Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
303 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በላሊይበላ ገዳም ለሚተዳደሩ አገልጋዮችና ለአከባቢው ነዋሪዎች ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሰሜን ወሎ፣ የደቡብ ወሎና የከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ በቤተክህነት በሰጡት መግለጫ፣ በሮሃ ቅዱስ ላሊይበላ ገዳም የሚተዳደሩ አገልጋዮችና የአከባቢው ነዋሪዎች ችግር ላይ መውደቃቸውን አሰታወቁ።
በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።
ከባለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በተከሰተው የኮሮና ወረርሽኝና በጦርነቱ ምክንያት ከቱሪዝም የሚገኘው ገቢ ባለመኖሩ ምክንያት ለችግር በመጋለጣቸው የቱሪዝም ገቢው እስኪጀመር ድረስ ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።
ካህናት፣ የአብነት ተማሪዎች፣ አረጋውያንና መነኮሳት እንዲሁም ወላጅ አልበ ህፃናትን ጨምሮ ከ10 ሺህ በላይ በቀጥታና በተዘዋዋሪ በገዳሙ የቱሪዝም ገቢ የሚተዳደሩ እንደሆኑ ተናግረዋል።
የአከባቢው ህብረተሰብና የገዳሙ አገልጋዮች ከሐምሌ ጀምሮ በሰሜን ወሎ እና በዋግኽምራ በደረሰው ውድመትና ከቱሪስት ገቢ የሚገኘው በመቋረጡ ተደራራቢ ችግር ውስጥ መሆኑንም ገልፀዋል።
በከባቢው በጦርነቱ የወደሙ የውሃ የመብራት የህክምና እና የሌሎች መሠረተ ልማቶች የቅርሱ ጠባቂዎች መሰደድ ምክንያት እየሆነ በመሆኑ የማይዳሰስ ቅርስ የሆነውን መንፈሳዊ አገልግሎት በማየት ይመጡ የነበሩ ቱሪስቶች አየቀሩ መሆኑ ችግሩን አሳሳቢ አድርጎታል።
ከ1971 ዓ.ም ጀምሮ የዓለም ቅርስ ሆኖ ከተመዘገበ ጊዜ ጀምሮ አገልግሎት አየሰጠ የሚገኘው ገዳም ነው።
በኃይሉ አበራ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
አምባሳደሮች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ጎበኙ
****
(ኢ ፕ ድ)
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በቅርቡ ሹመት ለተሰጣቸው አምባሳደሮች ቦሌ ለሚ፣ ቂሊንጦና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች አሰጎበኘ።

በአለም ሀገራት የተሾሙ አምባሳደሮች በኢትዮጵያ በተለይም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ ዝርዝር የኢንቨስትመንት አማራጮችን ተመልክተው በሚሄዱባቸው የአለም ሀገራት በማስተዋወቅ ኢንቨስትመንትን ወደ ኢትዮጵያ ለመሳብ እንጂችሉ የተደረገ ጉብኝ ነው ተብሏል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ፣ አምባሳደሮች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለአለም ለማስተዋወቅ መስራት አለባቸው ብለዋል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ የስራ እንቅስቃሴዎችን፣ የኢንቨስትመንት አማራጮችንና የወደፊት ስራዎች ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ቀርቧል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለአለም ለማስተዋወቅ እንደሚረዳቸው አምባሳደሮቹ ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
የኤችአር 6600 እና ኤስ 3199 ረቂቅ ህጎችን በመቃወም በቤልጂየም የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ
*************
(ኢ ፕ ድ)

የኤችአር 6600 እና ኤስ 3199 ረቂቅ ህጎች በመቃወም በቤልጂየም የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ።

ሰልፈኞቹ የአሜሪካ መንግስትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከኢትዮጵያ ጎን እንሲሰለፉም ጠይቀዋል።

ኢትዮጵያውያኑ የአሸባሪው የህወሃት ቡድን በአፋር እና የአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል በመገንዘብ የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሴኔት አባላት ያረቀቋቸውን ህጎች እንዲሰርዙም የሚጠይቁ መፈክሮችን አሰምተዋል።

ሰልፈኞቹ ከአሜሪካ መንግስት በተጨማሪም ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት በመሬት ላይ ያለውን ሃቅ በመገንዘብ ከኢትዮጵያውያን ጎን እንዲሰለፉም ጥሪ አቅርበዋል።

በቤልጂየም የተካሄደው ሰልፍ አስተባባሪ አቶ ኤፍሬም ምትኩ እንዲህ ያሉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ለኢቲቪ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለተለያዩ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት የኢፍጣር ዝግጅት አደረጉ
*****************
(ኢ ፕ ድ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ለተለያዩ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት የኢፍጣር ዝግጅት ማድረጋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታወቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ማምሻውን ለተለያዩ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት የኢፍጣር ዝግጅት አድርገዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ
ከ345 በላይ ዓለም-አቀፍ ወደቦችን መዳረሻ በማድረግ የገቢ ጭነቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚጓጓዙ ተገለጸ
*****
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ከ345 በላይ ዓለም-አቀፍ ወደቦችን መዳረሻ በማድረግ የኢትዮጵያን ገቢ ጭነቶች እያጓጓዘ እንደሚገኝ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ከኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ የስራ ኃላፊዎች ጋር ዘርፉን ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ እንደገለፁት ድርጅቱ ከ345 በላይ ዓለም-አቀፍ ወደቦችን መዳረሻ አድርጎ የኢትዮጵያን ገቢ ጭነቶች እያጓጓዘ ይገኛል።

ዘርፉ የሚጠይቀውን የሰለጠነ የሰው ኃይል በማሟላትና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተግባራዊ በማድረግ ከዓለም-አቀፍ ኩባንያዎች ጋር ተወዳዳሪ ሆኖ እየሰራና ትርፋማነቱን አስጠብቆ እየሄደ ነው ብለዋል፡፡

የድርጅቱ ካፒታል 20 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገለጹት አቶ ሮባ ካፒታሉን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት የገቢና ወጪ ጭነቶችን በፍጥነት በብዛትና ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲጓጓዙ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ያሉት አቶ ሮባ አገልግሎቱን የበለጠ እናሳድገዋለን ብለዋል፡፡

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ ዋና ዳይሬክተር አብዲ ዘነበ (ዶ/ር)፣ ውይይት ሁለቱ ድርጅቶች ይበልጥ ተቀራርበው ለመስራትና አገልግሎቱን ከዚህ የበለጠ ለማስፋት ትልቅ ፋይዳ አለው። የተጀመሩ መልካም ስራዎቸ እየጎለበቱ መሄድ እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ