የከተማዋን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ነዋሪዎችና የፀጥታ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
“አካባቢየን በመጠበቅ ኃላፊነቴን እወጣለሁ” በሚል ሀሳብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የፓናል ውይይት አካሄዷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮናስ ዘውዴ፣ የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ማስቻል ነው። ለዚህም ስኬታማነት የከተማዋ ነዋሪዎች የጋራ ራዕይና ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ሁላችንም ለሠላም ዋጋ በመስጠት የአካባቢያችንን ሁለንተናዊ ሠላም ለማረጋገጥ ከጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቀንዓ ያዴታ በከተማዋ መልካቸውን በመለዋወጥ የሚያጋጥሙ የወንጀል እንቅስቃሴዎችን በመከለከል ዘላቂ ሰላምና ደሕንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የፀጥታ ተቋማትን ሁለንተናዊ አቅም በማሳደግ ወንጀልና የደንብ ጥሰትን መከላከልና መቆጣጠር ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል ኃላፊው ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አራጋው መንግሥት በሁሉም ረገድ የፀጥታ ተቋማትን ወቅቱ በሚጠይቀው መልኩ ሪፎርም ለማድረግ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ማህበረሰብ እቅፍ የፖሊስ ስራዎች ወንጀልን በመከላከል ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ማጠናከር ይገባል ተብሏል።
ያለሕብረተሰቡ ተሳትፎ በዘላቂነት ሠላምን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት ኮሚሽነር ጌቱ ፤የከተማችን ነዋሪ ፖሊስ የሚፈልገውን የመረጃ ድጋፍ በመስጠት በአጋርነት መቆም ይጠበቅበታል ብለዋል ።
የሐይማኖት አባቶች ፣ወጣቶች ፣የብሎክ አደረጃጀት ተወካዮች ፣የፀጥታ አካላት፣ታወቂ ግለሰቦች በውይይቱ መሳተፋቸውን ቢሮው አሰታውቋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*********************
(ኢ ፕ ድ)
“አካባቢየን በመጠበቅ ኃላፊነቴን እወጣለሁ” በሚል ሀሳብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የፓናል ውይይት አካሄዷል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ዮናስ ዘውዴ፣ የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ማስቻል ነው። ለዚህም ስኬታማነት የከተማዋ ነዋሪዎች የጋራ ራዕይና ትብብር አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ሁላችንም ለሠላም ዋጋ በመስጠት የአካባቢያችንን ሁለንተናዊ ሠላም ለማረጋገጥ ከጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቀንዓ ያዴታ በከተማዋ መልካቸውን በመለዋወጥ የሚያጋጥሙ የወንጀል እንቅስቃሴዎችን በመከለከል ዘላቂ ሰላምና ደሕንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የፀጥታ ተቋማትን ሁለንተናዊ አቅም በማሳደግ ወንጀልና የደንብ ጥሰትን መከላከልና መቆጣጠር ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል ኃላፊው ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አራጋው መንግሥት በሁሉም ረገድ የፀጥታ ተቋማትን ወቅቱ በሚጠይቀው መልኩ ሪፎርም ለማድረግ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ማህበረሰብ እቅፍ የፖሊስ ስራዎች ወንጀልን በመከላከል ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ማጠናከር ይገባል ተብሏል።
ያለሕብረተሰቡ ተሳትፎ በዘላቂነት ሠላምን ማረጋገጥ አይቻልም ያሉት ኮሚሽነር ጌቱ ፤የከተማችን ነዋሪ ፖሊስ የሚፈልገውን የመረጃ ድጋፍ በመስጠት በአጋርነት መቆም ይጠበቅበታል ብለዋል ።
የሐይማኖት አባቶች ፣ወጣቶች ፣የብሎክ አደረጃጀት ተወካዮች ፣የፀጥታ አካላት፣ታወቂ ግለሰቦች በውይይቱ መሳተፋቸውን ቢሮው አሰታውቋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በየአመቱ ለህንጻ ኪራይ የሚያወጣውን ከፍተኛ ገንዘብ ለማስቀረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተለያዩ ቢሮዎቹ በየአመቱ ለህንጻ ኪራይ የሚያወጣውን አንድ ቢሊየን ብር ለማስቀረት እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ የሱፍ ኢብራሂም የተቋሙ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በቀረበበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት ከተማ አስተዳደሩ በአመት አንድ ቢሊየን ብር ለህንጻ ኪራይ እያወጣ ይገኛል።
ህንጻዎችን በማስገንባት ይህንን ወጪ ለማስቀረትና ከኪራይ ነጻ ለማድረግ መሬት ተዘጋጅቶ እንቅስቀሴ ተጀምሯል። የህንጻዎቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ መንግስትን ከወጪ በመታደግ ገንዘቡን ለሌሎች ልማቶች እንዲያውል የሚጠቅመው ይሆናል።
የሚገነቡት ህንጻዎች በአንድ አካባቢ በመሆኑ በተቋማት መካከል የሚኖርን የስራ ግንኙነት የሚያፋጥንና ለመረጃና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁ ለትራንስፖርት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል። ከከተማ መስተዳድሩ አገልግሎት የሚፈልጉ ተገልጋዮችም ተቋማቱን በአንድ አካባቢ የሚያገኟቸው በመሆኑ ከውጣ ውረድ ይድናሉም ነው ያሉት።
ባለስልጣኑ ባለቤት አልባ ህንጻዎችን እየለየ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስኪያጁ እስካሁንም ባለቤት አልባ ህንጻዎች መለየታቸውን በመጠቆም በፍርድ ቤት አሳውጆ ተረክቦ ለማስተዳደር በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በራስወርቅ ሙሉጌታ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
********************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለተለያዩ ቢሮዎቹ በየአመቱ ለህንጻ ኪራይ የሚያወጣውን አንድ ቢሊየን ብር ለማስቀረት እየሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን አስታወቀ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ የሱፍ ኢብራሂም የተቋሙ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በቀረበበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት ከተማ አስተዳደሩ በአመት አንድ ቢሊየን ብር ለህንጻ ኪራይ እያወጣ ይገኛል።
ህንጻዎችን በማስገንባት ይህንን ወጪ ለማስቀረትና ከኪራይ ነጻ ለማድረግ መሬት ተዘጋጅቶ እንቅስቀሴ ተጀምሯል። የህንጻዎቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ መንግስትን ከወጪ በመታደግ ገንዘቡን ለሌሎች ልማቶች እንዲያውል የሚጠቅመው ይሆናል።
የሚገነቡት ህንጻዎች በአንድ አካባቢ በመሆኑ በተቋማት መካከል የሚኖርን የስራ ግንኙነት የሚያፋጥንና ለመረጃና ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲሁ ለትራንስፖርት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል። ከከተማ መስተዳድሩ አገልግሎት የሚፈልጉ ተገልጋዮችም ተቋማቱን በአንድ አካባቢ የሚያገኟቸው በመሆኑ ከውጣ ውረድ ይድናሉም ነው ያሉት።
ባለስልጣኑ ባለቤት አልባ ህንጻዎችን እየለየ መሆኑን የተናገሩት ዋና ስራ አስኪያጁ እስካሁንም ባለቤት አልባ ህንጻዎች መለየታቸውን በመጠቆም በፍርድ ቤት አሳውጆ ተረክቦ ለማስተዳደር በሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በራስወርቅ ሙሉጌታ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
አሪፍ ፔይ የተሰኘ የኦንላይን ክፍያ ስርዓት ከብሄራዊ ባንክ ፍቃድ አገኘ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
አሪፍ ፔይ የተሰኘ የኦንላይን ክፍያ ስርዓት ከብሄራዊ ባንክ ፍቃድ አግኝቶ ወደ ስራ መግባቱን አሰታወቀ።
ነጋዴዎች፣ የቢዝነስ ሰዎችና ማንኛውም ተጠቃሚ በኦንላይን ክፍያ መፈፀም የሚያስችላቸውና ደረሰኝ ማግኘት የሚችሉበት የክፍያ ስርዓት ነው ተብሏል።
በተለያዩ አካባቢዎች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለድርሻነት በ3 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር የመነሻ ሃብት ነው ስራውን የጀመረው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ እንደ አሪፍ ፔይ ያሉ የኦንላይን ክፍያ ስርዓቶች የኤሌክትሮኒክስ ንግድን ለማሳለጥ ትልቅ ጠቀሜታ አላቸው ብለዋል።
ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የኦንላይን ክፍያ አማራጮች መበራከት አለባቸው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኢኖቬሽን የታገዘ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት እንዲበራከቱ የስታርት አፕ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለመጽደቅ የሚያስችለው የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በኦንላይን ክፍያ እየፈፀሙ ያሉት ዜጎች ከአጠቃላይ ህዝብ ቁጥር 2 ከመቶው ብቻ መሆናቸውን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*********************
(ኢ ፕ ድ)
አሪፍ ፔይ የተሰኘ የኦንላይን ክፍያ ስርዓት ከብሄራዊ ባንክ ፍቃድ አግኝቶ ወደ ስራ መግባቱን አሰታወቀ።
ነጋዴዎች፣ የቢዝነስ ሰዎችና ማንኛውም ተጠቃሚ በኦንላይን ክፍያ መፈፀም የሚያስችላቸውና ደረሰኝ ማግኘት የሚችሉበት የክፍያ ስርዓት ነው ተብሏል።
በተለያዩ አካባቢዎች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለድርሻነት በ3 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር የመነሻ ሃብት ነው ስራውን የጀመረው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ እንደ አሪፍ ፔይ ያሉ የኦንላይን ክፍያ ስርዓቶች የኤሌክትሮኒክስ ንግድን ለማሳለጥ ትልቅ ጠቀሜታ አላቸው ብለዋል።
ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የኦንላይን ክፍያ አማራጮች መበራከት አለባቸው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኢኖቬሽን የታገዘ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት እንዲበራከቱ የስታርት አፕ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለመጽደቅ የሚያስችለው የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በኦንላይን ክፍያ እየፈፀሙ ያሉት ዜጎች ከአጠቃላይ ህዝብ ቁጥር 2 ከመቶው ብቻ መሆናቸውን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
ሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ 47 ተሽከርካሪዎች ወደ መቀሌ መጓዛቸው ተገለፀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ተጨማሪ ሰብአዊ እርዳታ የጫኑ የተባባሩት መንግስታት ድርጅትና የዓለም የምግብ ፕሮግራም 47 ተሽከርካሪዎች ወደ መቀሌ ማቅናታቸው ተገለጸ።
እነዚህ ተሽከርካሪዎች ምግብ፣ ምግብ ነክና ሌሎች ህይወት አድን ዕርዳታ መጫናቸውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አስታውቋል።
በተጨማሪም ሶስት ቦቴ ነዳጅ የጫኑ መኪናዎችም ወደ መቀሌ ተጉዘዋል ያለው ድርጅቱ፤ ተሽከርካሪዎቹ ያለምንም ችግር እየተጓዙ መሆኑንም ጨምሮ አስታውቋል።
በሀይማኖት ከበደ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ተጨማሪ ሰብአዊ እርዳታ የጫኑ የተባባሩት መንግስታት ድርጅትና የዓለም የምግብ ፕሮግራም 47 ተሽከርካሪዎች ወደ መቀሌ ማቅናታቸው ተገለጸ።
እነዚህ ተሽከርካሪዎች ምግብ፣ ምግብ ነክና ሌሎች ህይወት አድን ዕርዳታ መጫናቸውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ አስታውቋል።
በተጨማሪም ሶስት ቦቴ ነዳጅ የጫኑ መኪናዎችም ወደ መቀሌ ተጉዘዋል ያለው ድርጅቱ፤ ተሽከርካሪዎቹ ያለምንም ችግር እየተጓዙ መሆኑንም ጨምሮ አስታውቋል።
በሀይማኖት ከበደ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
የህብረት ስራ ማህበራት ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በከተማዋ የሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራት ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ
የህብርት ስራ ማህበራት የሚስተዋሉባቸው ችግሮች ስር ነቀል በሆነ አግባብ ለመፍታት አላማ ያደረገ ከተማ አቀፍ የህብረት ስራ ማህበራት የንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህብረት ስራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው አሊ በመርሀ ግብሩ ላይ እንደገለጽት በከተማዋ በተለያዩ ዘርፎች ከ8 ሺህ በላይ የህብረት ስራ ማህበራት ተደራጅተው ይገኛሉ። የህብረት ስራ ማህበራቱ ከአንድ ነጥብ 5 ሚሊዮን አባላት አላቸው።
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ በገንዘብ ቁጠባና ብድር አገልግሎት 1ሺህ 186 ህብረት ስራ ማህበራት በመደራጀት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ በመቆጠብ የከተማውን ነዋሪ የቁጠባ ባህል እንዲዳብር በማድረግ ከተቆጠበው ለማህበሩ አባላትና ለሌሎች ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር የራሳቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
በከተማዋ 148 መሰረታዊ የሸማቾች ህብርት ስራ ማህበራትና 10 የሸማች ህብርት ስራ ዩኒየኖች በመጠቀም ከገጠር ከተማ የገበያ ትስስር በመፍጠር ለአባሉ ብሎም ለመላው የከተማችን ነዋሪ የግብርናና የግብርና ውጤቶችን ተደራሽ እያደረጉ ነው። የኢንዱስትሪ ምርቶች ለተጠቃሚው በማቅረብም የበኩላቸውን ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አቶ ግዛቸው ገልጸዋል፡፡
የኅብረት ስራ ማኅበራቱ የሚጠበቅባቸውን ሚና ከመወጣት አኳያ ለአባላቶቻቸውም ሆነ ለህዝቡ ከሚሰጡት አገልግሎት አንጻር ሲታይ ፤ የብልሹ አሰራርና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በስፋት ይነሳሉ። እነዚህን የዘመናዊነት አሰራርና የአገልጋይነት ችግሮች ለመፍታት ህብረት ስራ ማህበራቱን በአሰራር፤ በአደረጃጀት ፤በግብአት ስር ነቀል ሪፎረም በማድረግ ህብረት ስራ ማህበራቱን ማስተካከል አላማ ያደረገ የንቅናቄ መድረክ መሆኑንም ተናግረዋል።
የመንግስት አመራር አካላት ከፍተኛ ድጋፍ ከታከለበት በማህበራቱ በኩል የሚታዩ ጉድለቶች ለማረምና ማህበራቱን ለተሸለ አገልግሎት ለማብቃት ጉልህ ሚና ስለሚኖረው በተለይ በየደረጃው የሚገኝ አመራር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ ማቅረባቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በከተማዋ የሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራት ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ
የህብርት ስራ ማህበራት የሚስተዋሉባቸው ችግሮች ስር ነቀል በሆነ አግባብ ለመፍታት አላማ ያደረገ ከተማ አቀፍ የህብረት ስራ ማህበራት የንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህብረት ስራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው አሊ በመርሀ ግብሩ ላይ እንደገለጽት በከተማዋ በተለያዩ ዘርፎች ከ8 ሺህ በላይ የህብረት ስራ ማህበራት ተደራጅተው ይገኛሉ። የህብረት ስራ ማህበራቱ ከአንድ ነጥብ 5 ሚሊዮን አባላት አላቸው።
እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ በገንዘብ ቁጠባና ብድር አገልግሎት 1ሺህ 186 ህብረት ስራ ማህበራት በመደራጀት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ በመቆጠብ የከተማውን ነዋሪ የቁጠባ ባህል እንዲዳብር በማድረግ ከተቆጠበው ለማህበሩ አባላትና ለሌሎች ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር የራሳቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
በከተማዋ 148 መሰረታዊ የሸማቾች ህብርት ስራ ማህበራትና 10 የሸማች ህብርት ስራ ዩኒየኖች በመጠቀም ከገጠር ከተማ የገበያ ትስስር በመፍጠር ለአባሉ ብሎም ለመላው የከተማችን ነዋሪ የግብርናና የግብርና ውጤቶችን ተደራሽ እያደረጉ ነው። የኢንዱስትሪ ምርቶች ለተጠቃሚው በማቅረብም የበኩላቸውን ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አቶ ግዛቸው ገልጸዋል፡፡
የኅብረት ስራ ማኅበራቱ የሚጠበቅባቸውን ሚና ከመወጣት አኳያ ለአባላቶቻቸውም ሆነ ለህዝቡ ከሚሰጡት አገልግሎት አንጻር ሲታይ ፤ የብልሹ አሰራርና የመልካም አስተዳደር ችግሮች በስፋት ይነሳሉ። እነዚህን የዘመናዊነት አሰራርና የአገልጋይነት ችግሮች ለመፍታት ህብረት ስራ ማህበራቱን በአሰራር፤ በአደረጃጀት ፤በግብአት ስር ነቀል ሪፎረም በማድረግ ህብረት ስራ ማህበራቱን ማስተካከል አላማ ያደረገ የንቅናቄ መድረክ መሆኑንም ተናግረዋል።
የመንግስት አመራር አካላት ከፍተኛ ድጋፍ ከታከለበት በማህበራቱ በኩል የሚታዩ ጉድለቶች ለማረምና ማህበራቱን ለተሸለ አገልግሎት ለማብቃት ጉልህ ሚና ስለሚኖረው በተለይ በየደረጃው የሚገኝ አመራር አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ ማቅረባቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
በጀርመን የሚዘጋጁ የአፍሪካ ኹነቶችን በአዲስ አበባ ለማዘጋጀት የሚያስችል ምክክር ተካሄደ
**************
(ኢ ፕ ድ)
በጀርመን አዘጋጅነት የሚካሄዱ የአፍሪካ ኹነቶችን በአዲስ አበባ ከተማ ለማዘጋጀት የሚያስችል ምክክር ተካሄደ።
በምክክር መድረኩ ላይ የአፍሪካ ህብረት፣ በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ እና የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር ተሳትፈዋል።
በመድረኩ የተገኙት ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ እንደገለፁት መሰል ሁነቶች ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው።
ኹነቶቹ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ሲከናወኑ ለዝግጅቱ የሚያሰፈልገው ወጪ ሙሉ በሙሉ በአዘጋጆቹ እንደሚሸፈን ተገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፈን አወር በበኩላቸው ጀርመን ኹነቱን ኢትዮጵያ ላይ መከናወኑ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያውን በሁሉም ዘርፍ ያለውን ትብብር እንደሚያጠናክረው ገልፀዋል።
በዳግማዊት ግርማ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️
**************
(ኢ ፕ ድ)
በጀርመን አዘጋጅነት የሚካሄዱ የአፍሪካ ኹነቶችን በአዲስ አበባ ከተማ ለማዘጋጀት የሚያስችል ምክክር ተካሄደ።
በምክክር መድረኩ ላይ የአፍሪካ ህብረት፣ በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ እና የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር ተሳትፈዋል።
በመድረኩ የተገኙት ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ እንደገለፁት መሰል ሁነቶች ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው።
ኹነቶቹ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ሲከናወኑ ለዝግጅቱ የሚያሰፈልገው ወጪ ሙሉ በሙሉ በአዘጋጆቹ እንደሚሸፈን ተገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፈን አወር በበኩላቸው ጀርመን ኹነቱን ኢትዮጵያ ላይ መከናወኑ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያውን በሁሉም ዘርፍ ያለውን ትብብር እንደሚያጠናክረው ገልፀዋል።
በዳግማዊት ግርማ
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼️
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼️
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼️
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼️