ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የተ.መ.ድ. ዋና ጸሐፊ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሀና ቴቴን አሰናበቱ
**************
ፕሬዚዳንቷ በዚሁ ወቅት ልዩ መልዕክተኛዋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
**************
ፕሬዚዳንቷ በዚሁ ወቅት ልዩ መልዕክተኛዋ ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ላበረከቱት ከፍተኛ ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።
👍44❤12
ኢትዮጵያ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በመከላከል ረገድ ላስመዘገበችዉ አመርቂ ዉጤት እዉቅና አገኘች
********************
በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል (ኤንሲዲ) ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ሽልማት አበርክቷል።
እውቅናው የተሰጠው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ስራዎችን በማከናወን እና ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት መስጠት በመቻሏ በተለይም የማህፀን ጫፍ ካንሰርን በመከላከል ላስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሽልማቱን መቀበላቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
********************
በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተመድ 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል (ኤንሲዲ) ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ሽልማት አበርክቷል።
እውቅናው የተሰጠው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠር ስራዎችን በማከናወን እና ማህበረሰቡን ያማከለ አገልግሎት መስጠት በመቻሏ በተለይም የማህፀን ጫፍ ካንሰርን በመከላከል ላስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሽልማቱን መቀበላቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍29❤2
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በፍሪላንስ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ከዚህ በታች ለተገለጸው ክፍት የስራ መደብ ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይሄ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አምስት (5) ተከታታይ የስራ ቀናት ሸጎሌ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዲቪዥን ቢሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የሥራ መደብ ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በፍሪላንስ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ከዚህ በታች ለተገለጸው ክፍት የስራ መደብ ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች ይሄ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አምስት (5) ተከታታይ የስራ ቀናት ሸጎሌ በሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዲቪዥን ቢሮ ዘወትር በስራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
👍9❤6👎1
የዘንድሮው ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር ተገለፀ
****************
የዘንድሮው ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር የአባገዳዎች ሕብረት አስታውቋል፡፡
የኢሬቻ በዓል አከባበርን አስመልክቶ የአባገዳዎች ሕብረት መግለጫ የሰጠ ሲሆን፤ በዚህም በዓሉ በመስከረም 25 ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ፤ በመስከረም 26 ደግሞ ኢሬቻ ሆረ አርሰዴ እንደሚከበር ተገልጿል።
መግለጫውን የሰጡት አባ ገዳዎችና ሃዳ ሲንቄዎች ኢሬቻ የእርቅና የሰላም በዓል በመሆኑ ዘንድሮም አንድነትንና ሕብረትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ገልጸዋል።
የኦሮሚያ አባገዳዎች ህብረት ሰብሳቢ አባገዳ ወርነህ ተሬሳ፤ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርዓት እሴትን በጠበቀ መልኩ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid021ZRuaKAiqMGKJGKjjN37SX6sy5oJRPoSdXmWewqYwJyHZ6pz6enKvoCeAPFK5NcNl
****************
የዘንድሮው ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር የአባገዳዎች ሕብረት አስታውቋል፡፡
የኢሬቻ በዓል አከባበርን አስመልክቶ የአባገዳዎች ሕብረት መግለጫ የሰጠ ሲሆን፤ በዚህም በዓሉ በመስከረም 25 ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ፤ በመስከረም 26 ደግሞ ኢሬቻ ሆረ አርሰዴ እንደሚከበር ተገልጿል።
መግለጫውን የሰጡት አባ ገዳዎችና ሃዳ ሲንቄዎች ኢሬቻ የእርቅና የሰላም በዓል በመሆኑ ዘንድሮም አንድነትንና ሕብረትን በሚያጠናክር መልኩ እንደሚከበር ገልጸዋል።
የኦሮሚያ አባገዳዎች ህብረት ሰብሳቢ አባገዳ ወርነህ ተሬሳ፤ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርዓት እሴትን በጠበቀ መልኩ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid021ZRuaKAiqMGKJGKjjN37SX6sy5oJRPoSdXmWewqYwJyHZ6pz6enKvoCeAPFK5NcNl
👏14❤9👍8👎8
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2017 ዓመት የመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓሉ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
የመስቀል በዓል የሕልም ጉልበት የታየበት በዓል ነው፡፡
ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ለማውጣት ያለመችው ምንም አመቺ ነገር ባልነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ዙሪያዋ ጨለማ ነበር፡፡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ማንም በማያስበው ጊዜ፤ አይቻልም አይሞከርም በሚባልበት ወቅት፤ አንድ ቀን፤ ፈጣሪዋ ሲፈቅድ፤ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት ሕልም ነበራት፡፡
ሕልሟ እንዲሳካ ሠራች፤ ታገለች፡፡ ጨለማውን እየገፈፈች፤ አስቸጋሪውን ጎዳና እየጠረገች፤ ከውስብስብ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ወደ ፊት ተጓዘች፡፡ በመጨረሻም ኢየሩሳሌም ተሻግራ፣ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት በቃች፡፡ ሕልሟ እውን ሆነ፡፡ ታሪክን ቀየረች፡፡ ልዕልናን ዐወጀች፡፡ ደመራ ለሚታገል፤ ተስፋ ለማይቆርጥና እስከ መጨረሻው ለሚጸና ሰው ሕልሙ አንድ ቀን እውን እንደሚሆን የሚያሳይ ትእምርት ነው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0fhvFHPF476JMQQZc67nK5sHuGbERdXmS1so9mfrh8xLXkdBwhQKYcLnyB5y4Xwxnl
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2017 ዓመት የመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓሉ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
የመስቀል በዓል የሕልም ጉልበት የታየበት በዓል ነው፡፡
ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ለማውጣት ያለመችው ምንም አመቺ ነገር ባልነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ዙሪያዋ ጨለማ ነበር፡፡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ማንም በማያስበው ጊዜ፤ አይቻልም አይሞከርም በሚባልበት ወቅት፤ አንድ ቀን፤ ፈጣሪዋ ሲፈቅድ፤ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት ሕልም ነበራት፡፡
ሕልሟ እንዲሳካ ሠራች፤ ታገለች፡፡ ጨለማውን እየገፈፈች፤ አስቸጋሪውን ጎዳና እየጠረገች፤ ከውስብስብ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ወደ ፊት ተጓዘች፡፡ በመጨረሻም ኢየሩሳሌም ተሻግራ፣ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት በቃች፡፡ ሕልሟ እውን ሆነ፡፡ ታሪክን ቀየረች፡፡ ልዕልናን ዐወጀች፡፡ ደመራ ለሚታገል፤ ተስፋ ለማይቆርጥና እስከ መጨረሻው ለሚጸና ሰው ሕልሙ አንድ ቀን እውን እንደሚሆን የሚያሳይ ትእምርት ነው፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0fhvFHPF476JMQQZc67nK5sHuGbERdXmS1so9mfrh8xLXkdBwhQKYcLnyB5y4Xwxnl
👍29❤16👏6
"እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ" - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
****************
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓሉ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
የመስቀል በዓል ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ በኢትዮጵያውያን የሚከበር በዓል ነው። አከባበሩ ኅብራዊ ነው። የየአካባቢው ቀለም ይጨመርበታል። የሚከበረው ግን በተመሳሳይ ወቅት ነው። ከግላዊ ይልቅ ቤተሰባዊና ማኅበራዊ በዓል ነው።
መስቀል ነባር ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ያሳያል። በብዙ አካባቢዎች የዘመን መለወጫ በዓላት በመስከረም ወር፣ ከመስቀል በዓል ጋር ተያይዘው መከበራቸው ጥንታዊ ማኅበራዊ ትሥሥራችንን ሳያመለክት አይቀርም።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02fDXJHU7VJFrK1EP91aj97ZFgMrev2yGDVYD7K3H17hNyq8u7A5LmpcWPKaAGF2xbl
****************
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለበዓሉ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡-
የመስቀል በዓል ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ በኢትዮጵያውያን የሚከበር በዓል ነው። አከባበሩ ኅብራዊ ነው። የየአካባቢው ቀለም ይጨመርበታል። የሚከበረው ግን በተመሳሳይ ወቅት ነው። ከግላዊ ይልቅ ቤተሰባዊና ማኅበራዊ በዓል ነው።
መስቀል ነባር ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ያሳያል። በብዙ አካባቢዎች የዘመን መለወጫ በዓላት በመስከረም ወር፣ ከመስቀል በዓል ጋር ተያይዘው መከበራቸው ጥንታዊ ማኅበራዊ ትሥሥራችንን ሳያመለክት አይቀርም።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02fDXJHU7VJFrK1EP91aj97ZFgMrev2yGDVYD7K3H17hNyq8u7A5LmpcWPKaAGF2xbl
👍21👏5
የሀረሪ ክልል መንግስት ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
******************
የሀረሪ ክልላዊ መንግስት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለደመራና ለመስቀል በዓል የአንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡
የክልሉ መንግስት በመልእክቱ፤ ህዝበ ክርስትያኑ የደመራ በዓል አከባበር እሴቱን ጠብቆ እንዲከበር በማድረግ የተቸገሩ ወገኖችን በማብላትና የተጠሙትን በማጠጣት እንዲሁም የተለመደ የመተዛዘንና የመረዳዳት ባህሉን በመተግበር በዓሉን እንዲያከብር ጥሪ አቅርቧል።
ህዝበ ክርስትያኑን ጨምሮ መላው የክልሉ ነዋሪ ሰላምን፣ አብሮነትን፣ መተባበርንና ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጎልበት እንዲሁም በክልሉ የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ የልማት ተግባራት እንዲጠናከርም ጠይቋል።
የክልሉ መንግስት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለደመራና ለመስቀል በዓል የአንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፎ፤ በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን ተመኘቷል።
******************
የሀረሪ ክልላዊ መንግስት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለደመራና ለመስቀል በዓል የአንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡
የክልሉ መንግስት በመልእክቱ፤ ህዝበ ክርስትያኑ የደመራ በዓል አከባበር እሴቱን ጠብቆ እንዲከበር በማድረግ የተቸገሩ ወገኖችን በማብላትና የተጠሙትን በማጠጣት እንዲሁም የተለመደ የመተዛዘንና የመረዳዳት ባህሉን በመተግበር በዓሉን እንዲያከብር ጥሪ አቅርቧል።
ህዝበ ክርስትያኑን ጨምሮ መላው የክልሉ ነዋሪ ሰላምን፣ አብሮነትን፣ መተባበርንና ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጎልበት እንዲሁም በክልሉ የተጀመሩ ሁሉን አቀፍ የልማት ተግባራት እንዲጠናከርም ጠይቋል።
የክልሉ መንግስት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለደመራና ለመስቀል በዓል የአንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፎ፤ በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን ተመኘቷል።
❤7👍6
ርዕሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳ በኦሮሚያ ክልል የተጀመረውን አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ
********************
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ በክልሉ የተጀመረውን አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ጠዴ ድልዲማ በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡
በምስራቅ ሸዋ ዞን 302 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት የተዋቀሩ ሲሆን 281 የሚሆኑት ወደ ስራ መግባታቸዉን የዞኑ አስተዳደር አቶ አባቦ ማሞ ገልፀዋል::
በሉሜ ወረደ የጠዴ ድልዲማ ቀበሌ አስተዳደር ወ/ሮ ትግስት ኢብራህም የህዝብ አገልግሎት በቀበሌ ደረጃ እንዲሰጥ መደረጉ የበለጠ አመራሩ እራሱን ሰጥቶ ህዝቡን በንቃት እንዲገለግል አድርጎታል ብለዋል::
ነዋሪዎችም አገልግሎት በቅርበት ማግኘታቸው እንዳስደታቸው እና ግዜያቸዉን እንደቆጠበላቸዉ ገልፀዋል::
በዓሊ ደደፎ
********************
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ ከፍያለው ተፈራ በክልሉ የተጀመረውን አዲስ የቀበሌ አደረጃጀት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ጠዴ ድልዲማ በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡
በምስራቅ ሸዋ ዞን 302 ቀበሌዎች በአዲሱ አደረጃጀት የተዋቀሩ ሲሆን 281 የሚሆኑት ወደ ስራ መግባታቸዉን የዞኑ አስተዳደር አቶ አባቦ ማሞ ገልፀዋል::
በሉሜ ወረደ የጠዴ ድልዲማ ቀበሌ አስተዳደር ወ/ሮ ትግስት ኢብራህም የህዝብ አገልግሎት በቀበሌ ደረጃ እንዲሰጥ መደረጉ የበለጠ አመራሩ እራሱን ሰጥቶ ህዝቡን በንቃት እንዲገለግል አድርጎታል ብለዋል::
ነዋሪዎችም አገልግሎት በቅርበት ማግኘታቸው እንዳስደታቸው እና ግዜያቸዉን እንደቆጠበላቸዉ ገልፀዋል::
በዓሊ ደደፎ
👍18👎5