አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ከ13 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ከውጭ ሀገር ገበያ ማግኘት ችለዋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በ2014 በጀት ዓመት 9 ወራት 216 የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻችን ወደውጭ ሀገር በመላክ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘታቸውን አሰታወቀ።
የተቋሙ የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሰ፣ ባለፉት 9 ወራት 216 የሚሆኑ ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የምርት ናሙናዎችን በማስተዋወቅና በቀጥታም ከላኪዎች ጋር የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ በማድረግ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡
በእነዚህ ኢንተርፕራይዞች 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም ምርት ወደውጭ ሀገር ተልኳል። ወደ ውጭ ከተላኩ ዋና ዋና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች መካከል የአግሮፕሮሰሲንግ፣ የዕደ-ጥበብ፣ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች እና የኬሚካልና ማዕድን ምርቶች ይገኙበታል ብለዋል፡፡
በሀገሪቱም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለፉት ወራት በርካታ ችግሮች ቢከሰቱም የሀገሪቱ ምርቶች በውጪ ሀገር ገበያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተወዳዳሪነታቸውንናጥራታቸው እየጨመረ በመምጣቱ የሽያጭ ዋጋቸውም በዚያው ልክ መጨመሩን አቶ አሸናፊ ተናግረዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር 2 ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸውን ምርቶች በአገር ውስጥ በማምረትና በመተካት የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉንም ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በ2014 በጀት ዓመት 9 ወራት 216 የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻችን ወደውጭ ሀገር በመላክ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘታቸውን አሰታወቀ።
የተቋሙ የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ መለሰ፣ ባለፉት 9 ወራት 216 የሚሆኑ ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች የምርት ናሙናዎችን በማስተዋወቅና በቀጥታም ከላኪዎች ጋር የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ በማድረግ 13 ነጥብ 3 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡
በእነዚህ ኢንተርፕራይዞች 5 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም ምርት ወደውጭ ሀገር ተልኳል። ወደ ውጭ ከተላኩ ዋና ዋና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች መካከል የአግሮፕሮሰሲንግ፣ የዕደ-ጥበብ፣ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች እና የኬሚካልና ማዕድን ምርቶች ይገኙበታል ብለዋል፡፡
በሀገሪቱም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለፉት ወራት በርካታ ችግሮች ቢከሰቱም የሀገሪቱ ምርቶች በውጪ ሀገር ገበያ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተወዳዳሪነታቸውንናጥራታቸው እየጨመረ በመምጣቱ የሽያጭ ዋጋቸውም በዚያው ልክ መጨመሩን አቶ አሸናፊ ተናግረዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር 2 ሚሊየን ዶላር ዋጋ ያላቸውን ምርቶች በአገር ውስጥ በማምረትና በመተካት የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉንም ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ባለፉት በዘጠኝ ወራት ከቀረቡት 531 ቅሬታዎች ለ529ኙ ውሳኔ መስጠቱን ኮሚሽኑ አስታወቀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ ባለፉት በዘጠኝ ወራት ከተቀረበለት 531 የይግባኝ መዛግብት ለ529ኙ ውሳኔ መስጠቱን አሰታወቀ።
ኮሚሽኑ የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።
የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አያሌው እንደተናገሩት፣ በንግድና በጉምሩክ ከታክስ ተጨማሪ አሴት ተመን ጋር ተያይዞ ለኮሚሽኑ ቅሬታ ሲቀርብለት ከውሳኔ በፊት ገለልተኛ የሆነ የግራ ቀኝ ክርክር በዳኞቹ አማካኝነት ስለሚያደርግ የሚሰጠው ውሳኔው ፍትሃዊ ነው።
ለኮሚሽኑ የሚቀርቡለት ቅሬታዎች ሲፈተሹ አብዛኞቹ ያልተሟሉና ግልጽነት የጎደላቸው መረጃዎች መሆናቸው የገለጹት አቶ ሙሉጌታ የተሟላና እውነተኛ መረጃ ይዞ የሚቀርቡ ቅሬታ አቅራቢዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
በዋቅሹም ፍቃዱ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ ባለፉት በዘጠኝ ወራት ከተቀረበለት 531 የይግባኝ መዛግብት ለ529ኙ ውሳኔ መስጠቱን አሰታወቀ።
ኮሚሽኑ የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።
የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አያሌው እንደተናገሩት፣ በንግድና በጉምሩክ ከታክስ ተጨማሪ አሴት ተመን ጋር ተያይዞ ለኮሚሽኑ ቅሬታ ሲቀርብለት ከውሳኔ በፊት ገለልተኛ የሆነ የግራ ቀኝ ክርክር በዳኞቹ አማካኝነት ስለሚያደርግ የሚሰጠው ውሳኔው ፍትሃዊ ነው።
ለኮሚሽኑ የሚቀርቡለት ቅሬታዎች ሲፈተሹ አብዛኞቹ ያልተሟሉና ግልጽነት የጎደላቸው መረጃዎች መሆናቸው የገለጹት አቶ ሙሉጌታ የተሟላና እውነተኛ መረጃ ይዞ የሚቀርቡ ቅሬታ አቅራቢዎች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
በዋቅሹም ፍቃዱ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ኤጀንሲው ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ተከትሎ ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ተጓዦች የሚያገለግል ጊዜያዊ መመሪያ ይፍ ሆነ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ተከትሎ ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የሚያገለግል ጊዜያዊ መመሪያ ማውጣቱን አሰታወቀ።
ኤጀንሲው ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በላከው ደብዳቤ መሰረት የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ከቪዛ፣ ካልታደሰ ፓስፖርትና ከትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ጋር በተያያዘ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ጊዜያዊ መመሪያው መዘጋጀቱን ተገልጿል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ከኢድ እስከ ኢድ ጥሪን ተከትሎ ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የሚያገለግል ጊዜያዊ መመሪያ ማውጣቱን አሰታወቀ።
ኤጀንሲው ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት በላከው ደብዳቤ መሰረት የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ከቪዛ፣ ካልታደሰ ፓስፖርትና ከትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ጋር በተያያዘ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ጊዜያዊ መመሪያው መዘጋጀቱን ተገልጿል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ፊርማ አስመስሎ በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ በማድረግ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ ተከሳሾች ላይ ክስ ተመሰረተ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የባለቤቱን ፊርማ አስመስለው በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ በማድረግ መንግስታዊ ሰነዶችን በሀሰት አስመስሎ በማዘጋጀትና በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ ተከሳሾች ላይ ክስ ተመስርቷል።
ተከሳሾቹ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዋሽ 7 ቅርንጫፍ ደንበኛ በሆኑት መዲና ሔንኬብ የውሃ ስራዎች ድርጅት ከተንቀሳቃሽ ሂሳብ ቁጥራቸው ላይ የሂሳቡ ባለቤቱ ቼክ ፈርመው ባልሰጡበት የባለቤቱን ፊርማ አስመስለው በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ አድርገዋል።
በተጨማሪም ሀሰተኛ ቼኮችን በማቅረብ የወሰዱትን ገንዘብ ለመደበቅና ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ የሞባይል ባንኪንግን ተጠቅመው በተለያዩ ግለሰቦች ወደተከፈተ አካውንት ያስተላለፉ በመሆኑ ተከሳሾች በፈፀሙት መንግስታዊ ሰነዶችን በሀሰት አስመስሎ ማዘጋጀትና በሀሰት ሰነድ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።
ተከሳሽ ሹክረዲን ሙሃመድ፣ ሳሙዔል ዳምጤ እና መሳይ ታደሰ የተባሉ ግለሰቦች የሙስና ወንጀል ለመደንገግ የወጣውን አንቀፅ 23 /1/ለ እና 2/ሀ/ ߹ የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 /1/ሀ/ እንዲሁም በወንጀል የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረትን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀፅ 29/1/ሀ/ ስር የተመለከተውን በመተላለፋቸው ክስ የተመሰረተባቸው።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ወንጀል ቸሎት በህግ ጥላ ስር ላለው 1ኛ ተከሳሽ የክስ ቻርጁ አንዲደርሰው ተደርጎ የክስ መቃወሚያ ካለውና ያልተያዙት 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሽን ደግሞ ፖሊስ አፈላልጎ አንዲያቀርብ ለሚያዝያ 10/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ከፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የባለቤቱን ፊርማ አስመስለው በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ በማድረግ መንግስታዊ ሰነዶችን በሀሰት አስመስሎ በማዘጋጀትና በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል በፈፀሙ ተከሳሾች ላይ ክስ ተመስርቷል።
ተከሳሾቹ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዋሽ 7 ቅርንጫፍ ደንበኛ በሆኑት መዲና ሔንኬብ የውሃ ስራዎች ድርጅት ከተንቀሳቃሽ ሂሳብ ቁጥራቸው ላይ የሂሳቡ ባለቤቱ ቼክ ፈርመው ባልሰጡበት የባለቤቱን ፊርማ አስመስለው በመፈረም ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ወጪና ገቢ አድርገዋል።
በተጨማሪም ሀሰተኛ ቼኮችን በማቅረብ የወሰዱትን ገንዘብ ለመደበቅና ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ የሞባይል ባንኪንግን ተጠቅመው በተለያዩ ግለሰቦች ወደተከፈተ አካውንት ያስተላለፉ በመሆኑ ተከሳሾች በፈፀሙት መንግስታዊ ሰነዶችን በሀሰት አስመስሎ ማዘጋጀትና በሀሰት ሰነድ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።
ተከሳሽ ሹክረዲን ሙሃመድ፣ ሳሙዔል ዳምጤ እና መሳይ ታደሰ የተባሉ ግለሰቦች የሙስና ወንጀል ለመደንገግ የወጣውን አንቀፅ 23 /1/ለ እና 2/ሀ/ ߹ የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 /1/ሀ/ እንዲሁም በወንጀል የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረትን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀፅ 29/1/ሀ/ ስር የተመለከተውን በመተላለፋቸው ክስ የተመሰረተባቸው።
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ወንጀል ቸሎት በህግ ጥላ ስር ላለው 1ኛ ተከሳሽ የክስ ቻርጁ አንዲደርሰው ተደርጎ የክስ መቃወሚያ ካለውና ያልተያዙት 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሽን ደግሞ ፖሊስ አፈላልጎ አንዲያቀርብ ለሚያዝያ 10/2014 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ከፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
"ከ94 ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት መድረክ ቅዳሜ ይካሄዳል" - የደቡብ ወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ክልል 94 ሺህ 200 ወጣቶች የሚሳተፉበት ክልል አቀፍ የውይይት መድረክ ሚያዚያ 8/2014 እንደሚካሄድ የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
የሊግ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሰንበቶ አባባ፣ ወጣቱ በብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎችን በአግባቡ ተረድቶ ወደቀጣዩ ተግባር በእውቀት እንዲገባ የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል፡፡
መድረኮቹ ለወጣቱ የተሻለ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችሉ፣ መካተትና መሻሻል አለባቸው የሚሏቸውን ጉዳዮች በነጻነት የሚያነሱባቸውና የወጣቱን ወሳኝ ችግሮች ለመፍታት እንደመነሻ የሚሆኑ ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ያለወጣቱ ተሳትፎ የትኛውም ጉዳይ ግቡን እንደማይመታ ያምናል ያሉት አቶ ሰንበቶ የጉባኤው ውሳኔዎች ወደተግባር የሚቀየሩት በወጣቱ ስለሆነ ሁሉም ወጣቶች በመድረኮቹ በንቃት እንዲሳተፉም አሳስበዋል፡፡
በመድረኮቹ የፓርቲዉ አባል ያልሆኑ ወጣቶችም ጭምር እንደሚሳተፉ ያስታወቁት ጽህፈት ቤት ሃኃፊው፣ የውይይት መድረኮቹ በ157 አካባቢዎች እንደሚካሄዱና ለዚህም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡
ወጣቱ ለአካባቢው፣ለክልሉና ለአገሪቱ ይበጃሉ የሚላቸውን ሀሳቦች በቅንነት በማንሳት ዘላቂ ሰላም ያለው፣ የበለጸገ አገርና ህዝብ ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት የራሱን ሚና እንዲጫወትም አቶ ሰንበቶ ጠይቀዋል፡፡
የኑሮ ውድነቱን ለማስተካከልና የምርት አቅርቦቱን ለማሳደግ የሚያስችል የከተማ ግብርና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የሚካሄድ ሲሆን በከተማ ግብርና መልካም ተሞክሮ ያላቸው ግለሰቦች ጥረትም ጉብኝት ይካሄዳል ብለዋል፡፡
የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከ840 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉት ያመለከቱት አቶ ሰንበቶ በቀጣይ እስከ ገጠር ቀበሌያት የሚገኙ ሁሉንም ወጣቶች በጉባኤው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ለማወያየት እቅድ መያዙን አስታውቀዋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ክልል 94 ሺህ 200 ወጣቶች የሚሳተፉበት ክልል አቀፍ የውይይት መድረክ ሚያዚያ 8/2014 እንደሚካሄድ የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡
የሊግ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሰንበቶ አባባ፣ ወጣቱ በብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎችን በአግባቡ ተረድቶ ወደቀጣዩ ተግባር በእውቀት እንዲገባ የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል፡፡
መድረኮቹ ለወጣቱ የተሻለ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችሉ፣ መካተትና መሻሻል አለባቸው የሚሏቸውን ጉዳዮች በነጻነት የሚያነሱባቸውና የወጣቱን ወሳኝ ችግሮች ለመፍታት እንደመነሻ የሚሆኑ ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡
ብልጽግና ፓርቲ ያለወጣቱ ተሳትፎ የትኛውም ጉዳይ ግቡን እንደማይመታ ያምናል ያሉት አቶ ሰንበቶ የጉባኤው ውሳኔዎች ወደተግባር የሚቀየሩት በወጣቱ ስለሆነ ሁሉም ወጣቶች በመድረኮቹ በንቃት እንዲሳተፉም አሳስበዋል፡፡
በመድረኮቹ የፓርቲዉ አባል ያልሆኑ ወጣቶችም ጭምር እንደሚሳተፉ ያስታወቁት ጽህፈት ቤት ሃኃፊው፣ የውይይት መድረኮቹ በ157 አካባቢዎች እንደሚካሄዱና ለዚህም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡
ወጣቱ ለአካባቢው፣ለክልሉና ለአገሪቱ ይበጃሉ የሚላቸውን ሀሳቦች በቅንነት በማንሳት ዘላቂ ሰላም ያለው፣ የበለጸገ አገርና ህዝብ ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት የራሱን ሚና እንዲጫወትም አቶ ሰንበቶ ጠይቀዋል፡፡
የኑሮ ውድነቱን ለማስተካከልና የምርት አቅርቦቱን ለማሳደግ የሚያስችል የከተማ ግብርና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የሚካሄድ ሲሆን በከተማ ግብርና መልካም ተሞክሮ ያላቸው ግለሰቦች ጥረትም ጉብኝት ይካሄዳል ብለዋል፡፡
የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከ840 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉት ያመለከቱት አቶ ሰንበቶ በቀጣይ እስከ ገጠር ቀበሌያት የሚገኙ ሁሉንም ወጣቶች በጉባኤው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ለማወያየት እቅድ መያዙን አስታውቀዋል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በደቡብ አፍሪካ የጎርፍ አደጋ ባደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በደቡብ አፍሪካ በጣለው ከባድ ዝናብና ባስከተለው የጎርፍ አደጋ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ባለፉት ጥቂት ቀናት በጣለው ከባድ ዝናብና በተከሰተው ጎርፍ ለተጎዱ ደቡብ አፍሪካውያን መጽናናትን ተመኝተዋል።
በደቡብ አፍሪካ የጣለው ከባድ ዝናብና ባስከተለው ጎርፍ በንብረት እና በሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በደቡብ አፍሪካ በጣለው ከባድ ዝናብና ባስከተለው የጎርፍ አደጋ በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ ባለፉት ጥቂት ቀናት በጣለው ከባድ ዝናብና በተከሰተው ጎርፍ ለተጎዱ ደቡብ አፍሪካውያን መጽናናትን ተመኝተዋል።
በደቡብ አፍሪካ የጣለው ከባድ ዝናብና ባስከተለው ጎርፍ በንብረት እና በሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የከተማዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ነዋሪዎችና የፀጥታ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
“አካባቢየን በመጠበቅ ኃላፊነቴን እወጣለሁ” በሚል ሀሳብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የፓናል ውይይት አካሄዷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮናስ ዘውዴ፣ የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ማስቻል ነው። ለዚህም ስኬታማነት የከተማዋ ነዋሪዎች የጋራ ራዕይና ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ሁላችንም ለሠላም ዋጋ በመስጠት የአካባቢያችንን ሁለንተናዊ ሠላም ለማረጋገጥ ከጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቀንዓ ያዴታ በከተማዋ መልካቸውን በመለዋወጥ የሚያጋጥሙ የወንጀል እንቅስቃሴዎችን በመከለከል ዘላቂ ሰላምና ደሕንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የፀጥታ ተቋማትን ሁለንተናዊ አቅም በማሳደግ ወንጀልና የደንብ ጥሰትን መከላከልና መቆጣጠር ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል ኃላፊው ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አራጋው መንግሥት በሁሉም ረገድ የፀጥታ ተቋማትን ወቅቱ በሚጠይቀው መልኩ ሪፎርም ለማድረግ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ማህበረሰብ እቅፍ የፖሊስ ስራዎች ወንጀልን በመከላከል ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ማጠናከር ይገባል ተብሏል።
ያለሕብረተሰቡ ተሳትፎ በዘላቂነት ሠላምን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት ኮሚሽነር ጌቱ ፤የከተማችን ነዋሪ ፖሊስ የሚፈልገውን የመረጃ ድጋፍ በመስጠት በአጋርነት መቆም ይጠበቅበታል ብለዋል ።
የሐይማኖት አባቶች ፣ወጣቶች ፣የብሎክ አደረጃጀት ተወካዮች ፣የፀጥታ አካላት፣ታወቂ ግለሰቦች በውይይቱ መሳተፋቸውን ቢሮው አሰታውቋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*********************
(ኢ ፕ ድ)
“አካባቢየን በመጠበቅ ኃላፊነቴን እወጣለሁ” በሚል ሀሳብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የፓናል ውይይት አካሄዷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮናስ ዘውዴ፣ የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ማስቻል ነው። ለዚህም ስኬታማነት የከተማዋ ነዋሪዎች የጋራ ራዕይና ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ሁላችንም ለሠላም ዋጋ በመስጠት የአካባቢያችንን ሁለንተናዊ ሠላም ለማረጋገጥ ከጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቀንዓ ያዴታ በከተማዋ መልካቸውን በመለዋወጥ የሚያጋጥሙ የወንጀል እንቅስቃሴዎችን በመከለከል ዘላቂ ሰላምና ደሕንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የፀጥታ ተቋማትን ሁለንተናዊ አቅም በማሳደግ ወንጀልና የደንብ ጥሰትን መከላከልና መቆጣጠር ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል ኃላፊው ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አራጋው መንግሥት በሁሉም ረገድ የፀጥታ ተቋማትን ወቅቱ በሚጠይቀው መልኩ ሪፎርም ለማድረግ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ማህበረሰብ እቅፍ የፖሊስ ስራዎች ወንጀልን በመከላከል ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ማጠናከር ይገባል ተብሏል።
ያለሕብረተሰቡ ተሳትፎ በዘላቂነት ሠላምን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት ኮሚሽነር ጌቱ ፤የከተማችን ነዋሪ ፖሊስ የሚፈልገውን የመረጃ ድጋፍ በመስጠት በአጋርነት መቆም ይጠበቅበታል ብለዋል ።
የሐይማኖት አባቶች ፣ወጣቶች ፣የብሎክ አደረጃጀት ተወካዮች ፣የፀጥታ አካላት፣ታወቂ ግለሰቦች በውይይቱ መሳተፋቸውን ቢሮው አሰታውቋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በየአመቱ ለህንጻ ኪራይ የሚያወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ ለማስቀረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተለያዩ ቢሮዎቹ በየአመቱ ለህንጻ ኪራይ የሚያወጣውን አንድ ቢሊየን ብር ለማስቀረት እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ የሱፍ ኢብራሂም የተቋሙ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በቀረበበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት ከተማ አስተዳደሩ በአመት አንድ ቢሊየን ብር ለህንጻ ኪራይ እያወጣ ይገኛል።
ህንጻዎችን በማስገንባት ይህንን ወጪ ለማስቀረትና ከኪራይ ነጻ ለማድረግ መሬት ተዘጋጅቶ እንቅስቀሴ ተጀምሯል። የህንጻዎቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ መንግስትን ከወጪ በመታደግ ገንዘቡን ለሌሎች ልማቶች እንዲያውል የሚጠቅመው ይሆናል።
የሚገነቡት ህንጻዎች በአንድ አካባቢ በመሆኑ በተቋማት መካከል የሚኖርን የስራ ግንኙነት የሚያፋጥንና ለመረጃና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁ ለትራንስፖርት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል። ከከተማ መስተዳድሩ አገልግሎት የሚፈልጉ ተገልጋዮችም ተቋማቱን በአንድ አካባቢ የሚያገኟቸው በመሆኑ ከውጣ ውረድ ይድናሉም ነው ያሉት።
ባለስልጣኑ ባለቤት አልባ ህንጻዎችን እየለየ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስኪያጁ እስካሁንም ባለቤት አልባ ህንጻዎች መለየታቸውን በመጠቆም በፍርድ ቤት አሳውጆ ተረክቦ ለማስተዳደር በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በራስወርቅ ሙሉጌታ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተለያዩ ቢሮዎቹ በየአመቱ ለህንጻ ኪራይ የሚያወጣውን አንድ ቢሊየን ብር ለማስቀረት እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ የሱፍ ኢብራሂም የተቋሙ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በቀረበበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት ከተማ አስተዳደሩ በአመት አንድ ቢሊየን ብር ለህንጻ ኪራይ እያወጣ ይገኛል።
ህንጻዎችን በማስገንባት ይህንን ወጪ ለማስቀረትና ከኪራይ ነጻ ለማድረግ መሬት ተዘጋጅቶ እንቅስቀሴ ተጀምሯል። የህንጻዎቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ መንግስትን ከወጪ በመታደግ ገንዘቡን ለሌሎች ልማቶች እንዲያውል የሚጠቅመው ይሆናል።
የሚገነቡት ህንጻዎች በአንድ አካባቢ በመሆኑ በተቋማት መካከል የሚኖርን የስራ ግንኙነት የሚያፋጥንና ለመረጃና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁ ለትራንስፖርት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል። ከከተማ መስተዳድሩ አገልግሎት የሚፈልጉ ተገልጋዮችም ተቋማቱን በአንድ አካባቢ የሚያገኟቸው በመሆኑ ከውጣ ውረድ ይድናሉም ነው ያሉት።
ባለስልጣኑ ባለቤት አልባ ህንጻዎችን እየለየ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስኪያጁ እስካሁንም ባለቤት አልባ ህንጻዎች መለየታቸውን በመጠቆም በፍርድ ቤት አሳውጆ ተረክቦ ለማስተዳደር በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በራስወርቅ ሙሉጌታ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️