Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
40K photos
302 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
አምባሳደሮች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ጎበኙ
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በቅርቡ ሹመት ለተሰጣቸው አምባሳደሮች ቦሌ ለሚ፣ ቂሊንጦና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አሰጎበኘ።

በአለም ሀገራት የተሾሙ አምባሳደሮች በኢትዮጵያ በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ ዝርዝር የኢንቨስትመንት አማራጮችን ተመልክተው በሚሄዱባቸው የአለም ሀገራት በማስተዋወቅ ኢንቨስትመንትን ወደ ኢትዮጵያ ለመሳብ እንጂችሉ የተደረገ ጉብኝ ነው ተብሏል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ፣ አምባሳደሮች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለአለም ለማስተዋወቅ መስራት አለባቸው ብለዋል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ የስራ እንቅስቃሴዎችን፣ የኢንቨስትመንት አማራጮችንና የወደፊት ስራዎች ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ቀርቧል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለአለም ለማስተዋወቅ እንደሚረዳቸው አምባሳደሮቹ ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
የኤችአር 6600 እና ኤስ 3199 ረቂቅ ህጎችን በመቃወም በቤልጂየም የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ
*************
(ኢ ፕ ድ)

የኤችአር 6600 እና ኤስ 3199 ረቂቅ ህጎች በመቃወም በቤልጂየም የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ።

ሰልፈኞቹ የአሜሪካ መንግስትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከኢትዮጵያ ጎን እንሲሰለፉም ጠይቀዋል።

ኢትዮጵያውያኑ የአሸባሪው የህወሃት ቡድን በአፋር እና የአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል በመገንዘብ የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሴኔት አባላት ያረቀቋቸውን ህጎች እንዲሰርዙም የሚጠይቁ መፈክሮችን አሰምተዋል።

ሰልፈኞቹ ከአሜሪካ መንግስት በተጨማሪም ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት በመሬት ላይ ያለውን ሃቅ በመገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጎን እንዲሰለፉም ጥሪ አቅርበዋል።

በቤልጂየም የተካሄደው ሰልፍ አስተባባሪ አቶ ኤፍሬም ምትኩ እንዲህ ያሉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ለኢቲቪ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለተለያዩ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት የኢፍጣር ዝግጅት አደረጉ
*****************
(ኢ ፕ ድ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ለተለያዩ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት የኢፍጣር ዝግጅት ማድረጋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታወቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ማምሻውን ለተለያዩ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት የኢፍጣር ዝግጅት አድርገዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
ከ345 በላይ ዓለም-አቀፍ ወደቦችን መዳረሻ በማድረግ የገቢ ጭነቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚጓጓዙ ተገለጸ
*****
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ከ345 በላይ ዓለም-አቀፍ ወደቦችን መዳረሻ በማድረግ የኢትዮጵያን ገቢ ጭነቶች እያጓጓዘ እንደሚገኝ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ከኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ የስራ ኃላፊዎች ጋር ዘርፉን ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ እንደገለፁት ድርጅቱ ከ345 በላይ ዓለም-አቀፍ ወደቦችን መዳረሻ አድርጎ የኢትዮጵያን ገቢ ጭነቶች እያጓጓዘ ይገኛል።

ዘርፉ የሚጠይቀውን የሰለጠነ የሰው ኃይል በማሟላትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተግባራዊ በማድረግ ከዓለም-አቀፍ ኩባንያዎች ጋር ተወዳዳሪ ሆኖ እየሰራና ትርፋማነቱን አስጠብቆ እየሄደ ነው ብለዋል፡፡

የድርጅቱ ካፒታል 20 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገለጹት አቶ ሮባ ካፒታሉን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት የገቢና ወጪ ጭነቶችን በፍጥነት በብዛትና ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲጓጓዙ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ያሉት አቶ ሮባ አገልግሎቱን የበለጠ እናሳድገዋለን ብለዋል፡፡

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ ዋና ዳይሬክተር አብዲ ዘነበ (ዶ/ር)፣ ውይይት ሁለቱ ድርጅቶች ይበልጥ ተቀራርበው ለመስራትና አገልግሎቱን ከዚህ የበለጠ ለማስፋት ትልቅ ፋይዳ አለው። የተጀመሩ መልካም ስራዎቸ እየጎለበቱ መሄድ እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
”ያልተረጋጋ የፖለቲካ ሁኔታን ንግግር እንጂ ጦርነት አይፈታውም"
– አቶ ሞገስ ባልቻ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር
********************
(ኢ ፕ ድ)
በየትኛውም የዓለም ክፍል ያለውን ያልተረጋጋ የፖለቲካ ሁኔታ ንግግር እንጂ ጦርነት አይፈታውም ሲሉ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር አቶ ሞገስ ባልቻ ገለጹ፡፡ አገራዊ ምክክሩ አገራዊ ተስፋ የሚሰጥ እንደሆነም ጠቅሰዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ዘርፍ ኃላፊ ሚኒስትር አቶ ሞገስ ባልቻ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደጠቀሱት፤ በየትኛውም የዓለም አካባቢ ያለውን ያልተረጋጋ የፖለቲካ ሁኔታ የሚፈታው በጦርነት ሳይሆን በውይይት መድረክ ነው፡፡

ከጦርነት ይልቅ ንግግር ለመግባባት አዎንታዊ ሚና እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለያየ ማህበራዊ ትስስር ውስጥ ያለ በመሆኑ መለያየት እንደማይችል፤ መፍትሄው ደግሞ ተነጋግሮ አንድ መሆንና በተግባቦት ችግሮችን መፍታት የሚቻልበትን ሁኔታ መፍጠር ነው ብለዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ አገራዊ ምክክሩ ጠቃሚ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ የማያግባቡና ልዩነት ላይ ያሉ ጉዳዮችን...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70741

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ክልሉ የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ የሦስት ወራት ዕቅድ አዘጋጅቶ መተግበር መጀመሩን ገለጸ
******************
(ኢ ፕ ድ)

አንገብጋቢ የሕዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ የሦስት ወራት ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ መግባቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አስታወቀ፡፡

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይስሀቅ አብድልቃድር ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ክልሉ በብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ በተቀመጡ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከሕዝቡ ጋር ውይይት በማድረግ የሕዝቡን አንገብጋቢ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የሦስት ወራት ዕቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡

ፓርቲው በአስቀመጣቸው አቅጣጫዎች ዙሪያ ከሕዝብ ውይይት መደረጉን አመልክተው፤ ፓርቲው ያስቀመጣቸውና ሕዝብ ያነሳቸው ጥያቄዎችን ለመመለስ ሕዝቡ፣ መንግሥትና ባለድርሻ አካላት እጅና ጓንት ሆነው ዕቅዱን ለመፈጸም ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል፡፡

ክልሉ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚካሄድበት ከመሆኑም አንጻር የተለያዩ ጸረ ሰላም ኃይሎች ፍላጎታቸውን የሚያንጸባርቁበት መሆኑን አመልክተው፤ ሸኔና በርታ ነፃ አውጪ የተሰኘው ቡድንና ሌሎች ጸንፈኞች ኃይሎች...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70742

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
በዘንድሮው ክረምት በደን ለመሸፈን ከታቀደው ከ448 ሺ በላይ ሄክታር መሬት መለየቱ ተጠቆመ
*******************
(ኢ ፕ ድ)

በመጪው ክረምት በደን ለመሸፈን ከታቀደው 800ሺ ሄክታር መሬት ውስጥ 448 ሺ 468 ሄክታር መሬት ለችግኝ ተከላ መለየቱን የኢትዮጵያ ደን ልማት አስታወቀ፡፡

እስካሁን ባለው መረጃ ሁለት ነጥብ 738 ቢሊዮን የደን ችግኝ ተፈልቶ መዘጋጀቱ ተጠቁሟል፡፡

በኢትዮጵያ ደን ልማት የደን ልማት ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ቢተው ሽባባው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሚቀጥለው ክረምት በደን ይሸፈናል ተብሎ ከታቀደው ስምንት መቶ ሺ ሄክታር መሬት መካከል እስካሁን በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች 448 ሺ 468 ሄክታር መሬት ለችግኝ ተከላ ተለይቷል።፡

በዚህ ዓመት እንደ አገር የደንና የአገሮ ፎረስተሪው ችግኝ ተዳምሮ ስድስት ቢሊዮን ችግኝ ተፈልቶ ይተከላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በደን ችግኝ በኩል ይለማል ተብሎ በዕቅድ የተያዘው አራት ቢሊዮን ችግኝ ሲሆን እስካሁን ባለው መረጃ ሁለት ነጥብ 738 ቢሊዮን ችግኝ ተፈልቶ ለተከላ...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70772

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ