Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
40K photos
302 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የሰዎችን ሕይወት በማጥፋትና ዜጎችን በማፈናቀል የፖለቲካ ዓላማን ማሳካት እንደማይቻል ተጠቆመ
****************
(ኢ ፕ ድ)

የንጹሃን ሰዎችን ሕይወት በማጥፋትና ዜጎችን ከቀያቸው በማፈናቀል የፖለቲካ ዓላማን ማሳካት እንደማይቻል ተጠቆመ። ሰላም በየአካባቢው ለማረጋገጥ ትልቁን ድርሻ የሚጫወተው መንግሥት ቢሆንም ኅብረተሰቡም ጽንፈኞችንና ሽብርተኞችን በመታገልና በማጋለጥ የማይተካ ሚና እንዳለው ተገልጿል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የሕግና ሰላም ልማት መምህር አቶ ሮባ ጴጥሮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ ግጭቶች በፖለቲካ ልዩነት፣ በጎሳ፣ በሃይማኖትና በሌሎች በርካታ ምክንያቶች ሊከሰቱ ቢችሉም አገር ያለ ሰላም፤ ሰላም ደግሞ ያለ ውይይት ሊኖር አይችልም።

በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚስተዋለው ግጭትና የሰላም መደፍረስ መንስኤዎቹ በርካታ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የሽብር ቡድኖችና ፅንፈኛ ኃይሎች የማኅበረሰቡን ሕይወት አደጋ ውስጥ በመጣልና ከቀዬው በማፈናቀል በሰላም ወጥቶ እንዳይገባ ፈተና መሆናቸውን ተናግረዋል።

የአገር ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት የተጣለበት መንግሥት በአገር ደህንነት ላይ የተጋረጡ ስጋቶችን....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70817

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
“ጂፒኤስ ያስገጠሙ የሕዝብ ተሽከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማ ይደረግላቸዋል” -የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ከ12 ሰዎች በላይ የመጫን አቅም ያላቸውና ጂፒኤስ ያስገጠሙ የሕዝብ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ባወጡባቸው አካባቢ በሚመጣው የመረጃ ቋት (ዳታ ቤዝ) መሠረት የነዳጅ ድጎማው ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
የነዳጅ ድጎማውን ለማግኘት እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2014 ዓ.ም እያንዳንዱ ተሽከርካሪ ጂፒኤስ ማስገጠም እንደሚኖርበት ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት አቶ አረጋዊ ማሩ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የነዳጅ ድጎማው የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ተሽከርካሪዎች ለኅብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ያስችላል። ድጎማውም ከሐምሌ አንድ 2014ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል።
በድጎማ ሥርዓቱ ተሽከርካሪዎች ጂፒኤስ ማስገጠም የመጀመሪያው መስፈርት መሆኑን የገለጹት አቶ አረጋዊ፤ ይህም የትራንስፖርት ስምሪቱን በቴክኖሎጂ በማስተሳሰር ቁጥጥሩን ለማሳለጥ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።
እንደ አቶ አረጋዊ ገለጻ፤ በአዲስ አበባ ነባራዊ ሁኔታ የሰሌዳ ቁጥር ያላቸው፤ 12 ሰዎችንና ከዚያ በላይ የመጫን አቅም ያላቸው ኮድ አንድ ብዙኃን ትራንስፖርት የነዳጅ ድጎማው ተጠቃሚዎች ናቸው። እንዲሁም ኮድ ሦስት የሆኑና ጂፒኤስ የተገጠመላቸው ከ12 ሰዎች በላይ የሚጭኑ ተሽከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማው በቀጥታ ይመለከታቸዋል።
ከሌሎች ክልሎች ሰሌዳ አውጥተው በከተማዋ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70839
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ መንግሥት እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ የኑሮ ውድነትን እያባባሱ ባሉ ስግብግብ ነጋዴዎች ላይ መንግሥት እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ። የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጫናው ከፍተኛ በመሆኑ ወቅቱን የዋጀ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሥራ ሊሠራ ይገባል።
የፖለቲካና የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ወሰንሰገድ አሰፋ በተለይም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ አሁን እየታየ ያለው የምርቶች የዋጋ ንረት አገራዊ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ ጉዳይ ሆኖ እየታየ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈጠር ማንኛውም ኢኮኖሚ እድገት ሲመጣ በራሱ የሚፈጠር የዋጋ ግሽበት መኖሩን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የዋጋ ግሽበት እያደገ መምጣት ደግሞ ከሰዎች የመሥራት አቅም ማደግ ጋር የሚያያዝ እንደሆነም ገልጸዋል። ለአብነት የኢኮኖሚ የዋጋ ግሽበት የፍላጎትና የአቅርቦት መጠን አለመመጣጠን መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ጠቁመዋል።
በምንዛሬ እጥረት የሚፈጠር የዋጋ ንረት ቢኖርም በብዙ ቢሊዮን ዶላር ወጪ የግብርና ምርት ግብዓት ማሟያ የሚውለው በጀት ለጦርነት የሚመደብ ከሆነ፣ የመሠረታዊ ፍላጎት እጥረት እንዲኖር ያደርጋል። በዚህ ወቅት የዋጋ ንረቱ እያሻቀበ የኑሮ ውድነቱ እንዲባባስ ያደርጋል።
የዋጋ ንረቱ ክፍተት አገራዊ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መሆኑን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70824
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
በአፋር ክልል ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የዕለት ደራሽ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል
****************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የአስቸኳይ ጊዜ የዕለት ደራሽ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።
የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደበበ ዘውዴ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በክልሉ ከሚገኙ 21 ወረዳዎች ከአንድ ነጥብ ሦስት ሚሊዮን በላይ ሰዎች የአስቸኳይ ጊዜ የዕለት ደራሽ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። በአሸባሪው የሕወሓት ቡድን ወረራ ምክንያት ከ645 ሺህ በላይ ዜጎች ከትውልድ ቀዬአቸው ተፈናቅለዋል።
በክልሉ ለጉዳት ከተጋለጡት አንዱ በሆነው ኪልባቲ ዞን ሁለት ሥር የሚገኙ ስድስት ወረዳዎች አባአላ፣ መጋሌ፣ ኮነቫ፣ ዳሎል፣ ኢረብቲ እና በርሃሌ በወረራው ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ያሉት ኃላፊው በተለይም አባአላ እና ኢረብቲ ወረዳዎች አልፎ አልፎ የሚነሱ ግጭቶች ለተፈናቃይ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70824
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በኩላሊትና ካንሰር ሕክምና ላይ አተኩሮ እየሠራ መሆኑን ገለጸ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በጤናው ዘርፍ በኩላሊትና ካንሰር ሕክምና ላይ በማተኮር ውጤት ለማስመዝገብ እየሠራ መሆኑን ገለጸ።
ዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው በጤና ዘርፍ የኩላሊት ሕክምናና ካንሰር ላይ ለመሥራት በትኩረት አቅጣጫ ለይቷል። በእነዚህ የሕክምና ዘርፎች ለአካባቢው ማህበረሰብ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ ይገኛል።
ለኩላሊት እጥበት ከተለያዩ አካባቢዎች ለሚመጡ ታካሚዎች የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፤ ይህንን አገልግሎት ይበልጥ ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው ብለዋል።
በካንሰር ሕክምናም በተሻለ መልኩ አገልግሎቱን ለመስጠት እየሠራ እንደሚገኘ ገልጸው፤ በተለይ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የሕክምና ዓይነቶች ኅብረተሰቡን ለማገልግል ራሱን ዘመኑ በአፈራቸው ቤተ ሙከራዎችና የሕክምና መሣሪያዎች ራሱን የማዘመን ሥራ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70823
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ሦስት ወረዳዎች የአቮካዶ ምርትን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ውጤታማነታቸው መረጋገጡን ማኅበሩ አስታወቀ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጥራት ያለው የአቮካዶ ምርት ለውጭ ገበያ በማቅረብ ሦስት አካባቢዎች ውጤታማነታቸው በተግባር መረጋገጡን የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማኅበር አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማኅበር የፕሮጀክት ማናጀር አቶ ዋለ ጌታነህ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ፤ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ቡታጂራ አካባቢና በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ጥራት ያለው የአቮካዶ ምርት ለውጭ ገበያ በማቅረብ ውጤታማነታቸው በተግባር ተረጋግጧል።
እስካሁን በተከናወኑ ሥራዎች በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ለወጪ ንግድ የሚውሉ ጥራት ያላቸው የአቮካዶ ምርቶችን ማዘጋጀት ቢቻልም በኢትዮጵያ በርካታ ቦታዎች ላይ ጥራት ያለው የአቮካዶ ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም መኖሩን ጠቁመዋል።
የአካባቢዎቹን ተሞክሮም ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ማስፋፋት ያስፈልጋል ያሉት አቶ ዋለ፤ ይህን አቅም በአግባቡ ለመጠቀምና ዘርፉን ለማሳደግ የግብዓት አቅራቢዎችና አምራቹን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=70826
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ከ13 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ከውጭ ሀገር ገበያ ማግኘት ችለዋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በ2014 በጀት ዓመት 9 ወራት 216 የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻችን ወደውጭ ሀገር በመላክ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘታቸውን አሰታወቀ።
የተቋሙ የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሰ፣ ባለፉት 9 ወራት 216 የሚሆኑ ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የምርት ናሙናዎችን በማስተዋወቅና በቀጥታም ከላኪዎች ጋር የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ በማድረግ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡
በእነዚህ ኢንተርፕራይዞች 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም ምርት ወደውጭ ሀገር ተልኳል። ወደ ውጭ ከተላኩ ዋና ዋና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች መካከል የአግሮፕሮሰሲንግ፣ የዕደ-ጥበብ፣ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች እና የኬሚካልና ማዕድን ምርቶች ይገኙበታል ብለዋል፡፡
በሀገሪቱም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለፉት ወራት በርካታ ችግሮች ቢከሰቱም የሀገሪቱ ምርቶች በውጪ ሀገር ገበያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተወዳዳሪነታቸውንናጥራታቸው እየጨመረ በመምጣቱ የሽያጭ ዋጋቸውም በዚያው ልክ መጨመሩን አቶ አሸናፊ ተናግረዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር 2 ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸውን ምርቶች በአገር ውስጥ በማምረትና በመተካት የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉንም ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ባለፉት በዘጠኝ ወራት ከቀረቡት 531 ቅሬታዎች ለ529ኙ ውሳኔ መስጠቱን ኮሚሽኑ አስታወቀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ ባለፉት በዘጠኝ ወራት ከተቀረበለት 531 የይግባኝ መዛግብት ለ529ኙ ውሳኔ መስጠቱን አሰታወቀ።
ኮሚሽኑ የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።
የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አያሌው እንደተናገሩት፣ በንግድና በጉምሩክ ከታክስ ተጨማሪ አሴት ተመን ጋር ተያይዞ ለኮሚሽኑ ቅሬታ ሲቀርብለት ከውሳኔ በፊት ገለልተኛ የሆነ የግራ ቀኝ ክርክር በዳኞቹ አማካኝነት ስለሚያደርግ የሚሰጠው ውሳኔው ፍትሃዊ ነው።
ለኮሚሽኑ የሚቀርቡለት ቅሬታዎች ሲፈተሹ አብዛኞቹ ያልተሟሉና ግልጽነት የጎደላቸው መረጃዎች መሆናቸው የገለጹት አቶ ሙሉጌታ የተሟላና እውነተኛ መረጃ ይዞ የሚቀርቡ ቅሬታ አቅራቢዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
በዋቅሹም ፍቃዱ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ኤጀንሲው ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ተከትሎ ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ተጓዦች የሚያገለግል ጊዜያዊ መመሪያ ይፍ ሆነ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ተከትሎ ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የሚያገለግል ጊዜያዊ መመሪያ ማውጣቱን አሰታወቀ።
ኤጀንሲው ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በላከው ደብዳቤ መሰረት የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ከቪዛ፣ ካልታደሰ ፓስፖርትና ከትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ጋር በተያያዘ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ጊዜያዊ መመሪያው መዘጋጀቱን ተገልጿል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ፊርማ አስመስሎ በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ በማድረግ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ ተከሳሾች ላይ ክስ ተመሰረተ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የባለቤቱን ፊርማ አስመስለው በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ በማድረግ መንግስታዊ ሰነዶችን በሀሰት አስመስሎ በማዘጋጀትና በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ ተከሳሾች ላይ ክስ ተመስርቷል።
ተከሳሾቹ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዋሽ 7 ቅርንጫፍ ደንበኛ በሆኑት መዲና ሔንኬብ የውሃ ስራዎች ድርጅት ከተንቀሳቃሽ ሂሳብ ቁጥራቸው ላይ የሂሳቡ ባለቤቱ ቼክ ፈርመው ባልሰጡበት የባለቤቱን ፊርማ አስመስለው በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ አድርገዋል።
በተጨማሪም ሀሰተኛ ቼኮችን በማቅረብ የወሰዱትን ገንዘብ ለመደበቅና ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ የሞባይል ባንኪንግን ተጠቅመው በተለያዩ ግለሰቦች ወደተከፈተ አካውንት ያስተላለፉ በመሆኑ ተከሳሾች በፈፀሙት መንግስታዊ ሰነዶችን በሀሰት አስመስሎ ማዘጋጀትና በሀሰት ሰነድ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።
ተከሳሽ ሹክረዲን ሙሃመድ፣ ሳሙዔል ዳምጤ እና መሳይ ታደሰ የተባሉ ግለሰቦች የሙስና ወንጀል ለመደንገግ የወጣውን አንቀፅ 23 /1/ለ እና 2/ሀ/ ߹ የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 /1/ሀ/ እንዲሁም በወንጀል የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረትን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀፅ 29/1/ሀ/ ስር የተመለከተውን በመተላለፋቸው ክስ የተመሰረተባቸው።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ወንጀል ቸሎት በህግ ጥላ ስር ላለው 1ኛ ተከሳሽ የክስ ቻርጁ አንዲደርሰው ተደርጎ የክስ መቃወሚያ ካለውና ያልተያዙት 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሽን ደግሞ ፖሊስ አፈላልጎ አንዲያቀርብ ለሚያዝያ 10/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ከፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
"ከ94 ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት መድረክ ቅዳሜ ይካሄዳል" - የደቡብ ወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ክልል 94 ሺህ 200 ወጣቶች የሚሳተፉበት ክልል አቀፍ የውይይት መድረክ ሚያዚያ 8/2014 እንደሚካሄድ የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
የሊግ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሰንበቶ አባባ፣ ወጣቱ በብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎችን በአግባቡ ተረድቶ ወደቀጣዩ ተግባር በእውቀት እንዲገባ የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል፡፡
መድረኮቹ ለወጣቱ የተሻለ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችሉ፣ መካተትና መሻሻል አለባቸው የሚሏቸውን ጉዳዮች በነጻነት የሚያነሱባቸውና የወጣቱን ወሳኝ ችግሮች ለመፍታት እንደመነሻ የሚሆኑ ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ያለወጣቱ ተሳትፎ የትኛውም ጉዳይ ግቡን እንደማይመታ ያምናል ያሉት አቶ ሰንበቶ የጉባኤው ውሳኔዎች ወደተግባር የሚቀየሩት በወጣቱ ስለሆነ ሁሉም ወጣቶች በመድረኮቹ በንቃት እንዲሳተፉም አሳስበዋል፡፡
በመድረኮቹ የፓርቲዉ አባል ያልሆኑ ወጣቶችም ጭምር እንደሚሳተፉ ያስታወቁት ጽህፈት ቤት ሃኃፊው፣ የውይይት መድረኮቹ በ157 አካባቢዎች እንደሚካሄዱና ለዚህም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡
ወጣቱ ለአካባቢው፣ለክልሉና ለአገሪቱ ይበጃሉ የሚላቸውን ሀሳቦች በቅንነት በማንሳት ዘላቂ ሰላም ያለው፣ የበለጸገ አገርና ህዝብ ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት የራሱን ሚና እንዲጫወትም አቶ ሰንበቶ ጠይቀዋል፡፡
የኑሮ ውድነቱን ለማስተካከልና የምርት አቅርቦቱን ለማሳደግ የሚያስችል የከተማ ግብርና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የሚካሄድ ሲሆን በከተማ ግብርና መልካም ተሞክሮ ያላቸው ግለሰቦች ጥረትም ጉብኝት ይካሄዳል ብለዋል፡፡
የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከ840 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉት ያመለከቱት አቶ ሰንበቶ በቀጣይ እስከ ገጠር ቀበሌያት የሚገኙ ሁሉንም ወጣቶች በጉባኤው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ለማወያየት እቅድ መያዙን አስታውቀዋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በደቡብ አፍሪካ የጎርፍ አደጋ ባደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በደቡብ አፍሪካ በጣለው ከባድ ዝናብና ባስከተለው የጎርፍ አደጋ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ባለፉት ጥቂት ቀናት በጣለው ከባድ ዝናብና በተከሰተው ጎርፍ ለተጎዱ ደቡብ አፍሪካውያን መጽናናትን ተመኝተዋል።
በደቡብ አፍሪካ የጣለው ከባድ ዝናብና ባስከተለው ጎርፍ በንብረት እና በሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️