"ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነት እና ክብር" በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ የህዝብ መድረክ እየተካሄደ ነው
**********************
መድረኩን የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ፣ የአፋር ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኤሌማ አቡበከር እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ እየመሩ ይገኛሉ።
በአካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ከህብረተሰቡ ጋር መወያየት የመድረኩ ዓላማ እንደሆነ ተገልጿል ።
በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን እና የከተማ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከከተማው የተለያዩ የማኅበራዊ መሠረቶች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎችም እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
በትዕግስቱ ቡቼ
**********************
መድረኩን የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ፣ የአፋር ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኤሌማ አቡበከር እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ረዳት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ዮሐንስ በየነ እየመሩ ይገኛሉ።
በአካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ከህብረተሰቡ ጋር መወያየት የመድረኩ ዓላማ እንደሆነ ተገልጿል ።
በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን እና የከተማ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከከተማው የተለያዩ የማኅበራዊ መሠረቶች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎችም እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
በትዕግስቱ ቡቼ
👍40❤2
በመዲናዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለክልሎችም ተሞክሮ የሚሆኑ ናቸው - አቶ አረጋ ከበደ
********************
በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለክልሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ እና የግብርና ሚኒስትሩ ከጎበኟቸው ፕሮጀክቶች መካከል፤ የለሚ ኩራ የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከል፣ የእንስሳት ልማት እና ልህቀት ማዕከል፣ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶ እና ማበልፅጊያ ማዕከል እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች እና ታላላቅ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ርዕሰ መሥተዳድሩ ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡት የልማት ስራዎች የኑሮ ውድነቱን ከማቃለል አንጻር ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ማመላከታቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
********************
በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ለክልሎችም ተሞክሮ እንደሚሆኑ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ተናግረዋል፡፡
የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ የተገነቡ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ እና የግብርና ሚኒስትሩ ከጎበኟቸው ፕሮጀክቶች መካከል፤ የለሚ ኩራ የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከል፣ የእንስሳት ልማት እና ልህቀት ማዕከል፣ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶ እና ማበልፅጊያ ማዕከል እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ይገኙበታል፡፡
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች እና ታላላቅ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን ርዕሰ መሥተዳድሩ ገልጸዋል፡፡
በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡት የልማት ስራዎች የኑሮ ውድነቱን ከማቃለል አንጻር ጉልህ ሚና እንዳላቸውም ማመላከታቸውን ከከንቲባ ጽ/ቤት የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍30❤5👎1
"ዛሬ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ አቡነ ማትያስ ጋር በመሆን በኮሪደር ልማት ምክንያት በፈረሱ ቤቶች ምትክ በቤተክርስቲያኒቱ የሚገነባ ህንፃ የመሠረተ ድንጋይ አስቀምጠናል።
ቤተ ክህነት የከተማውን ልማት ሥራ በላቀ ሁኔታ በመደገፍ እና ለኮሪደር ልማት ስራዎች መጀመር፤ በማፍረስ ሂደትም ሆነ መልሶ በመገንባት ሂደት እንዲሁም ህንፃዎችን በማደስ ላደረገችው ተሳትፎ እና ተግባራዊ የሆነ ምላሽ ከልቤ ለማመስገን እወዳለሁ።
በዚህ አጋጣሚ ከቤተክርስቲያንቱ ለቀረበልኝ ምስጋናም እጅግ በጣም አድርጌ አመሰግናለሁ ።"
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ቤተ ክህነት የከተማውን ልማት ሥራ በላቀ ሁኔታ በመደገፍ እና ለኮሪደር ልማት ስራዎች መጀመር፤ በማፍረስ ሂደትም ሆነ መልሶ በመገንባት ሂደት እንዲሁም ህንፃዎችን በማደስ ላደረገችው ተሳትፎ እና ተግባራዊ የሆነ ምላሽ ከልቤ ለማመስገን እወዳለሁ።
በዚህ አጋጣሚ ከቤተክርስቲያንቱ ለቀረበልኝ ምስጋናም እጅግ በጣም አድርጌ አመሰግናለሁ ።"
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤25👍23👎5
አክሱም አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
*******************
የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ጋር በመሆን ነው የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ያደረጉት፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ዳግም አገልግሎቱን በይፋ መጀመሩ የሰላሙ ውጤት መሆኑን ገልጸው፤ አክሱም ሁሉን አቀፍ የቱሪስት መስህብ ያለው ከተማ ነው ብለዋል።
በቀጣይም ለአክሱም ህዝብና ቅርስ የሚመጥን የልማት ስራዎች እንደሚከናወን ተናግረዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid035CgxcdD4k1oM1UnsPWeVpZTuMW6xocAGLPPp3LH6PA5Nw4HXpxofRvGkvXaMRnhcl
*******************
የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ጋር በመሆን ነው የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ያደረጉት፡፡
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ዳግም አገልግሎቱን በይፋ መጀመሩ የሰላሙ ውጤት መሆኑን ገልጸው፤ አክሱም ሁሉን አቀፍ የቱሪስት መስህብ ያለው ከተማ ነው ብለዋል።
በቀጣይም ለአክሱም ህዝብና ቅርስ የሚመጥን የልማት ስራዎች እንደሚከናወን ተናግረዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid035CgxcdD4k1oM1UnsPWeVpZTuMW6xocAGLPPp3LH6PA5Nw4HXpxofRvGkvXaMRnhcl
Facebook
Ethiopian Broadcasting Corporation
የአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
*******************
የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ...
*******************
የአክሱም አፄ ዮሐንስ አራተኛ አውሮፕላን ማረፊያ ዛሬ በይፋ ተመርቆ ዳግም አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ...
👍27❤4
በኦሮሚያ ክልል በተያዘው ዓመት ምርት የሚሰጥ የቡና ሽፋንን ወደ 1.45 ሚሊዮን ሄክታር ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ነው
*****************
በግብርናው ዘርፍ ለማሳካት ከተያዙ አራት ግቦች መካከል አንዱ የሆነውን ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ብዛት፣ ዓይነት እና ጥራት የማሳደግ አፈፃፀም በስኬት ጎዳና ላይ ይገኛል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
በተለይም የቡና ልማት ኢኒሼቲቭ በ2011 ዓ.ም፣ በ“ነቀምቴ አዋጅ” ይፋ ከተደረገ ጀምሮ ለአገሪቱ ብሎም ለክልሉ እያስገኘ ካለው ውጤት በተጓዳኝ አርሶ አደሩንም ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም ነው የገለጹት።
እንደ አቶ ሽመልስ ገለጻ፥ ኢኒሼቲቩ በ2011 ዓ.ም 997 ሚሊዮን የቡና ችግኝ በመትከል የተጀመረ ሲሆን፤ በ2015 ዓ.ም 1.33 ቢሊዮን የቡና ችግኝ ለመትከል ተችሏል።
በአጠቃላይ፣ በአምስቱ ዓመታት ሂደት ከ866 ሚሊዮን ሄክታር በሚልቅ አዲስ መሬት ላይ ከ5.4 ቢሊዮን በላይ ቡና የተተከለ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ወደ ግማሽ የሚጠጋው በአራቱ የወለጋ ዞኖች የተከናወነ ነው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02q1uB8VPvZnmtT73u3fgWLSDnyM96Y1RNQZxVaFWLa8tcJ98McG8s5XtSPCaMdGwbl
*****************
በግብርናው ዘርፍ ለማሳካት ከተያዙ አራት ግቦች መካከል አንዱ የሆነውን ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ብዛት፣ ዓይነት እና ጥራት የማሳደግ አፈፃፀም በስኬት ጎዳና ላይ ይገኛል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
በተለይም የቡና ልማት ኢኒሼቲቭ በ2011 ዓ.ም፣ በ“ነቀምቴ አዋጅ” ይፋ ከተደረገ ጀምሮ ለአገሪቱ ብሎም ለክልሉ እያስገኘ ካለው ውጤት በተጓዳኝ አርሶ አደሩንም ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑንም ነው የገለጹት።
እንደ አቶ ሽመልስ ገለጻ፥ ኢኒሼቲቩ በ2011 ዓ.ም 997 ሚሊዮን የቡና ችግኝ በመትከል የተጀመረ ሲሆን፤ በ2015 ዓ.ም 1.33 ቢሊዮን የቡና ችግኝ ለመትከል ተችሏል።
በአጠቃላይ፣ በአምስቱ ዓመታት ሂደት ከ866 ሚሊዮን ሄክታር በሚልቅ አዲስ መሬት ላይ ከ5.4 ቢሊዮን በላይ ቡና የተተከለ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ወደ ግማሽ የሚጠጋው በአራቱ የወለጋ ዞኖች የተከናወነ ነው።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02q1uB8VPvZnmtT73u3fgWLSDnyM96Y1RNQZxVaFWLa8tcJ98McG8s5XtSPCaMdGwbl
Facebook
Ethiopian Broadcasting Corporation
በኦሮሚያ ክልል በተያዘው ዓመት ምርት የሚሰጥ የቡና ሽፋንን ወደ 1.45 ሚሊዮን ሄክታር ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ነው
*****************
በግብርናው ዘርፍ ለማሳካት ከተያዙ አራት ግቦች መካከል አንዱ የሆነውን ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ብዛት፣ ዓይነት እና ጥራት የማሳደግ አፈፃፀም በስኬት ጎዳና ላይ...
*****************
በግብርናው ዘርፍ ለማሳካት ከተያዙ አራት ግቦች መካከል አንዱ የሆነውን ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ብዛት፣ ዓይነት እና ጥራት የማሳደግ አፈፃፀም በስኬት ጎዳና ላይ...
👍52❤9👏7