EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) – Telegram
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
138K subscribers
38.3K photos
462 videos
80 files
13.1K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
የኢትዮጵያ ህልም የነበረው ኅብረት ተሳክቷልን?
****************

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና በቅኝ ግዛት ሥር ለነበሩት ሀገራት ነጻነት የከፈለችው ዋጋ ውድ ነው፡፡ ነጻነቷን ጠብቃ የኖረችው ኢትዮጵያ ብቻዋን የመንግሥታቱ ማኅበር አባል በነበረችበት ወቅት የአውሮፓውያንን የግፍ ወረራ አውግዛለች፤ ብቻዋንም በፍትህ አደባባይ ቆማለች፡፡

የኢትዮጵያ የፍትህ አደባባይ ጩኸት የገለጠው የአውሮፓውያን ግፍ አውዳሚው የሁለተኛ ዓለም ጦርነት እንዲከሰት አድርጓል፡፡ ይሁንና ከታሪክ ያልተማረው ዓለም አሁንም ኢትዮጵያ፣ የአፍሪካን እና የጭቁን ሕዝቦችን ጩኸት እየሰማ ባለመሆኑ ዓለም መከራ ውስጥ እንድትኖር አድርጓታል፡፡

ኢትዮጵያ የዓለም ኅብረቶችን መሥራች ሆና በአባልነት የምትቀላቀለው በዓለም ላይ ፍትህ እንዲሰፍን፣ ጉልበተኞች አቅመ ቢሶችን እንዳይጨፈልቁ እና ሁሉም የዓለም ሕዝብ በእኩልነት የመኖር መብቱ እንዲከበርለት ነው፡፡

ለዚህም ነው ራሷ ነጻነቷን ስላስከበረች በቃ ብላ ያልተቀመጠችው፡፡ አፍሪካውያን ወንድሞቿ ነጻ ሳይወጡ ነጻነቷ ሙሉ ስለማይሆን አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲሆኑ የታገለችው፡፡ የዓለምን ፍትህ የማይሻው የምዕራባውያኑ ጎራ ይህን የኢትዮጵያን ጥረት ለማሰናከል እና አፍሪካን ድምጽ አልባ ለማድረግ ዛሬም ኢ-ፍትሃዊ ጫናውን እንደቀጠለ ነው፡፡

ኢትዮጵያ አፍሪካ ነጻነቷን እንድታገኝ ካደረገቻቸው ትግሎች ጎን ለጎን አፍሪካውያን ኅብረት ፈጥረው የሚደርስባቸውን ጫና እንዲቋቋሙ እና ሕዝቦቻቸው ወደ ተሻለ ህይወት እንዲሸጋገሩ ስትሰራ ቆይታለች፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0taa67HvPawF3sNSrRCjMEQVw2szFxEWgwjPzvxoA34xN6B3dwGcgNXeC3RyVzYPFl
👍6512👏4
የኢትዮጵያ ሬድዮ ለመላው አፍሪካውያን ድምጽ ሆኖ ያገለገለ ነው፡- ጋዜጠኛ እና የታሪክ ፀሀፊ ጥበቡ በለጠ
******************

"ሬድዮ ለፀረ ቅኝ ግዛት" ትግል በሚል ሀሳብ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ ያደረጉት ጋዜጠኛ እና የታሪክ ፀሀፊው ጥበቡ በለጠ፤ የኢትዮጵያ ሬድዮ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያንም በተለያዩ ቋንቋዎች ድምጽ ሆኖ ያገለገለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሬድዮ ለአፍሪካ ነጻነት ትልቅ ሚና መጫወቱን ያወሱት አቶ ጥበቡ፤ የኢትዮጵያ ሬድዮ ወደ ስራ ሲገባ መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ስር የወደቀበት እና ነጻነት የሚናፈቅበት ወቅት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ፤ በኢትዮጵያ ሬድዮ አማካኝነት የነጻነት ድምጽ ማሰማት መቻሏን የገለጹት አቶ ጥበቡ፤ የኢትዮጵያ ሬድዮ ለነጻነት ብስራት መታገያ እና ማታገያ ሆኖ መቆየቱንም አቶ አክለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የሬድዮ ቴክኖሎጂን ያመጣችበት እና ያሳደገችበት ጊዜ በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ነው የሚሉት ባለሙያው፤ ከ1928 በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ የጣሊያን ወረራ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ከወረራው ማግስት ጀምሮም ጣሊያኖች ኢትዮጵያ ያቋቋመችውን ሬድዮ በመዝጋት የራሳቸውን የፕሮፓጋንዳ ማሽን መፍጠራቸውን አውስተው፤ ኢትዮጵያውያ ግን ለዚህ እጅ ባለመስጠት በሌሎች የህትመት ውጤቶች ለፀረ ቅኝ ግዛት ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ይሄንን ተከትሎ ኢትዮጵያ ከጦርነቱ በኋላ፤ በኮሚዮኒኬሽንም ሆነ በጦርነት በዲፕሎማሲው ድል ያደረገችበት እንደነበር ገልፀዋል፡፡https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid032td8LeRRyVsa8gLgPyWfpqb6jSkGCuwU6tsDFYnmpfjUzsaHwDmZg5hj66xihb4Xl
👍37👎53👏1
Live stream finished (9 hours)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ እና ከፖርቱጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
*********************

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲልቪ ባይፖ-ተሞን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

በተመሳሳይ ሚኒስትሩ ከፖርቱጋል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጃኦ ጎሜዝ ክራቪኝዎ ጋር በሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

አምባሳደር ታዬ ኢትዮጵያ ከፖርቱጋል ጋር በቱሪዝም፣ በትምህርት፣ በንግድ እና በኢንቬስትመንት ዘርፎች ተባብራ መስራት ትፈልጋለች ብለዋል።

የፖርቱጋሉ ሚኒስትር በበኩላቸው አገራቸው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ትግበራን እንደምትደግፍ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍48👏87
ከነገ ጀምሮ የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ እስኪጠናቀቅ ለአሽከርካሪዎች ዝግ የሚሆኑ መንገዶች
************************

37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 44ኛው የሚኒስትሮች ስራ አስፈፃሚ ም/ቤት ስብሰባ በሰላምና በስኬት ለማጠናቀቅ እንዲቻል በሚከናወነው የፀጥታ ስራ እና የትራፊክ ፍሰቱ የተሳለጠ እንዲሆን አሽከርካሪዎች ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠይቋል።

በዚሁ መሠረት ከነገ ሐሙስ የካቲት 7 ቀን ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅ፡-
• ከፓርላማ መብራት - በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - መስቀል አደባባይ - ፍላሚንጎ - ኦምሎፒያ - ወሎ ሰፈር - ጃፓን ኤምባሲ - ፍሬንድ ሺፕ - ቦሌ ቀለበት መንገድ - ኤርፖርት
• ከፓርላማ መብራት - በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት - ፍልውሃ - ብሔራዊ ቴአትር - ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ሕብረት አዳራሽ ዙሪያ
• ከፓርላማ መብራት - ብሔራዊ ቤተ-መንግሥት - ወዳጅነት ፓርክ - ንግድ ማተሚያ ቤት - ሞናርክ ሆቴል - ቴዎድሮስ አደባባይ - ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል - ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን - ብሔራዊ ቴአትር - ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ሕብረት ባሉ መንገዶች እንግዶች ሲያልፉ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለእንግዶቹ ቅድሚያ በመስጠት ተባባሪ እንዲሆኑ እና ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ አሳስቧል።

https://ebc.et/newsdetails.aspx?newsid=5856
👍548👎4
የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን ጨምሮ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ
*************************

በጉብኝት መርሐ ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፣ የሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የሃይማኖት ተቋማት መሪዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ ለተገኙ ታዳሚዎች በዓድዋ ጦርነት የቀደሙ አባቶች ለነጻነት ስለከፈሉት መስዋዕትነት፣ የትግል ሂደት እንዲሁም ስለድል መታሰቢያው አጠቃላይ ይዘት ማብራሪያ መሰጠቱን ኢዜአ ዘግቧል።

በዚያው በዓድዋ ድል መታሰቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ የ44ኛው የሕብረቱ የአስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ ተሳታፊ ለሆኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ሌሎች እንግዶች የእራት ግብዣ ማድረጋቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍3711👏5👎1
ሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና በዛሬው ዕለት በጤና ትምህርት ፕሮግራሞች መሰጠት መጀመሩን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
************************

በዚሁ መሠረት ዛሬ ጠዋት 15 ሺህ 440 ተማሪዎች በ23 የጤና ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን፤ ከሰዓት 14 ሺህ 807 ተማሪዎች በ13 ፕሮግራሞች ተፈትነዋል።

የመውጫ ፈተናው በሁሉም የፈተና ማዕከላት (ከተሞች) በመሰጠት ላይ ሲሆን፤ የፈተና አሰጣጡን ፍትሃዊነትና ተዓማኒነት ለማስጠበቅ እንዲሁም አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ የተመደቡ ታዛቢዎችም በየተመደቡባቸው ተቋማት በመገኘት ስራ መጀመራቸው ተገልጿል።

ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተናው በ47 የመንግሥት ተቋማት በ84 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን፤ በመንግሥትና በግል ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑትን ጨምሮ 149 ሺህ 145 ተፈታኞች በ204 የፈተና ፕሮግራሞች እንደሚፈተኑ ተጠቁሟል።

ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተናው የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍579👎6👏3
"በእኛ ሁኔታ የሚያስፈልገን ልማት ነው፣ የሚያስፈልገን እርሻ ነው፣ የሚያስፈልገን ራስን መመገብ እና የተረፈውን ሸጦ መጠቀም ነው። የማያስፈልገን ደግሞ መባላት ነው።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍10026👎15
"የጎበኘናቸው የልማት ስራዎች ለህዝቡ ዕድገት ወሳኝ በመሆናቸው በቅርብ ተከታትለን ለፍፃሜ እናደርሳቸዋለን" - አቶ ተመስገን ጥሩነህ
**********

በአማራ ክልል ጉብኝት የተደረገባቸው የልማት ስራዎች ለህዝቡ ዕድገት ወሳኝ በመሆናቸው የቅርብ ክትትል በማድረግ ለፍፃሜ ለማድረስ አንደሚሰራ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፤ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል።

በአማራ ክልል በነበራቸው ቆይታ ከጠቅላላ የክልሉ አመራር ጋር በፀጥታ እና በልማት ስራዎች ዙሪያ ያደረጓቸው ውይይቶች ማርሽ ቀያሪ እንደነበሩ ጠቅሰዋል።

"የጎበኘናቸው የልማት ስራዎችም ለክልሉ ህዝብ ዕድገት ወሳኝ በመሆናቸው በቅርብ ተከታትለን ለፍፃሜ እናደርሳቸዋለን" ሲሉም ገልጸዋል።
👍6120👎5👏2
በአዳማ ከተማ ለሽብር ወንጀል ሊውል የነበረ በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ተያዘ
**************

በአዳማ ከተማ ለሽብር ወንጀል ሊውል የነበረ በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ እና ጥይት በፍተሻና በሕዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ዋለ።

በአዳማ ከተማ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በከተማው በተለያዩ ጊዜያት የሽብር ተግባር ለመፈፀም መነሻቸውን አዋሽ ሰባት፣ ሰበታ እና ሌሎች አካባቢዎች በማድረግ በተሽከርካሪ ታግዘው ሕገ-ወጥ መሣሪያውን ወደ አዲስ አበባ ከተማ እና ወደ ሌሎች አካባቢዎች በማዘዋወር የሽብር ተግባር ለመፈፀም የሞከሩ አሸባሪዎችንና ተባባሪዎቻቸውን ከህብረተሰቡ በተገኘ ጥቆማ እና በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ በቁጥጥር ስራ መዋል መቻሉ ተጠቅሷል፡፡

በዚህም 61 ቦንብ፣ 6 ሺህ የክላሽንኮቭ ጠመንጃ ጥይት፣ 4 ሺህ 983 የሽጉጥ ጥይት፣ 1 ሺህ 879 የብሬን ጥይት፣ 17 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 18 የተለያየ አይነት ሽጉጥ፣ ዘጠኝ የብሬን ሸንሸን (ሰንሰለት)፣ አንድ ስናይፐር፣ አንድ ላውንቸር፣ ሁለት ቁንቡላ፣ አንድ የጦር ሜዳ መነጽር እና 242 ሺህ 220 ብር መያዙን የአዳማ ከተማ ፖሊስ ገልጿል።

ህገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችንና ጥይቶችን ለሽብር ቡድኑ ሊያስተላልፉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች እና የመኪናው ሾፌርም ከነ-ኤግዚብቱ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዳማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ጠቁሟል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02E48btinTYvnD7w27AFXY2qWzLECSxVXdHU4TykT5YxuAuSCgfJJ4HesMdwsyhtKul
👍6012👏7