የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 3ኛ እና 4ኛ ጨዋታዎቹን በኮትዲቯር ያደርጋል
*************
ዋልያዎቹ ከጊኒ ጋር የሚያደርጓቸው እነዚህ የደርሶ መልስ መረሐ ግብሮች በኮትዲቯር እንደሚደረጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል።
የሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ ጨዋታ ጊኒ የሜዳዋ ጨዋታዋን ለማድረግ ባስመዘገበችውና በያሞሱክሩ በሚገኘው ስታድ ኮናን ባኒ ስታዲየም ጥቅምት 1/2017 ከምሽቱ 1፡00 ላይ ይከናወናል።
ሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ ባስመዘገበችውና አቢጃን በሚገኘው ስታድ ደ ኢቢምፔ ስታዲየም ጥቅምት 4/2017 ምሸት 4፡00 ላይ ይደረጋል።
ሞሮኮ በ2025 ለምታሰናዳው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ እስካሁን ሁለት ጨዋታዎችን ያደረጉት ዋልያዎቹ አንድ ነጥብ በመያዝ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ጊኒ በአንጻሩ እስካሁን ምንም ነጥብ አላስመዘገበችም።
በዮሴፍ ሹምዬ
*************
ዋልያዎቹ ከጊኒ ጋር የሚያደርጓቸው እነዚህ የደርሶ መልስ መረሐ ግብሮች በኮትዲቯር እንደሚደረጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል።
የሁለቱ ሀገራት የመጀመሪያ ጨዋታ ጊኒ የሜዳዋ ጨዋታዋን ለማድረግ ባስመዘገበችውና በያሞሱክሩ በሚገኘው ስታድ ኮናን ባኒ ስታዲየም ጥቅምት 1/2017 ከምሽቱ 1፡00 ላይ ይከናወናል።
ሁለተኛው ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ ባስመዘገበችውና አቢጃን በሚገኘው ስታድ ደ ኢቢምፔ ስታዲየም ጥቅምት 4/2017 ምሸት 4፡00 ላይ ይደረጋል።
ሞሮኮ በ2025 ለምታሰናዳው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ እስካሁን ሁለት ጨዋታዎችን ያደረጉት ዋልያዎቹ አንድ ነጥብ በመያዝ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
ጊኒ በአንጻሩ እስካሁን ምንም ነጥብ አላስመዘገበችም።
በዮሴፍ ሹምዬ
👍31❤3👎3
ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የተ.መ.ድ. ዋና ጸሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴቴን አሰናበቱ
**************
ፕሬዚዳንቷ በዚሁ ወቅት ልዩ መልዕክተኛዋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
**************
ፕሬዚዳንቷ በዚሁ ወቅት ልዩ መልዕክተኛዋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
👍44❤12
ኢትዮጵያ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ላስመዘገበችዉ አመርቂ ዉጤት እዉቅና አገኘች
********************
በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል (ኤንሲዲ) ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ሽልማት አበርክቷል።
እውቅናው የተሰጠው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ስራዎችን በማከናወን እና ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት መስጠት በመቻሏ በተለይም የማህፀን ጫፍ ካንሰርን በመከላከል ላስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሽልማቱን መቀበላቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
********************
በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል (ኤንሲዲ) ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ሽልማት አበርክቷል።
እውቅናው የተሰጠው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ስራዎችን በማከናወን እና ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት መስጠት በመቻሏ በተለይም የማህፀን ጫፍ ካንሰርን በመከላከል ላስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሽልማቱን መቀበላቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍29❤2
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በፍሪላንስ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ከዚህ በታች ለተገለጸው ክፍት የስራ መደብ ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይሄ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አምስት (5) ተከታታይ የስራ ቀናት ሸጎሌ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዲቪዥን ቢሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በፍሪላንስ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ከዚህ በታች ለተገለጸው ክፍት የስራ መደብ ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይሄ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አምስት (5) ተከታታይ የስራ ቀናት ሸጎሌ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዲቪዥን ቢሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
👍9❤6👎1
የዘንድሮው ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር ተገለፀ
****************
የዘንድሮው ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር የአባገዳዎች ሕብረት አስታውቋል፡፡
የኢሬቻ በዓል አከባበርን አስመልክቶ የአባገዳዎች ሕብረት መግለጫ የሰጠ ሲሆን፤ በዚህም በዓሉ በመስከረም 25 ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ፤ በመስከረም 26 ደግሞ ኢሬቻ ሆረ አርሰዴ እንደሚከበር ተገልጿል።
መግለጫውን የሰጡት አባ ገዳዎችና ሃዳ ሲንቄዎች ኢሬቻ የእርቅና የሰላም በዓል በመሆኑ ዘንድሮም አንድነትንና ሕብረትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ገልጸዋል።
የኦሮሚያ አባገዳዎች ህብረት ሰብሳቢ አባገዳ ወርነህ ተሬሳ፤ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርዓት እሴትን በጠበቀ መልኩ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid021ZRuaKAiqMGKJGKjjN37SX6sy5oJRPoSdXmWewqYwJyHZ6pz6enKvoCeAPFK5NcNl
****************
የዘንድሮው ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር የአባገዳዎች ሕብረት አስታውቋል፡፡
የኢሬቻ በዓል አከባበርን አስመልክቶ የአባገዳዎች ሕብረት መግለጫ የሰጠ ሲሆን፤ በዚህም በዓሉ በመስከረም 25 ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ፤ በመስከረም 26 ደግሞ ኢሬቻ ሆረ አርሰዴ እንደሚከበር ተገልጿል።
መግለጫውን የሰጡት አባ ገዳዎችና ሃዳ ሲንቄዎች ኢሬቻ የእርቅና የሰላም በዓል በመሆኑ ዘንድሮም አንድነትንና ሕብረትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ገልጸዋል።
የኦሮሚያ አባገዳዎች ህብረት ሰብሳቢ አባገዳ ወርነህ ተሬሳ፤ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርዓት እሴትን በጠበቀ መልኩ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid021ZRuaKAiqMGKJGKjjN37SX6sy5oJRPoSdXmWewqYwJyHZ6pz6enKvoCeAPFK5NcNl
👏14❤9👍8👎8
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2017 ዓመት የመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓሉ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
የመስቀል በዓል የሕልም ጉልበት የታየበት በዓል ነው፡፡
ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ለማውጣት ያለመችው ምንም አመቺ ነገር ባልነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ዙሪያዋ ጨለማ ነበር፡፡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ማንም በማያስበው ጊዜ፤ አይቻልም አይሞከርም በሚባልበት ወቅት፤ አንድ ቀን፤ ፈጣሪዋ ሲፈቅድ፤ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት ሕልም ነበራት፡፡
ሕልሟ እንዲሳካ ሠራች፤ ታገለች፡፡ ጨለማውን እየገፈፈች፤ አስቸጋሪውን ጎዳና እየጠረገች፤ ከውስብስብ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ወደ ፊት ተጓዘች፡፡ በመጨረሻም ኢየሩሳሌም ተሻግራ፣ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት በቃች፡፡ ሕልሟ እውን ሆነ፡፡ ታሪክን ቀየረች፡፡ ልዕልናን ዐወጀች፡፡ ደመራ ለሚታገል፤ ተስፋ ለማይቆርጥና እስከ መጨረሻው ለሚጸና ሰው ሕልሙ አንድ ቀን እውን እንደሚሆን የሚያሳይ ትእምርት ነው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0fhvFHPF476JMQQZc67nK5sHuGbERdXmS1so9mfrh8xLXkdBwhQKYcLnyB5y4Xwxnl
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2017 ዓመት የመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓሉ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
የመስቀል በዓል የሕልም ጉልበት የታየበት በዓል ነው፡፡
ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ለማውጣት ያለመችው ምንም አመቺ ነገር ባልነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ዙሪያዋ ጨለማ ነበር፡፡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ማንም በማያስበው ጊዜ፤ አይቻልም አይሞከርም በሚባልበት ወቅት፤ አንድ ቀን፤ ፈጣሪዋ ሲፈቅድ፤ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት ሕልም ነበራት፡፡
ሕልሟ እንዲሳካ ሠራች፤ ታገለች፡፡ ጨለማውን እየገፈፈች፤ አስቸጋሪውን ጎዳና እየጠረገች፤ ከውስብስብ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ወደ ፊት ተጓዘች፡፡ በመጨረሻም ኢየሩሳሌም ተሻግራ፣ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት በቃች፡፡ ሕልሟ እውን ሆነ፡፡ ታሪክን ቀየረች፡፡ ልዕልናን ዐወጀች፡፡ ደመራ ለሚታገል፤ ተስፋ ለማይቆርጥና እስከ መጨረሻው ለሚጸና ሰው ሕልሙ አንድ ቀን እውን እንደሚሆን የሚያሳይ ትእምርት ነው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0fhvFHPF476JMQQZc67nK5sHuGbERdXmS1so9mfrh8xLXkdBwhQKYcLnyB5y4Xwxnl
👍29❤16👏6