተሞች አንድም የእሳት አደጋ መከላከያ ባለመኖሩ ምክንያት ይህን ውድመት መቀነስ እንዳልተቻለም ገልጸዋል።
የአደጋው መነሻው በቀዳሚነት በቤንዚን ነው ተብሎ ታስቦ የነበረው ትክክል አልነበረም ያሉት አስተዳዳሪው በተደረገው ማጣራት የኤሌክትሪክ ንክኪ ተፈጥሮ ወደ ቤንዚን ቤት ማምራቱን አያይዘው ተናግረዋል።
በመጨረሻም ወረዳ አስተዳዳሪው በአሁኑ ወቅት የአደጋው ሰለባ የሆነው ህብረተሰባችን ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ በመሆኑ በአፋጣኝ ልንደርስለት ይገባል በማለት የድጋፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ከክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
ትናንት ከሰአት 11 ሰአት ገደማ በሰሙሮቢ ወረዳ ኮማሚ ቀበሌ በተነሳው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ በርካታ ንብረት በመውደሙ ለህብረተሰቡ አስቸኳይ እርዳታ እንዲደረግ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀሰን ሀንድዬ ጥሪ አቀረቡ።
ለህብረተሰቡ አልባሳት፣ ምግብ ነክ ነገሮች፣ መጠለያና የመጠጥ ውሃ በአፋጣኝ እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።
የእሳት ቃጠሎው በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አድርሷል። 80 የንግድ ቤቶች ውስጥ የነበሩ 500 ሺህ ብር በላይ ሸቀጣ ሸቀጥና ጥሬ ገንዘብ ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን በ80 መኖሪያ ቤቶችም የነበሩ እቃዎችና ጥሬ ገንዘብ እያንዳንዳቸው 200 ሺህ ብር ገደማ መውደሙን ተናግረዋል።
በንብረት ላይ ማለትም የቤቶችን ግምት ሳያካትት በቤት ውስጥ የነበረ ሸቀጣ ሸቀጥ፣ እቃዎችና ጥሬ ብር የደረሰው አደጋ 56 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ እንደሆነ አቶ ሀሰን ገልጸዋል።
በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን ተናግረዋል።
በአቅራቢያቸው በሚገኙት ሸዋሮቢትም ሆነ ደብረብረሃን ከተሞች አንድም የእሳት አደጋ መከላከያ ባለመኖሩ ምክንያት ይህን ውድመት መቀነስ እንዳልተቻለም ገልጸዋል።
የአደጋው መነሻው በቀዳሚነት በቤንዚን ነው ተብሎ ታስቦ የነበረው ትክክል አልነበረም ያሉት አስተዳዳሪው በተደረገው ማጣራት የኤሌክትሪክ ንክኪ ተፈጥሮ ወደ ቤንዚን ቤት ማምራቱን አያይዘው ተናግረዋል።
በመጨረሻም ወረዳ አስተዳዳሪው በአሁኑ ወቅት የአደጋው ሰለባ የሆነው ህብረተሰባችን ከፍተኛ የሆነ ችግር ውስጥ በመሆኑ በአፋጣኝ ልንደርስለት ይገባል በማለት የድጋፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ከክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
ለመተከል ዞን ተፈናቃዮች 5ኛው ዙር የሰብዓዊ ድጋፍ እየቀረበ ነው
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በመተከል ዞን በተለያዩ መጠለያ ጣቢዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች 5ኛው ዙር ሰብዓዊ ድጋፍ በመቅረብ ላይ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
በዞኑ በተፈጠረው አለመረጋጋት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚቀርበው ሰዓብዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ኮሚሽኑ ከአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከ42ሺ 3 መቶ ኩንታል በላይ የሰብዓዊ ድጋፍ በመጠየቅ በአሁኑ ሰዓት ለተፈናቃዮች እየቀረበ መሆኑን በኮሚሽኑ የምላሽ ፍላጎትና እርዳታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ዘውዱ ተሾመ አስታውቀዋል።
እስካሁን በዞኑ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የሚገኙ 282 ሺህ የሚደርሱ የህብረተሰብ ክፍሎች በየወረዳ ባለው መጠለያ ጣቢያ እንደሚገኙ ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በ5ኛው ዙር የሰብዓዊ ድጋፍ በዞኑ ስር በሚገኙ በሁሉም ወረዳዎች በመጓጓዝ ላይ መሆኑን ከዞኑ ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በመተከል ዞን በተለያዩ መጠለያ ጣቢዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች 5ኛው ዙር ሰብዓዊ ድጋፍ በመቅረብ ላይ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
በዞኑ በተፈጠረው አለመረጋጋት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚቀርበው ሰዓብዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ኮሚሽኑ ከአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር ከ42ሺ 3 መቶ ኩንታል በላይ የሰብዓዊ ድጋፍ በመጠየቅ በአሁኑ ሰዓት ለተፈናቃዮች እየቀረበ መሆኑን በኮሚሽኑ የምላሽ ፍላጎትና እርዳታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ዘውዱ ተሾመ አስታውቀዋል።
እስካሁን በዞኑ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የሚገኙ 282 ሺህ የሚደርሱ የህብረተሰብ ክፍሎች በየወረዳ ባለው መጠለያ ጣቢያ እንደሚገኙ ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በ5ኛው ዙር የሰብዓዊ ድጋፍ በዞኑ ስር በሚገኙ በሁሉም ወረዳዎች በመጓጓዝ ላይ መሆኑን ከዞኑ ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አትክልትና ፍራፍሬን ለህብረተሰቡ በቀጥታ ለማቅረብ እየሰራን ነው -አርሶ አደሮች
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አትክልትና ፍራፍሬን ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በቀጥታ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑን በከተማ ግብርና የተሰማሩ የአዳማ ከተማ አርሶ አደሮች ገለጹ።
አርሶ አደር ነገዎ ወርጂ እንደገለጹት በ12 ሄክታር መሬት ላይ ቃሪያ፣ ሽንኩርትና ቲማቲም እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ምርቱ እየደረሰ በመሆኑ ደላላ ጣልቃ ሳይገባ ለሸማቹ ህብረተሰብ በቀጥታ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጭዎቹ 10 ቀናት ውስጥ የቲማትምና የቃሪያ ምርት ለገበያ ማቅረብ እንደሚጀምሩ አመላክተዋል ።
ምርታቸውን ለምግብነት ከመጠቀም አልፈው ለህብረተሰቡ በቀጥታ በማቅረብ የዋጋ ንረቱን ለማቃለል የመሸጫ ቦታ ከመስተዳድሩ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸዋል።
“ወደ ከተማ ከተካለልን ወዲህ ብዙ እገዛ ተደርጎልን በከተማ ግብርና ተሰማርተን የጓሮ አትክልት እያለማን ነው” ያሉት ደግሞ የአዳማ ከተማ መልካ ሂዳ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ለገሰ ጉደታ ናቸው።
በአሁኑ ወቅት ለራሳቸው ለምግብነትም ሆነ ለከተማው ህብረተሰብ ለማቅረብ ቃሪያና ቲማቲም እንዲሁም ፓፓያ እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
ቀደም ብሎ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ያመርቱ የነበረውን አሁን በዓመት ሶስት ጊዜ እያመረቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ምርታቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየተጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ከአትክልት በተጨማሪ በበጋ ስንዴ ልማት ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
የአዳማ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ሂርጶ በበኩላቸው “በአሁኑ ወቅት በመንግስት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በከተማዋ ከ627 ሄክታር በላይ መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ስንዴን በመስኖ እያለማን ነው” ብለዋል።
በተጨማሪም 10 ትምህርት ቤቶች ላይ በ6 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑንም አቶ ጌታቸው መናገራቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።
“ምግባችን ከጓሮአችን” በሚል መሪ ሃሳብ አብዛኛው የከተማው ነዋሪ ቶሎ የሚደርስ አትክትልና ፍራፍሬ እንዲያለማ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አትክልትና ፍራፍሬን ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በቀጥታ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑን በከተማ ግብርና የተሰማሩ የአዳማ ከተማ አርሶ አደሮች ገለጹ።
አርሶ አደር ነገዎ ወርጂ እንደገለጹት በ12 ሄክታር መሬት ላይ ቃሪያ፣ ሽንኩርትና ቲማቲም እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን ላይ ምርቱ እየደረሰ በመሆኑ ደላላ ጣልቃ ሳይገባ ለሸማቹ ህብረተሰብ በቀጥታ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
በመጭዎቹ 10 ቀናት ውስጥ የቲማትምና የቃሪያ ምርት ለገበያ ማቅረብ እንደሚጀምሩ አመላክተዋል ።
ምርታቸውን ለምግብነት ከመጠቀም አልፈው ለህብረተሰቡ በቀጥታ በማቅረብ የዋጋ ንረቱን ለማቃለል የመሸጫ ቦታ ከመስተዳድሩ እየጠየቁ መሆኑን ገልጸዋል።
“ወደ ከተማ ከተካለልን ወዲህ ብዙ እገዛ ተደርጎልን በከተማ ግብርና ተሰማርተን የጓሮ አትክልት እያለማን ነው” ያሉት ደግሞ የአዳማ ከተማ መልካ ሂዳ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ለገሰ ጉደታ ናቸው።
በአሁኑ ወቅት ለራሳቸው ለምግብነትም ሆነ ለከተማው ህብረተሰብ ለማቅረብ ቃሪያና ቲማቲም እንዲሁም ፓፓያ እያለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
ቀደም ብሎ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ያመርቱ የነበረውን አሁን በዓመት ሶስት ጊዜ እያመረቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ምርታቸውን በቀጥታ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገበያን ለማረጋጋት እየተጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሩ ከአትክልት በተጨማሪ በበጋ ስንዴ ልማት ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
የአዳማ ከተማ ግብርና ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ሂርጶ በበኩላቸው “በአሁኑ ወቅት በመንግስት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በከተማዋ ከ627 ሄክታር በላይ መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ስንዴን በመስኖ እያለማን ነው” ብለዋል።
በተጨማሪም 10 ትምህርት ቤቶች ላይ በ6 ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑንም አቶ ጌታቸው መናገራቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።
“ምግባችን ከጓሮአችን” በሚል መሪ ሃሳብ አብዛኛው የከተማው ነዋሪ ቶሎ የሚደርስ አትክትልና ፍራፍሬ እንዲያለማ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የሆቴልና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ማዕከላት በዘርፉ ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው ተጠቆመ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በሆቴልና ቱሪዝም ሙያ ስልጠና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያበረታታ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከጀርመን ልማት ትብብር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መድረክ ሚኒስትር ዴኤታ በከር ሻሌ (ዶ/ር) በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ትብብርን አጠናክሮ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት ምቹ ሥራ መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪው ባለድርሻ አካላት ሥርዓተ ስልጠናውን በጋራ በመቅረፅ ፣ በማሰልጠንና በመመዘን ጭምር ከሆቴልና ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ማሰልጠኛ ማዕከላት ጋር ትኩረት ሰጥተው በጋራ መሥራት አለባቸው።
በቀጣይም በጋራ በመሥራት የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፉን ማሳደግ እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
የጀርመን መንግስት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እያደረገ ካለው ድጋፍ ባሻገር ይህንን ውይይት በማዘጋጀቱ አመስግነዋል፡፡
የጀርመን ትብብር ልማትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ቤንጃሚን ሀከር ኢትዮጵያ በቱሪዝም ብዙ ሀብት ያላት በመሆኑ ዘርፉን በብቁ ባለሞያዎች በማሳደግ ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻል የጀርመን መንግስት ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ቱሪዝም ኢንስቲትዩት፣ ኃይሌ ሪዞርት፣ሃያት ሪጀንሲ፣ ኩሪፍቱ ሪዞርት፣ ኢትዮጵያ ሼፍ ማህበር፣ ኢትዮጵያ የባህልና ቱሪዝም ጋዜጠኞች ማህበር ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በሆቴልና ቱሪዝም ሙያ ስልጠና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ የሚያበረታታ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከጀርመን ልማት ትብብር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው መድረክ ሚኒስትር ዴኤታ በከር ሻሌ (ዶ/ር) በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ትብብርን አጠናክሮ ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት ምቹ ሥራ መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪው ባለድርሻ አካላት ሥርዓተ ስልጠናውን በጋራ በመቅረፅ ፣ በማሰልጠንና በመመዘን ጭምር ከሆቴልና ቱሪዝም ኢንስቲትዩት ማሰልጠኛ ማዕከላት ጋር ትኩረት ሰጥተው በጋራ መሥራት አለባቸው።
በቀጣይም በጋራ በመሥራት የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፉን ማሳደግ እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
የጀርመን መንግስት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እያደረገ ካለው ድጋፍ ባሻገር ይህንን ውይይት በማዘጋጀቱ አመስግነዋል፡፡
የጀርመን ትብብር ልማትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ቤንጃሚን ሀከር ኢትዮጵያ በቱሪዝም ብዙ ሀብት ያላት በመሆኑ ዘርፉን በብቁ ባለሞያዎች በማሳደግ ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻል የጀርመን መንግስት ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ቱሪዝም ኢንስቲትዩት፣ ኃይሌ ሪዞርት፣ሃያት ሪጀንሲ፣ ኩሪፍቱ ሪዞርት፣ ኢትዮጵያ ሼፍ ማህበር፣ ኢትዮጵያ የባህልና ቱሪዝም ጋዜጠኞች ማህበር ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️