ባለፉት ሁለት ቀናት 50 ምግብና ነዳጅ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ከሰመራ ወደ ትግራይ ክልል ተልከዋል
👉 ተጨማሪ 10 የምግብ እርዳታን የያዙ የጭነት ተሽከርካሪዎች ከሰመራ ጉዞ ጀምረዋል፣
👉 በመጀመሪያው ዙር የምግብ ድጋፍን የያዙ 21 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ገብተዋል፣
****************
(ኢ ፕ ድ)
መንግስት በትግራይ ክልል እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ድጋፍ በተገቢው መንገድ አንዲደርስ ለማስቻል የግጭት ማቆም ውሳኔን ማሳለፉ የሚታወስ ነው።ይህንን ተከትሎም የሰብአዊ እርዳታን ወደ ክልሉ ለማድረስ በርካታ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል።
ከእነዚህም መካከል በየቀኑ የሚደረግ የአየር ትራንስፖርትን በማመቻቸት የእርዳታ አቅራቢ ተቋማት አቅም የፈቀደውን ያህል የመድሃኒት፤ የህክምና ቁሳቁስና አልሚ ምግብ እንዲያጓጉዙ ሁኔታዎችን አመቻችቷል።
በየብስ ትራንስፖርትም በመጀመሪያው ዙር የምግብ ድጋፍን የያዙ 21 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ እንዲገቡ ተደርጓል።
ባለፉት ሁለት ቀናት ደግሞ 47 የምግብ ድጋፍ የያዙና 3 ነዳጅ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች በድምሩ 50 የጭነት መኪኖች ከሰመራ ተነስተው ወደ መቀሌ ጉዞ እያደረጉ ነው።
ተጨማሪ 10 የምግብ እርዳታን የያዙ የጭነት ተሽከርካሪዎችም ከሰመራ ጉዞ ጀምረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደርሳቸው ለማድረግ የገባውን ቃል በማክበር ምቹ የሰብአዊ ርዳታ ማጓጓዣ ሁኔታን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።
አለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህንን መንግስት ያቀረበውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወደ ትግራይ የሚደርሰውን የእርዳታ መጠን ከፍ ሊያደርግ ይገባል።
በሌላ በኩል በአስቸጋሪ ሁኔታ ወስጥ የሚገኙት የክልሉ ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደርሳቸው ወራሪው ሃይል አሁንም ከያዛቸው የአፋርና አማራ ክልል አካባቢዎች እንዲወጣና ምቹ የእርዳታ ማስተላለፊያ መስመርን መዘርጋት እንዲቻል አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግ መንግስት ጥሪውን ያቀርባል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን ‼
👉 ተጨማሪ 10 የምግብ እርዳታን የያዙ የጭነት ተሽከርካሪዎች ከሰመራ ጉዞ ጀምረዋል፣
👉 በመጀመሪያው ዙር የምግብ ድጋፍን የያዙ 21 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ገብተዋል፣
****************
(ኢ ፕ ድ)
መንግስት በትግራይ ክልል እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ድጋፍ በተገቢው መንገድ አንዲደርስ ለማስቻል የግጭት ማቆም ውሳኔን ማሳለፉ የሚታወስ ነው።ይህንን ተከትሎም የሰብአዊ እርዳታን ወደ ክልሉ ለማድረስ በርካታ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል።
ከእነዚህም መካከል በየቀኑ የሚደረግ የአየር ትራንስፖርትን በማመቻቸት የእርዳታ አቅራቢ ተቋማት አቅም የፈቀደውን ያህል የመድሃኒት፤ የህክምና ቁሳቁስና አልሚ ምግብ እንዲያጓጉዙ ሁኔታዎችን አመቻችቷል።
በየብስ ትራንስፖርትም በመጀመሪያው ዙር የምግብ ድጋፍን የያዙ 21 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ እንዲገቡ ተደርጓል።
ባለፉት ሁለት ቀናት ደግሞ 47 የምግብ ድጋፍ የያዙና 3 ነዳጅ የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች በድምሩ 50 የጭነት መኪኖች ከሰመራ ተነስተው ወደ መቀሌ ጉዞ እያደረጉ ነው።
ተጨማሪ 10 የምግብ እርዳታን የያዙ የጭነት ተሽከርካሪዎችም ከሰመራ ጉዞ ጀምረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደርሳቸው ለማድረግ የገባውን ቃል በማክበር ምቹ የሰብአዊ ርዳታ ማጓጓዣ ሁኔታን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።
አለም አቀፉ ማህበረሰብም ይህንን መንግስት ያቀረበውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወደ ትግራይ የሚደርሰውን የእርዳታ መጠን ከፍ ሊያደርግ ይገባል።
በሌላ በኩል በአስቸጋሪ ሁኔታ ወስጥ የሚገኙት የክልሉ ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ እንዲደርሳቸው ወራሪው ሃይል አሁንም ከያዛቸው የአፋርና አማራ ክልል አካባቢዎች እንዲወጣና ምቹ የእርዳታ ማስተላለፊያ መስመርን መዘርጋት እንዲቻል አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግ መንግስት ጥሪውን ያቀርባል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን ‼
ከሳዑዲ ለተመለሱ ኢትዮጵያውያን በቤተ መንግስት የኢፍጣር ስነ-ስርዓት ተካሄደ
****
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ከሳዑዲ አረቢያ ለተመለሱ ኢትዮጵያውያን በቤተ መንግስት የኢፍጣር ስነ-ስርዓት ተካሄደ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሳዑዲ ዓረቢያ ለተመለሱ 250 ኢትዮጵያውያን የኢፍጣር እራት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አካሂደዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለብዙ ወራት በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከሳዑዲ እየመለሰ ይገኛል። ዜጎቹ ተጠቃልለው ወደ ሀገራቸው እስኪመለሱ ድረስ ይህን ሥራ ይቀጥላል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
****
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ከሳዑዲ አረቢያ ለተመለሱ ኢትዮጵያውያን በቤተ መንግስት የኢፍጣር ስነ-ስርዓት ተካሄደ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሳዑዲ ዓረቢያ ለተመለሱ 250 ኢትዮጵያውያን የኢፍጣር እራት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አካሂደዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለብዙ ወራት በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከሳዑዲ እየመለሰ ይገኛል። ዜጎቹ ተጠቃልለው ወደ ሀገራቸው እስኪመለሱ ድረስ ይህን ሥራ ይቀጥላል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
አቶ ደመቀ መኮንን የፓርላማ አባላትንና የሕክምና ባለሙያዎችን ካካተተው የእስራኤል የልዑካን ቡድን ጋር ተወያዩ
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የፓርላማ አባላትንና የሕክምና ባለሙያዎችን ያካተተውን የእስራኤል የልዑካን ቡድንን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በእስራኤል የፓርላማ አባል አቶ ጋዲ ይባርከን የተመራው የልዑክ ቡድኑ የፓርላማ አባላትንና የሕክምና ባለሙያዎችን ያካተተ ነው።
የልዑካን ቡድኑ በጎንደር አካባቢ ጉበኝት በማድረግ በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ ደመቀ መኮንን የልዑካን ቡድኑ በዚህ ወሳኝ ወቅት በአገራችን ጉብኝት ማድረጉን አድንቀዋል።
ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት መልሶ ለመገንባት ታሳቢ ያደረገው ይህ የእስራኤል የልዑካን ቡድን ውቅታዊ ጉብኝት፥ የሁለቱን ሀገራት የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑንም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን የልዑካን ቡድኑ በአጭር ጊዜ እቅዱ ቅድሚያ ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቆማት መልሶ መገንባት እና ማደረጃት ላይ ሊሆን እንደሚገባ በውይይታቸው ላይ ትኩረት ሰጥተው አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑ ዘለቄታነት ባለው ዕቅዱ ከጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል እና ከሌሎች የኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ጋር በቅርበት የመስራት ፍላጎት እንዳለው መግለጹንም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼
*****
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የፓርላማ አባላትንና የሕክምና ባለሙያዎችን ያካተተውን የእስራኤል የልዑካን ቡድንን ተቀብለው አነጋግረዋል።
በእስራኤል የፓርላማ አባል አቶ ጋዲ ይባርከን የተመራው የልዑክ ቡድኑ የፓርላማ አባላትንና የሕክምና ባለሙያዎችን ያካተተ ነው።
የልዑካን ቡድኑ በጎንደር አካባቢ ጉበኝት በማድረግ በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ግጭት ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት መልሶ ለመገንባት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ ደመቀ መኮንን የልዑካን ቡድኑ በዚህ ወሳኝ ወቅት በአገራችን ጉብኝት ማድረጉን አድንቀዋል።
ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት መልሶ ለመገንባት ታሳቢ ያደረገው ይህ የእስራኤል የልዑካን ቡድን ውቅታዊ ጉብኝት፥ የሁለቱን ሀገራት የቆየ እና ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑንም ነው አቶ ደመቀ የገለጹት።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን የልዑካን ቡድኑ በአጭር ጊዜ እቅዱ ቅድሚያ ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቆማት መልሶ መገንባት እና ማደረጃት ላይ ሊሆን እንደሚገባ በውይይታቸው ላይ ትኩረት ሰጥተው አንስተዋል።
የልዑካን ቡድኑ ዘለቄታነት ባለው ዕቅዱ ከጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል እና ከሌሎች የኢትዮጵያ የጤና ተቋማት ጋር በቅርበት የመስራት ፍላጎት እንዳለው መግለጹንም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼