ወልድያ ዩኒቨርሰቲ ለዋግኽምራ ተፈናቃዮች ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ
*************
(ኢ ፕ ድ)
የወልድያ ዩኒቨርሰቲ ለዋግኽምራ ተፈናቃዮች ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አደረገ፡፡
ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሰቆጣ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ግምቱ ከ አንድ ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ 300 ኩንታል የስንዴ ዱቄት ድጋፍ ማድረጋቸውን የዩኒቨርስቲው ምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሰለሞን አበጋዝ ገልፀዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት አቶ ሄኖክ ነጋሽ የወልድያ ዩኒቨርስቲ በርካታ ችግሮች እያለበት ችግራችን አሳስቦት ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፣ ዩኒቨርስቲው የጀመረውን ድጋፎች አጠናክሮ እንዲቀጥልና ሌሎች ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን ከዞኑ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*************
(ኢ ፕ ድ)
የወልድያ ዩኒቨርሰቲ ለዋግኽምራ ተፈናቃዮች ከ1.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዓይነት ድጋፍ አደረገ፡፡
ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሰቆጣ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ግምቱ ከ አንድ ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ 300 ኩንታል የስንዴ ዱቄት ድጋፍ ማድረጋቸውን የዩኒቨርስቲው ምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ሰለሞን አበጋዝ ገልፀዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት አቶ ሄኖክ ነጋሽ የወልድያ ዩኒቨርስቲ በርካታ ችግሮች እያለበት ችግራችን አሳስቦት ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፣ ዩኒቨርስቲው የጀመረውን ድጋፎች አጠናክሮ እንዲቀጥልና ሌሎች ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን ከዞኑ ኮሙዩኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ የሚገቡ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ለስግብግብ ግለሰቦች መጠቀሚያ እንዳይሆን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል
******************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችና አገልግሎቶችን ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ (ፍራንኮ ቫሉታ) በጉምሩክ በኩል እንዲገቡ ሲደረግ የስግብግብ ግለሰቦች መጠቀሚያ እንዳይሆን መጠንቀቅ እንደሚገባ የምጣኔ ሃብት ምሁሩ ኢየሱስወርቅ ዛፉ ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ያለ ውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገቡ መደረጉ ወቅቱን የጠበቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2017/18 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው 10 አይነት እቃዎች በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡
በፍራንኮ ቫሉታ የተፈቀዱ እቃዎችና አገልግሎቶች በጉምሩክ በኩል እንዲገቡ ሲደረግ የስግብግብ ግለሰቦች መጠቀሚያ እንዳይሆን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የፍራንኮ ቫሉታ ተጠቃሚዎች ለመንግስት የሚከፍሉትን ግብር ለመቀነስ በማሰብ የተጭበረበረ የሰነድ ማስረጃ ይዘው ሊመጡ የሚችልበት እድል ሊኖር ይችላል ሲሉም ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በሰው ችግር ለመበልጸግና የራስን ጥቅም ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት እየተባባሰ በመምጣቱ የመንግስትን የመቆጣጠር ሃላፊነት አብዝቶበታል ብለዋል፡፡
በመሆኑም መጥፎ ነገሮችን መቆጣጠር ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁላችንም ከመጥፎ ድርጉት በመቆጠብ ለውሳኔ ውጤታማነት መትጋት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ምንም እንኳን የእቃዎቹ አማካኝ የዋጋ መጠን በጉምሩክ ኮሚሽንና በባለሙያዎቹ የሚታወቅ ቢሆንም የህዝብና የአገር ጉዳይ የማያስጨንቃቸው ሊኖሩ ስለሚችሉ በጋራ መቆጣጠር ይገባል ብለዋል፡፡
መድሃኒት፣ ነዳጅና ማዳበሪያን ጨምሮ በፍራንኮ ቫሉታ የገቡት አስሩ እቃዎች ከአጠቃላይ የገቢ ንግዱ 41 በመቶ ወይም 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር የሚሸፍን ነበር፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠርና የውጭ አገር የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ለጠየቁት የፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ ምላሽ ለመስጠት መወሰኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡
በፋይናንስ ዘርፍ ከ60 አመት በላይ በማገልግል የካበተ ልምድ ያላቸው የምጣኔ ሃብት ምሁሩ እየሱስወርቅ ዛፉ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፍቃድ /ፍራንኮ ቫሉታ ማስገባት በሌሎች አገሮችም የተለመደ አሰራር መሆኑን ይናገራሉ።
መንግስት ለሀገር አስፈላጊ የሆኑ እቃዎችና አገልግሎቶችን ከውጭ ማምጣት የማይችል ከሆነና የግድ መግባት ካለባቸው ፍራንኮ ቫሉታ የሚፈቀድ መሆኑን ጠቁመዋል።
ፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ ተገዝተው የሚገቡ እቃዎችና አገልግሎቶችን በመንግስት አቅም ብቻ መሸፈን ሳይቻል ሲቀር የሚደረግ ውሳኔ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የሀገር ውስጥ ግጭትና ከአሸባሪው ህወሀት ጋር የነበረው ጦርነት፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ያልተመጣጠነ የወጭና ገቢ ንግድ በመፍጠር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ፈትኖታል ብለዋል፡፡
ዘይት፣ ስኳር፣ ሩዝና ወተት የመሰሉ ምርቶች በጉምሩክ በኩል በቀጥታ እንዲገቡ ማድረጉ የእለት ጉርስን ከማሟላትም ባለፈ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ያግዛል ብለዋል፡፡
ለአብነት የተቋቋሙት የዘይት ፋብሪካዎች ጥሬ እቃ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገቡ ካልተፈቀደ ዘይት ማምረት አይችሉም፤የኑሮ ውደነት እየተባባሰ ረሃብ እንዲከሰት ያደርጋል ብለዋል፡፡
በመሆኑም መንግስት አሁን አገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ አስገብቶ ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ትክክለኛና ወቅቱን የዋጀ ውሳኔ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
******************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችና አገልግሎቶችን ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ (ፍራንኮ ቫሉታ) በጉምሩክ በኩል እንዲገቡ ሲደረግ የስግብግብ ግለሰቦች መጠቀሚያ እንዳይሆን መጠንቀቅ እንደሚገባ የምጣኔ ሃብት ምሁሩ ኢየሱስወርቅ ዛፉ ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ያለ ውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገቡ መደረጉ ወቅቱን የጠበቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ2017/18 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ያወጣው ሪፖርት እንደሚያሳየው 10 አይነት እቃዎች በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡
በፍራንኮ ቫሉታ የተፈቀዱ እቃዎችና አገልግሎቶች በጉምሩክ በኩል እንዲገቡ ሲደረግ የስግብግብ ግለሰቦች መጠቀሚያ እንዳይሆን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የፍራንኮ ቫሉታ ተጠቃሚዎች ለመንግስት የሚከፍሉትን ግብር ለመቀነስ በማሰብ የተጭበረበረ የሰነድ ማስረጃ ይዘው ሊመጡ የሚችልበት እድል ሊኖር ይችላል ሲሉም ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በሰው ችግር ለመበልጸግና የራስን ጥቅም ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት እየተባባሰ በመምጣቱ የመንግስትን የመቆጣጠር ሃላፊነት አብዝቶበታል ብለዋል፡፡
በመሆኑም መጥፎ ነገሮችን መቆጣጠር ለመንግስት ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁላችንም ከመጥፎ ድርጉት በመቆጠብ ለውሳኔ ውጤታማነት መትጋት ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ምንም እንኳን የእቃዎቹ አማካኝ የዋጋ መጠን በጉምሩክ ኮሚሽንና በባለሙያዎቹ የሚታወቅ ቢሆንም የህዝብና የአገር ጉዳይ የማያስጨንቃቸው ሊኖሩ ስለሚችሉ በጋራ መቆጣጠር ይገባል ብለዋል፡፡
መድሃኒት፣ ነዳጅና ማዳበሪያን ጨምሮ በፍራንኮ ቫሉታ የገቡት አስሩ እቃዎች ከአጠቃላይ የገቢ ንግዱ 41 በመቶ ወይም 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር የሚሸፍን ነበር፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠርና የውጭ አገር የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ለጠየቁት የፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ ምላሽ ለመስጠት መወሰኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡
በፋይናንስ ዘርፍ ከ60 አመት በላይ በማገልግል የካበተ ልምድ ያላቸው የምጣኔ ሃብት ምሁሩ እየሱስወርቅ ዛፉ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፍቃድ /ፍራንኮ ቫሉታ ማስገባት በሌሎች አገሮችም የተለመደ አሰራር መሆኑን ይናገራሉ።
መንግስት ለሀገር አስፈላጊ የሆኑ እቃዎችና አገልግሎቶችን ከውጭ ማምጣት የማይችል ከሆነና የግድ መግባት ካለባቸው ፍራንኮ ቫሉታ የሚፈቀድ መሆኑን ጠቁመዋል።
ፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ ተገዝተው የሚገቡ እቃዎችና አገልግሎቶችን በመንግስት አቅም ብቻ መሸፈን ሳይቻል ሲቀር የሚደረግ ውሳኔ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የሀገር ውስጥ ግጭትና ከአሸባሪው ህወሀት ጋር የነበረው ጦርነት፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና ያልተመጣጠነ የወጭና ገቢ ንግድ በመፍጠር የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ፈትኖታል ብለዋል፡፡
ዘይት፣ ስኳር፣ ሩዝና ወተት የመሰሉ ምርቶች በጉምሩክ በኩል በቀጥታ እንዲገቡ ማድረጉ የእለት ጉርስን ከማሟላትም ባለፈ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማሳለጥ ያግዛል ብለዋል፡፡
ለአብነት የተቋቋሙት የዘይት ፋብሪካዎች ጥሬ እቃ ያለምንም የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ እንዲገቡ ካልተፈቀደ ዘይት ማምረት አይችሉም፤የኑሮ ውደነት እየተባባሰ ረሃብ እንዲከሰት ያደርጋል ብለዋል፡፡
በመሆኑም መንግስት አሁን አገሪቱ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ አስገብቶ ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ትክክለኛና ወቅቱን የዋጀ ውሳኔ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ጊቤ 3 የኃይል ማመንጨት ጣቢያ ከአምስት ሺህ 230 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ አመንጭቷል
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት አምስት ሺህ 230 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ማምረት መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰታወቀ።
የኃይል የማመንጨት አፈፃፀሙ ከዕቅድ በመቶ ብልጫ ያለው አፈፃፀም አስመዝግቧል፡፡
የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለፁት በ2014 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4 ሺህ 900 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት አቅዶ 5 ሺህ 230 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በማምረት የዕቅዱን 4 በመቶ ብልጫ አስመዝግቧል፡፡
ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የ19 በመቶ ብልጫ እንዳለው አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል፡፡
በመስከረም ወር የማመንጫ ዩኒቶችን ሊያስቆሙ የሚችሉ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች መገዛታቸው ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ኃይል እንዲያመነጭ አስችሏል ብለዋል።
የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ንጉሴ ማሙሻ በበኩላቸው ለዩኒቶቹ ተከታታይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች በወቅቱ መከናወናቸው የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ኃይል እንዲያመርት እገዛ አድርጓል ብለዋል፡፡
ተቋሙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚያቅዳቸውን ዕቅዶች ከግብ እንዲያደርስ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ግዢ ሊፋጠንና የስታፍ ፕላኑን የሚመጥን የሰው ኃይል እንዲሟላ ኃላፊዎቹ ጠይቀዋል፡፡
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ከ40 እስከ 50 በመቶ እየሸፈነ የሚገኝና ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል አስተዋፅኦው የጎላ እንደነበር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የጊቤ 3 የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት አምስት ሺህ 230 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ማምረት መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሰታወቀ።
የኃይል የማመንጨት አፈፃፀሙ ከዕቅድ በመቶ ብልጫ ያለው አፈፃፀም አስመዝግቧል፡፡
የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለፁት በ2014 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4 ሺህ 900 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት አቅዶ 5 ሺህ 230 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ በማምረት የዕቅዱን 4 በመቶ ብልጫ አስመዝግቧል፡፡
ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የ19 በመቶ ብልጫ እንዳለው አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል፡፡
በመስከረም ወር የማመንጫ ዩኒቶችን ሊያስቆሙ የሚችሉ ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች መገዛታቸው ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ኃይል እንዲያመነጭ አስችሏል ብለዋል።
የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ንጉሴ ማሙሻ በበኩላቸው ለዩኒቶቹ ተከታታይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች በወቅቱ መከናወናቸው የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ኃይል እንዲያመርት እገዛ አድርጓል ብለዋል፡፡
ተቋሙ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚያቅዳቸውን ዕቅዶች ከግብ እንዲያደርስ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ግዢ ሊፋጠንና የስታፍ ፕላኑን የሚመጥን የሰው ኃይል እንዲሟላ ኃላፊዎቹ ጠይቀዋል፡፡
የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ፍላጎት ከ40 እስከ 50 በመቶ እየሸፈነ የሚገኝና ኢኮኖሚውን በመደገፍ በኩል አስተዋፅኦው የጎላ እንደነበር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
በህገ-ወጥ ንግድ ተሰማርተው በተገኙ ከ33 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን ቢሮው አሰታወቀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በህገ-ወጥ ንግድ ተሰማርተው በተገኙ ከ33 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊና አስተዳደረዊ እርምጅ መወሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ገለፀ፡፡
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሃላፊ አቶ አደም ኑሪ እንደገለጹት 17 ሺህ 424 ማስጠንቀቂያ ፣14 ሺህ 285 የታሸጉ፣ 260 የተሰረዘ ንግድ ፈቃድ፣ 107 የታገደ ንግድ ፈቃድ ፣ 120 ከትስስር የወጡ ንግድ ድርጀቶች፣ አንድ 495 ከተፈቀደው የልኬት መጠን በታች በመለካት ህገ-ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል።
በርካታ የንግድ ማህበረሰብ በቅንነት እያገለገሉ የህብረተሰቡን ችግር ለማቃለል መስራታቸውንና ከ12 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችም ሚዛኖቻቸውን ወደ ዲጅታል መቀየራቸውን ተናግረዋል።
የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ የተለያዩ ህግ የማሰከበር ስራ እየሰራ በመሆኑ ህብረተሰብ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ መቅረቡን የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
ከንግዱና ከሸማቹ ማህበረሰብ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለመፍታት ግንዛቤ በመፍጠርና ህገ-ወጥነትን የመከላከል ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ቢሮው ጨምሮ አስታውቋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በህገ-ወጥ ንግድ ተሰማርተው በተገኙ ከ33 ሺህ በላይ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊና አስተዳደረዊ እርምጅ መወሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ ገለፀ፡፡
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሃላፊ አቶ አደም ኑሪ እንደገለጹት 17 ሺህ 424 ማስጠንቀቂያ ፣14 ሺህ 285 የታሸጉ፣ 260 የተሰረዘ ንግድ ፈቃድ፣ 107 የታገደ ንግድ ፈቃድ ፣ 120 ከትስስር የወጡ ንግድ ድርጀቶች፣ አንድ 495 ከተፈቀደው የልኬት መጠን በታች በመለካት ህገ-ወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል።
በርካታ የንግድ ማህበረሰብ በቅንነት እያገለገሉ የህብረተሰቡን ችግር ለማቃለል መስራታቸውንና ከ12 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችም ሚዛኖቻቸውን ወደ ዲጅታል መቀየራቸውን ተናግረዋል።
የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ የተለያዩ ህግ የማሰከበር ስራ እየሰራ በመሆኑ ህብረተሰብ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ መቅረቡን የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
ከንግዱና ከሸማቹ ማህበረሰብ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለመፍታት ግንዛቤ በመፍጠርና ህገ-ወጥነትን የመከላከል ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ቢሮው ጨምሮ አስታውቋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የዓለም ባንክ በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ አጸደቀ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ከአምስት ሚሊዮን በላይ ወገኖች ተጠቃሚ የሚያደርግ የገንዘብ ድጋፍ ማጽደቁን አስታወቀ።
የዓለም ባንከ ትናንት ባወጣው መግለጫው ላይ እንዳስታወቀው፤ በጦርነቱ ምክንያት በርካቶች ህይወታቸውን አጥተዋል፤ ሀብት ንብረታቸው ወድሟ፤ የህዝብ መገልገያ የሆኑ ተቋማትና ንብረቶችም በተመሳሳይ ወድመዋል፤ ዜጎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። ሴቶችና ህጻናትም ለጾታዊ ጥቃት ተጋልጠዋል።
ኢትዮጵያ ይህንን ችግር ለመቋቋም እያደረገች ያለውን ጥረት ለማገዝና ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም ባንኩ የ300 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማጽደቁን አስታውቋል።
ድጋፉ ለማህበረሰቡ አስቸኳይ የእለት ደራሽ ፍላጎቶች፣ የወደሙ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባትና ለተያያዥ ማህበረሰብ አቀፍ ጉዳዮች የሚውል መሆኑንም ባንኩ ገልጿል።
የባንኩ ፕሮጀክት በመነሻነት ተግባራዊ የሚደረገውም በአፋር፣ አማራ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ኦሮሚያና ትግራይ አካባቢዎች መሆኑም ተብራርቷል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ከአምስት ሚሊዮን በላይ ወገኖች ተጠቃሚ የሚያደርግ የገንዘብ ድጋፍ ማጽደቁን አስታወቀ።
የዓለም ባንከ ትናንት ባወጣው መግለጫው ላይ እንዳስታወቀው፤ በጦርነቱ ምክንያት በርካቶች ህይወታቸውን አጥተዋል፤ ሀብት ንብረታቸው ወድሟ፤ የህዝብ መገልገያ የሆኑ ተቋማትና ንብረቶችም በተመሳሳይ ወድመዋል፤ ዜጎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። ሴቶችና ህጻናትም ለጾታዊ ጥቃት ተጋልጠዋል።
ኢትዮጵያ ይህንን ችግር ለመቋቋም እያደረገች ያለውን ጥረት ለማገዝና ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም ባንኩ የ300 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማጽደቁን አስታውቋል።
ድጋፉ ለማህበረሰቡ አስቸኳይ የእለት ደራሽ ፍላጎቶች፣ የወደሙ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባትና ለተያያዥ ማህበረሰብ አቀፍ ጉዳዮች የሚውል መሆኑንም ባንኩ ገልጿል።
የባንኩ ፕሮጀክት በመነሻነት ተግባራዊ የሚደረገውም በአፋር፣ አማራ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ ኦሮሚያና ትግራይ አካባቢዎች መሆኑም ተብራርቷል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
በመጋቢት ወር ብቻ ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል
********************
(ኢ ፕ ድ)
በመጋቢት ወር ብቻ ከ27 ነጥብ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ የገቢዎች ሚኒስቴር አሰታወቀ ።
የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው እንዳስታወቁት፣ የተሰበሰበው ገቢ የዕቅዱ 99 ነጥብ 67 በመቶ ማሳካት ተችሏል። ከ2ዐ13 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃፀር 29 ነጥብ 11 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብለዋል።
ገቢው በበርካታ ተግዳሮቶች ውስጥ የተሰበሰበ በመሆኑ ጥሩ አፈፃፀም ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ይህም ውጤት ሊመዘገብ የቻለው ምንም ዓይነት ምክንያት ሳያሳብቡ በወቅቱ ግብራቸውን አስታውቀው በሚከፈሉ ግብር ከፋዮቻችን መልካምፈቀደኝነት በመኖሩ፤ የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት በመቻላቸው እንዲሁም አጋር አካላትና ሕዝቡ እውነተኛ ድጋፍ በማድረጉ ነው።
በመሆኑም በ3ቱም የጋራ ጥረት የመጣ ውጤት በመሆኑ በራሴና በገቢዎች ሚኒስቴር ሥም ከልብ እያመሰገንኩ በቀሪ ሦስት ወራትም የመጋቢትን ወር አፈፃፀም እንድንደግመው ድጋፋችሁ እንዳይለየን የአክብሮት ጥሬዬን ለማቅረብ እወዳለሁ ብለዋል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
********************
(ኢ ፕ ድ)
በመጋቢት ወር ብቻ ከ27 ነጥብ ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ የገቢዎች ሚኒስቴር አሰታወቀ ።
የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው እንዳስታወቁት፣ የተሰበሰበው ገቢ የዕቅዱ 99 ነጥብ 67 በመቶ ማሳካት ተችሏል። ከ2ዐ13 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃፀር 29 ነጥብ 11 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብለዋል።
ገቢው በበርካታ ተግዳሮቶች ውስጥ የተሰበሰበ በመሆኑ ጥሩ አፈፃፀም ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ይህም ውጤት ሊመዘገብ የቻለው ምንም ዓይነት ምክንያት ሳያሳብቡ በወቅቱ ግብራቸውን አስታውቀው በሚከፈሉ ግብር ከፋዮቻችን መልካምፈቀደኝነት በመኖሩ፤ የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት በመቻላቸው እንዲሁም አጋር አካላትና ሕዝቡ እውነተኛ ድጋፍ በማድረጉ ነው።
በመሆኑም በ3ቱም የጋራ ጥረት የመጣ ውጤት በመሆኑ በራሴና በገቢዎች ሚኒስቴር ሥም ከልብ እያመሰገንኩ በቀሪ ሦስት ወራትም የመጋቢትን ወር አፈፃፀም እንድንደግመው ድጋፋችሁ እንዳይለየን የአክብሮት ጥሬዬን ለማቅረብ እወዳለሁ ብለዋል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ አስነሳላችኋላሁ በማለት ጉቦ ሲቀበል የነበረ መርማሪ በቁጥጥር ስር ዋለ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥባቸው በተደረጉ ንብረቶች ላይ ግለሰቦችን "እግድ አስነሳላችኋላሁ" በማለት ጉቦ ሲቀበል የነበረ መርማሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሙስና ወንጀል በተጀመረ ምርመራ ምክንያት ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው በፍርድ ቤት የንብረት እግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥባቸው የተደረጉ ግለሰቦችን እግድ አስነሳላችኋላሁ በማለት ጉቦ ሲቀበል የነበረ መርማሪ በተቋሙ አመራሮችና በግለሰቦቹ ጥቆማ በፖለስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በግለሰቡ መኖሪያ ቤቱ በተደረገ ብርበራ 420 ሺህ የተገኘ ሲሆን በድርጊቱ ተሳታፊ በሆኑ ሌሎች ግለሰቦች ላይ ምርመራ ቀጥሏል፡፡
በመሆኑም ህብረተሰቡ መሰል ህገወጥ ድርጊቶችን በማጋለጥ የህግ የበላይነትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፍና መብቱን በህጋዊ መንገድ ብቻ በማስከበር የወንጀለኞች መጠቀሚያ ከመሆን ራሱን እንዲጠብቅ ሚኒስቴሩ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
********************
(ኢ ፕ ድ)
በፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥባቸው በተደረጉ ንብረቶች ላይ ግለሰቦችን "እግድ አስነሳላችኋላሁ" በማለት ጉቦ ሲቀበል የነበረ መርማሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሙስና ወንጀል በተጀመረ ምርመራ ምክንያት ከወንጀሉ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው በፍርድ ቤት የንብረት እግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥባቸው የተደረጉ ግለሰቦችን እግድ አስነሳላችኋላሁ በማለት ጉቦ ሲቀበል የነበረ መርማሪ በተቋሙ አመራሮችና በግለሰቦቹ ጥቆማ በፖለስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በግለሰቡ መኖሪያ ቤቱ በተደረገ ብርበራ 420 ሺህ የተገኘ ሲሆን በድርጊቱ ተሳታፊ በሆኑ ሌሎች ግለሰቦች ላይ ምርመራ ቀጥሏል፡፡
በመሆኑም ህብረተሰቡ መሰል ህገወጥ ድርጊቶችን በማጋለጥ የህግ የበላይነትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፍና መብቱን በህጋዊ መንገድ ብቻ በማስከበር የወንጀለኞች መጠቀሚያ ከመሆን ራሱን እንዲጠብቅ ሚኒስቴሩ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የእስራኤል የልዑካን ቡድን የጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄዱ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የእስራኤል የፓርላማ አባላት እና የጤና ባለሙያዎች ቡድን በአሸባሪው ህወሓት ወረራ የተጎዱ የጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምሁራንና ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄዱ፡፡
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮጵያና የእስራኤል ግንኙነት ትስስር ከዲፕሎማሲ ባለፈ ነው ያሉት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ የክልሉ ጤና ተቋማት የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ ነው።
ጉዳቱን መልሶ በመገንባት የተሟላ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ከየአቅጣጫው ለሚደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
የኢትዮጵያና የእስራኤል የፓርላማ አባላት፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ የአማራ ክልል የርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ እርዚቅ ኢሳ፣ የእስራኤል ቆንስላ ፅ/ቤት የጎንደር ቅርንጫፍ ዳይሬከረተር አቶ አዳነ ተድላ፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር እና ጉዳት የደረሰባቸው ዞኖች የጤና ተቋማት ኃላፊዎች በመድረኩ ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
******************
(ኢ ፕ ድ)
የእስራኤል የፓርላማ አባላት እና የጤና ባለሙያዎች ቡድን በአሸባሪው ህወሓት ወረራ የተጎዱ የጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምሁራንና ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄዱ፡፡
ዘመናትን የተሻገረው የኢትዮጵያና የእስራኤል ግንኙነት ትስስር ከዲፕሎማሲ ባለፈ ነው ያሉት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ የክልሉ ጤና ተቋማት የደረሰባቸው ጉዳት ከፍተኛ ነው።
ጉዳቱን መልሶ በመገንባት የተሟላ የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ከየአቅጣጫው ለሚደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
የኢትዮጵያና የእስራኤል የፓርላማ አባላት፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ የአማራ ክልል የርዕሰ መስተዳድር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ እርዚቅ ኢሳ፣ የእስራኤል ቆንስላ ፅ/ቤት የጎንደር ቅርንጫፍ ዳይሬከረተር አቶ አዳነ ተድላ፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር እና ጉዳት የደረሰባቸው ዞኖች የጤና ተቋማት ኃላፊዎች በመድረኩ ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️