የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ማታ ጀምሮ መመልከት ይችላሉ፡- የትምህርት ሚኒስቴር
**************************************
የትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በማጠናቀቅ ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ማታ ጀምሮ መመልከት እንደሚችሉ አስታውቋል።
በዚህም ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ እሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ በ https://result .ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ እንደሚችሉ ተገልጿል።
በመውጫ ፈተናው የሚፈለገውን የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ፈተናውን በየስድስት ወሩ ደጋግመው መውሰድ እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።
የመውጫ ፈተናው ከመሰጠቱ አስቀድሞ ተመራቂ ተማሪዎች ከፈተና ስርዓቱ ጋር እንዲለማመዱ የሙከራ እና የሞዴል ፈተና እንዲወስዱ መደረጉ ይታወሳል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከተጀመሩ ሪፎርሞች አንዱ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
**************************************
የትምህርት ሚኒስቴር ከሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በማጠናቀቅ ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ማታ ጀምሮ መመልከት እንደሚችሉ አስታውቋል።
በዚህም ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ እሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ በ https://result .ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ እንደሚችሉ ተገልጿል።
በመውጫ ፈተናው የሚፈለገውን የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ፈተናውን በየስድስት ወሩ ደጋግመው መውሰድ እንደሚችሉም ነው የተገለፀው።
የመውጫ ፈተናው ከመሰጠቱ አስቀድሞ ተመራቂ ተማሪዎች ከፈተና ስርዓቱ ጋር እንዲለማመዱ የሙከራ እና የሞዴል ፈተና እንዲወስዱ መደረጉ ይታወሳል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከተጀመሩ ሪፎርሞች አንዱ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
👍62👎22❤20👏3
ተጀመረ
ነገን ዛሬ እንትከል!!!
**********
ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት እለት ነው!!
መላው ኢትዮጵያውያንም በያሉበት ስፍራ ጀንበር ወጥታ እስከምትገባ የአረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ነገን ዛሬ ይተክላሉ።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid026uZPSxKbRsRW4tXw5gcg6rZFkodYpZUCTGhfqWLhBmLk7wtbFfbpRpizhUh3xukkl
ነገን ዛሬ እንትከል!!!
**********
ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት እለት ነው!!
መላው ኢትዮጵያውያንም በያሉበት ስፍራ ጀንበር ወጥታ እስከምትገባ የአረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ነገን ዛሬ ይተክላሉ።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid026uZPSxKbRsRW4tXw5gcg6rZFkodYpZUCTGhfqWLhBmLk7wtbFfbpRpizhUh3xukkl
👍54👎30❤10👏8
ችግኝ መትከላችንን በጠዋት ጀምረናል፤ እስከምሽት ይቀጥላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
********************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ ማለዳ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።
በማለዳ በዝናብ ወጥታችሁ አረንጓዴ አሻራችሁን እያሳረፋችሁ ለምትገኙ ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ምስጋናችን ይድረስ ብለዋል።
ዛሬ ኢትዮጵያውያን በህብረት ታሪክ የምንሰራበት ቀን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ዛሬ ለኛ ቀላል የሚመስለው ጉዳይ ብዙዎች የከበዳቸው እና የማይችሉት ነው ብለዋል።https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid08HimLAqS82RNYbUFa3PsVxCt3AYWZyDw1ZZp2qJiQUuYLqgKQ1YT935AVdztfNb4l
********************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ ማለዳ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል።
በማለዳ በዝናብ ወጥታችሁ አረንጓዴ አሻራችሁን እያሳረፋችሁ ለምትገኙ ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ ምስጋናችን ይድረስ ብለዋል።
ዛሬ ኢትዮጵያውያን በህብረት ታሪክ የምንሰራበት ቀን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ዛሬ ለኛ ቀላል የሚመስለው ጉዳይ ብዙዎች የከበዳቸው እና የማይችሉት ነው ብለዋል።https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid08HimLAqS82RNYbUFa3PsVxCt3AYWZyDw1ZZp2qJiQUuYLqgKQ1YT935AVdztfNb4l
❤34👍33👎27
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የ500 ሚልዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ከጽ/ቤቱ ሰራተኞች እና በከተማው ከሚኖሩ አካል ጉዳተኞች ጋር ዛሬ ማለዳ የአፕል ችግኞችን በመትከል አስጀመሩ።
👍45❤24👎22👏1
ከማለዳው 12 ሰዓት እስከ 3፡30 ሰዓት ድረስ 147 ሚሊዮን 965 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል፡- የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት
****************
ከ9 ሺህ በላይ የችግኝ ጣቢያዎች አሁንም መረጃዎችን ወደ ማዕከሉ እየላኩ እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ገልጸዋል።
ከሁነቶች መከታተያ ክፍል (situation room) የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ፤ ዜጎች በሁሉም የሃገሪቱ ክፍል በንቃት እየተሳተፉ ነው ብለዋል።
****************
ከ9 ሺህ በላይ የችግኝ ጣቢያዎች አሁንም መረጃዎችን ወደ ማዕከሉ እየላኩ እንደሚገኝ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ገልጸዋል።
ከሁነቶች መከታተያ ክፍል (situation room) የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚንስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ፤ ዜጎች በሁሉም የሃገሪቱ ክፍል በንቃት እየተሳተፉ ነው ብለዋል።
👍47👎16❤11👏1
የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተሳትፎ በዛሬው የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ
👍76👎17❤16👏4