"ኅብር ህይወቴ" የተሰኘው የኤሜሪተስ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ግለ ታሪክ መፅሐፍ ተመረቀ
*****************
ለረጅም ዓመታት በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ ምርምር እና ጥናት በማድረግ የሚታወቁት ኤሜሪተስ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በራሳቸው የህይወት ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥነው "ኅብር ሕይወቴ" ግለ ታሪክ መፅሃፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዋናው ግቢ 6 ኪሎ ካምፓስ ራስ መኮንን አዳራሽ ተመርቋል።
መፅሃፉ በ3 ዋና ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን የፕሮፌሰሩን የልጅነት፣ ወጣትነት እና ጉልምስና ዕድሜያቸውን ባሳለፉበት አካዳሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ የህይወት ዑደቶች ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው፡፡
ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በርካታ ጥናታዊ ፅሁፎችን ጨምሮ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መፅሃፍቶችን ለንባብ ያበቁ ሲሆን ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ በተለያዩ ሃገራት ዩኒቨርሲቲዎች ተጋባዥ መምህር በመሆን አስተምረዋል፡፡
"ኅብር ሕይወቴ ግለ ታሪክ" የተሰኝውን መጽሐፍ የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም ወዳጆች ማሕበር፣ የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም፣ የታሪክ ክፍለ ትምህርት፣ የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የውጭ ግንኙነት ክፍል በጋራ በመሆን ነው ያስመረቁት።
*****************
ለረጅም ዓመታት በኢትዮጵያ ታሪክ ዙሪያ ምርምር እና ጥናት በማድረግ የሚታወቁት ኤሜሪተስ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በራሳቸው የህይወት ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥነው "ኅብር ሕይወቴ" ግለ ታሪክ መፅሃፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዋናው ግቢ 6 ኪሎ ካምፓስ ራስ መኮንን አዳራሽ ተመርቋል።
መፅሃፉ በ3 ዋና ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን የፕሮፌሰሩን የልጅነት፣ ወጣትነት እና ጉልምስና ዕድሜያቸውን ባሳለፉበት አካዳሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ የህይወት ዑደቶች ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው፡፡
ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ በርካታ ጥናታዊ ፅሁፎችን ጨምሮ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ መፅሃፍቶችን ለንባብ ያበቁ ሲሆን ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ በተለያዩ ሃገራት ዩኒቨርሲቲዎች ተጋባዥ መምህር በመሆን አስተምረዋል፡፡
"ኅብር ሕይወቴ ግለ ታሪክ" የተሰኝውን መጽሐፍ የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም ወዳጆች ማሕበር፣ የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም፣ የታሪክ ክፍለ ትምህርት፣ የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የውጭ ግንኙነት ክፍል በጋራ በመሆን ነው ያስመረቁት።
👍50👎10❤9
በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ታሪክ ደማቅ ዐሻራ ያኖሩት አንጋፋው የሚዲያ መሪ፡- አቶ አማረ አረጋዊ
*********************
አቶ አማረ አረጋዊ የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌቪዠን ዋና ሥራ አስኪያጅ እና ከሀገሪቱ አንጋፋ የሚዲያ መሪዎች ውስጥ ግንባር ቀደም ናቸው። ከ40 ዓመታት በላይ በጋዜጠኝነት እና በሚዲያ መሪነት ያገለገሉት አቶ አማረ፣ ከኢቲቪ በተጨማሪ በሪፖርተር ጋዜጣ መሥራችነታቸው፣ በኢትዮጵያ የሚዲያ ካውንስል ምሥረታ እና ለጋዜጠኝነት እና ኮሙዩኒኬሽን ዕድገት ባላቸው አበርክቶት ይታወቃሉ።
በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ታሪክ ውስጥ ደማቅ ዐሻራ ያሳረፉት አንጋፋው ጋዜጠኛ እና የሚዲያ መሪ አቶ አማረ አረጋዊ፣ የኢቢሲ አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ምርቃትን ምክንያት በማድረግ የዛሬው የአርዓያ ሰብ አምድ ባለታሪካችን አድርገናቸዋል።
አቶ አማረ ታኅሣሥ 29 ቀን 1947 ዓ.ም ከአባታቸው አቶ አረጋዊ ወ/ኪዳን እና ከእናታቸው ወ/ሮ ዘነበች ገ/ማርያም በመቐለ ከተማ የተወለዱ ሲሆን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በትውልድ ከተማቸው መቐለ ተምረዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid08Eskiqtz522UZ6pL6dDgFsp2V6vHKoj1jyxwmrBg53wKggBUWFQY6aNQwiPytuJkl
*********************
አቶ አማረ አረጋዊ የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌቪዠን ዋና ሥራ አስኪያጅ እና ከሀገሪቱ አንጋፋ የሚዲያ መሪዎች ውስጥ ግንባር ቀደም ናቸው። ከ40 ዓመታት በላይ በጋዜጠኝነት እና በሚዲያ መሪነት ያገለገሉት አቶ አማረ፣ ከኢቲቪ በተጨማሪ በሪፖርተር ጋዜጣ መሥራችነታቸው፣ በኢትዮጵያ የሚዲያ ካውንስል ምሥረታ እና ለጋዜጠኝነት እና ኮሙዩኒኬሽን ዕድገት ባላቸው አበርክቶት ይታወቃሉ።
በኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ታሪክ ውስጥ ደማቅ ዐሻራ ያሳረፉት አንጋፋው ጋዜጠኛ እና የሚዲያ መሪ አቶ አማረ አረጋዊ፣ የኢቢሲ አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ምርቃትን ምክንያት በማድረግ የዛሬው የአርዓያ ሰብ አምድ ባለታሪካችን አድርገናቸዋል።
አቶ አማረ ታኅሣሥ 29 ቀን 1947 ዓ.ም ከአባታቸው አቶ አረጋዊ ወ/ኪዳን እና ከእናታቸው ወ/ሮ ዘነበች ገ/ማርያም በመቐለ ከተማ የተወለዱ ሲሆን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በትውልድ ከተማቸው መቐለ ተምረዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid08Eskiqtz522UZ6pL6dDgFsp2V6vHKoj1jyxwmrBg53wKggBUWFQY6aNQwiPytuJkl
👍47👎9❤5👏1
ተወዳጁ ሙዚቀኛ ብስራት ሱራፌል ''ማለፊያ'' የተሸኘ ሁለተኛ አልበሙን ለአድማጭ ሊያደርስ ነው
*********************
ተወዳጁ ሙዚቀኛ ብስራት ሱራፌል ''ማለፊያ'' የተሸኘ ሁለተኛ አልበሙን ለአድማጭ ሊያደርስ ነው።
በሀገሪቱ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ በአጭር ጊዜ ተደማጭና ታዋቂ ለመሆን የቻለውና የበርካታ ግጥምና ዜማ ደራሲ የሆነው ድምፃዊ ብስራት ሱራፌል ሁለተኛ አልበሙን ከኤላ ቲቪ ጋር በመሆን የፊታችን ሀምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም ለአድማጭ እንደሚያደርስ ዛሬ በሀገር ፍቅር ቴአትር አዳራሽ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ።
ከዚህ ቀደም ቃል በቃል የተሰኘ የመጀመሪያ አልበሙንና የተለያዩ ነጠላ ዜማዎችን በመስራት በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ተወዳጅና ታዋቂ ለመሆን የቻለው አርቲስት ብስራት ሱራፌል ''ማለፊያ'' የተሰኘው አዲሱ አልበም ለ 4 አመታት ያህል የተለፋበትና ከ20 በላይ በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ስመ ጥር የሆኑ ባለሙያዎች በግጥም በዜማ እንዲሁም በቅንብር የተሳተፉበት መሆኑ ተገልጿል።
https://www.facebook.com/EBCmezenagna/posts/pfbid02ts9tHcaPAEZuuycwubxTDvjpUdukm5nkJfbM83PABM6WMpeEieXZT5AaaGU43nq3l
*********************
ተወዳጁ ሙዚቀኛ ብስራት ሱራፌል ''ማለፊያ'' የተሸኘ ሁለተኛ አልበሙን ለአድማጭ ሊያደርስ ነው።
በሀገሪቱ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ በአጭር ጊዜ ተደማጭና ታዋቂ ለመሆን የቻለውና የበርካታ ግጥምና ዜማ ደራሲ የሆነው ድምፃዊ ብስራት ሱራፌል ሁለተኛ አልበሙን ከኤላ ቲቪ ጋር በመሆን የፊታችን ሀምሌ 14 ቀን 2015 ዓ.ም ለአድማጭ እንደሚያደርስ ዛሬ በሀገር ፍቅር ቴአትር አዳራሽ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ።
ከዚህ ቀደም ቃል በቃል የተሰኘ የመጀመሪያ አልበሙንና የተለያዩ ነጠላ ዜማዎችን በመስራት በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ተወዳጅና ታዋቂ ለመሆን የቻለው አርቲስት ብስራት ሱራፌል ''ማለፊያ'' የተሰኘው አዲሱ አልበም ለ 4 አመታት ያህል የተለፋበትና ከ20 በላይ በሙዚቃው ኢንዱስትሪ ስመ ጥር የሆኑ ባለሙያዎች በግጥም በዜማ እንዲሁም በቅንብር የተሳተፉበት መሆኑ ተገልጿል።
https://www.facebook.com/EBCmezenagna/posts/pfbid02ts9tHcaPAEZuuycwubxTDvjpUdukm5nkJfbM83PABM6WMpeEieXZT5AaaGU43nq3l
👍24👎11❤10
ወደ ጎረቤት ሀገር ሊሻገር የነበር አደንዛዥ እፅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ደረቅ ጫት እና ነዳጅ በቁጥጥር ስር ዋለ
**********************
በሁመራ ከተማ፣ ዲማ፣ ባዕከር እና ራዊያን ኬላ በተደረገ ፍተሻ ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ሊሻገር የነበረ አደንዛዥ ዕፅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ደረቅ ጫት፣ እና ነዳጅ በመከላከያ ሠራዊቱ በቁጥጥር ስር ዋለ።
እቃዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሕብረተሰቡ ለህግ አካላት ባደረገው ጥቆማ በመነሻነት በተደረገ ክትትል መሆኑን ሌተናል ኮሎኔል ግርማ በድዬ ተናግረዋል።
ሠራዊቱ በኬላዎችም ይሁን በሌላ መንገድ የሚዘዋወሩ ህገ-ወጥ ዝውውሮችን በመቆጣጠር ሀገራዊ ግዴታውን እየተወጣ እንደሆነም ሌተናል ኮሎኔል ግርማ ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0JLTdtK9S9XsAyt17BFY3Y9KZBe89AEscGoMLhkNTiKA3eYQsHUpinSkiaKNndTEPl
**********************
በሁመራ ከተማ፣ ዲማ፣ ባዕከር እና ራዊያን ኬላ በተደረገ ፍተሻ ወደ ጎረቤት ሀገር ሱዳን ሊሻገር የነበረ አደንዛዥ ዕፅ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ደረቅ ጫት፣ እና ነዳጅ በመከላከያ ሠራዊቱ በቁጥጥር ስር ዋለ።
እቃዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሕብረተሰቡ ለህግ አካላት ባደረገው ጥቆማ በመነሻነት በተደረገ ክትትል መሆኑን ሌተናል ኮሎኔል ግርማ በድዬ ተናግረዋል።
ሠራዊቱ በኬላዎችም ይሁን በሌላ መንገድ የሚዘዋወሩ ህገ-ወጥ ዝውውሮችን በመቆጣጠር ሀገራዊ ግዴታውን እየተወጣ እንደሆነም ሌተናል ኮሎኔል ግርማ ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0JLTdtK9S9XsAyt17BFY3Y9KZBe89AEscGoMLhkNTiKA3eYQsHUpinSkiaKNndTEPl
👍67❤19👎18👏6
ትዊተር ሜታን ፍርድ ቤት ሊያቆመው መሆኑን አስታወቀ
******************
የፌስቡክ እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ “ትሪድስ” የተሰኘ እና የትዊተር ተቀናቃኝ የሆነ አዲስ መተግበሪያን ይፋ ካደረገ በኋላ ትዊተር ኩባንያውን ሊከስ መሆኑን አስታውቋል።
ሜታ የቀድሞ ሠራተኞቼን በመቅጠር የንግድ ምሥጢሮቼ ላይ ስርቆት ፈጽሟል ሲል ትዊተር በጠበቃው በኩል ለሜታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ የክስ ደብዳቤ መላኩ ታውቋል።
የትዊተር ባለቤት የኤለን መስክ ጠበቃ የሆኑት አሌክስ ስፒሮ የጻፉት ደብዳቤ “ሜታ ስልታዊ እና ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ የትዊተርን የንግድ ምሥጢሮች እና ሌሎች የአዕምሮአዊ ንብረቶችን አለአግባብ በመዝረፍ ላይ መሰማራቱን” የሚገልጽ ነው።
https://www.facebook.com/photo/?fbid=657377266416456&set=a.637938368360346
******************
የፌስቡክ እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ “ትሪድስ” የተሰኘ እና የትዊተር ተቀናቃኝ የሆነ አዲስ መተግበሪያን ይፋ ካደረገ በኋላ ትዊተር ኩባንያውን ሊከስ መሆኑን አስታውቋል።
ሜታ የቀድሞ ሠራተኞቼን በመቅጠር የንግድ ምሥጢሮቼ ላይ ስርቆት ፈጽሟል ሲል ትዊተር በጠበቃው በኩል ለሜታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማርክ ዙከርበርግ የክስ ደብዳቤ መላኩ ታውቋል።
የትዊተር ባለቤት የኤለን መስክ ጠበቃ የሆኑት አሌክስ ስፒሮ የጻፉት ደብዳቤ “ሜታ ስልታዊ እና ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ የትዊተርን የንግድ ምሥጢሮች እና ሌሎች የአዕምሮአዊ ንብረቶችን አለአግባብ በመዝረፍ ላይ መሰማራቱን” የሚገልጽ ነው።
https://www.facebook.com/photo/?fbid=657377266416456&set=a.637938368360346
👍68👎18❤11
በተጠናቀቀው በጀት በአዲስ አበባ ከ416 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
**********************************
በ2015 በጀት በመዲናዋ ከ416 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ሶስተኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ሁለተኛ ዓመት የስራ ዘመን አራተኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤ እያካሄደ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ ለከተማዋ ምክር ቤት የአስተዳደሩን የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት በማቅረብ ላይ ናቸው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0Md2pKCoFzcPqtxQvHoxvqR4EULq5besoEH7iskftJsZtqahz2eJHMV6oEDUQpj8jl
**********************************
በ2015 በጀት በመዲናዋ ከ416 ሺህ በላይ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ሶስተኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ሁለተኛ ዓመት የስራ ዘመን አራተኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤ እያካሄደ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አበቤ ለከተማዋ ምክር ቤት የአስተዳደሩን የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት በማቅረብ ላይ ናቸው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0Md2pKCoFzcPqtxQvHoxvqR4EULq5besoEH7iskftJsZtqahz2eJHMV6oEDUQpj8jl
👎96👍70❤15👏4
ለድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው የዕውቅና ሽልማት ተሰጠ
*********************
ለ15ኛ ጊዜ የተካሄደው የአማራ ክልል ባህል እና ኪነ ጥበባት ፌስቲቫል ለድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ)፣ ለጌትነት እንየው እና ለአበበ ብርሃኔ የዕውቅና ሽልማት ሰጥቷል።
ገና በልጅነት ዘመኗ ጀመሮ ስለ ሀገር እና ስለ ሀገር ፍቅር በማቀንቀን በብዙዎች ልብ ውስጥ የገባችው እጅጋየሁ ሽባባው ላደረገችው አስተዋፅዖ ነው ሽልማት የተበረከተላት። ጂጂ ለሀገር ባቀነቀነቻቸው ዘፈኖቿ ብዙዎችን አስተሳስራለች።
https://www.facebook.com/EBCmezenagna/posts/pfbid02SnbWBc4CbYiUpgBLpJ4FFYnwvGknw4tHkXYPc4hPuVdXChXZimyNwBYRzLpQzxenl
*********************
ለ15ኛ ጊዜ የተካሄደው የአማራ ክልል ባህል እና ኪነ ጥበባት ፌስቲቫል ለድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ)፣ ለጌትነት እንየው እና ለአበበ ብርሃኔ የዕውቅና ሽልማት ሰጥቷል።
ገና በልጅነት ዘመኗ ጀመሮ ስለ ሀገር እና ስለ ሀገር ፍቅር በማቀንቀን በብዙዎች ልብ ውስጥ የገባችው እጅጋየሁ ሽባባው ላደረገችው አስተዋፅዖ ነው ሽልማት የተበረከተላት። ጂጂ ለሀገር ባቀነቀነቻቸው ዘፈኖቿ ብዙዎችን አስተሳስራለች።
https://www.facebook.com/EBCmezenagna/posts/pfbid02SnbWBc4CbYiUpgBLpJ4FFYnwvGknw4tHkXYPc4hPuVdXChXZimyNwBYRzLpQzxenl
👍99❤17👏12👎10
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰላም ልዑካን መቐሌ ገቡ
***********************************************
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰላም ልዑካን ትግራይ ክልል መዲና መቐሌ ገብተዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የሀገር ሽማግሌዎች መቐሌ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት ሲደርሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በመቐሌ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት ተገናኝተው መወያየታቸውን የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት መረጃ ያመለክታል።
***********************************************
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰላም ልዑካን ትግራይ ክልል መዲና መቐሌ ገብተዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የሀገር ሽማግሌዎች መቐሌ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት ሲደርሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በመቐሌ አሉላ አባ ነጋ ኤርፖርት ተገናኝተው መወያየታቸውን የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት መረጃ ያመለክታል።
👍62👎17❤8👏5