የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው
**********************
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ይገኛል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተመራቂ ዕጩ መኮንኖች በማሠልጠኛ ማዕከሉ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩና የሚጠበቅባቸውን ሥልጠና ወስደው ያለፉ መሆናቸው ተገልጿል።
ይመር አደም
**********************
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ይገኛል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተመራቂ ዕጩ መኮንኖች በማሠልጠኛ ማዕከሉ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩና የሚጠበቅባቸውን ሥልጠና ወስደው ያለፉ መሆናቸው ተገልጿል።
ይመር አደም
👍19❤12👏3👎2
ኢትዮጵያ ዕድገት ተኮር የኢኮኖሚ ሪፎርም እያካሄደች ትገኛለች - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)
**************************
ኢትዮጵያ ዕድገት ተኮር የኢኮኖሚ ሪፎርም እያካሄደች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ ሪፎርሙ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን እና የግል ዘርፉን ተሳትፎ እንደሚያበረታታም ጠቁመዋል፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የንግድ ሚኒስትሮች 15ኛ ጉባኤ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ጉባኤው የጋራ ግቦችን ውጤታማ የሚያደርጉ አቅጣጫዎችን ለማመላከት፣ ችግሮችን ለመፍታት እና ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ለመምከር እንደሚያግዝም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና በአባል ሃገራት መካክል ንግድን በማሳለጥ ኢንዱስትሪያላይዜሽንን በመገንባት ሂደት ውስጥ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር መናገራቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
**************************
ኢትዮጵያ ዕድገት ተኮር የኢኮኖሚ ሪፎርም እያካሄደች እንደምትገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ ሪፎርሙ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን እና የግል ዘርፉን ተሳትፎ እንደሚያበረታታም ጠቁመዋል፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና የንግድ ሚኒስትሮች 15ኛ ጉባኤ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ጉባኤው የጋራ ግቦችን ውጤታማ የሚያደርጉ አቅጣጫዎችን ለማመላከት፣ ችግሮችን ለመፍታት እና ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ለመምከር እንደሚያግዝም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና በአባል ሃገራት መካክል ንግድን በማሳለጥ ኢንዱስትሪያላይዜሽንን በመገንባት ሂደት ውስጥ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር መናገራቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
👍18❤6
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ አስረከቡ
*********************
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል፡፡
ኮሚሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሲያካሂድ የቆየውን የአጀንዳ ልየታ መርሐ-ግብር አጠናቋል፡፡
የክልሉ ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ እንዲሁም ለኮሚሽነር ዘገየ አስፋው እና ሙሉጌታ አጎ አስረክበዋል።
ላለፉት 7 ቀናት በክልሉ በተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የማኀበረሰብ ተወካዮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግስት አካላት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና የሲቪል ማኀበራት ሲሳተፉ ቆይተዋል።
ሰለሞን ከበደ
*********************
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክበዋል፡፡
ኮሚሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሲያካሂድ የቆየውን የአጀንዳ ልየታ መርሐ-ግብር አጠናቋል፡፡
የክልሉ ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ እንዲሁም ለኮሚሽነር ዘገየ አስፋው እና ሙሉጌታ አጎ አስረክበዋል።
ላለፉት 7 ቀናት በክልሉ በተካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የማኀበረሰብ ተወካዮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግስት አካላት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና የሲቪል ማኀበራት ሲሳተፉ ቆይተዋል።
ሰለሞን ከበደ
👍13👏2❤1
መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በላቀ ደረጃ የማስጠበቅ አስተማማኝ ብቃት ላይ ይገኛል - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
*************************
መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና ብሔራዊ ጥቅም በላቀ ደረጃ የማስጠበቅ አስተማማኝ ብቃት ላይ እንደሚገኝ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናግረዋል፡፡
ሠራዊቱ የኢትዮጵያን የዕድገት ጉዞ በበጎ የማይመለከቱ ታሪካዊ ጠላቶችን እና የውስጥ ተላላኪ ኃይሎችን አፍራሽ ተግባር በታላቅ ብቃት እያከሸፈ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡
መከላከያ ሠራዊት የጠላቶችን እና የቅጥረኞችን ሴራ በማሸነፍ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገት ጉዞ ከግብ እንድታደርስ በሚያስችለው ብቃት ላይ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
*************************
መከላከያ ሠራዊት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና ብሔራዊ ጥቅም በላቀ ደረጃ የማስጠበቅ አስተማማኝ ብቃት ላይ እንደሚገኝ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናግረዋል፡፡
ሠራዊቱ የኢትዮጵያን የዕድገት ጉዞ በበጎ የማይመለከቱ ታሪካዊ ጠላቶችን እና የውስጥ ተላላኪ ኃይሎችን አፍራሽ ተግባር በታላቅ ብቃት እያከሸፈ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡
መከላከያ ሠራዊት የጠላቶችን እና የቅጥረኞችን ሴራ በማሸነፍ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገት ጉዞ ከግብ እንድታደርስ በሚያስችለው ብቃት ላይ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ እና የሁርሶ ዕጩ መኮንን ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የወልወል ድህረ-ምረቃ እና የ25ኛ ሰላም ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ጄኔራል መኮንኖች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
👍22❤10👏2
ኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ ለውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ ሁኔታ ፈጥራለች - ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ
**************************
ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ ለውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ ሁኔታ መፍጠሯን ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ተናግረዋል፡፡
ይህም የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ለማቀላጠፍ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ነጻ የንግድ ቀጣናው የአህጉሪቱን ዘላቂ ዕድገት የሚያረጋግጥ እና ወደ ብልፅግና የሚያሸጋግር በመሆኑ ለተግባራዊነቱ መረባረብ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና “የጋራ ራዕያችንን የምናሳካበት የበለጸገች አፍሪካን እውን የምናደርግበት ነው” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
15ኛው የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የንግድ ሚኒስትሮች ጉባዔ በአፍሪካ ህብረት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
**************************
ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ ለውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ ሁኔታ መፍጠሯን ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ተናግረዋል፡፡
ይህም የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራን ለማቀላጠፍ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ነጻ የንግድ ቀጣናው የአህጉሪቱን ዘላቂ ዕድገት የሚያረጋግጥ እና ወደ ብልፅግና የሚያሸጋግር በመሆኑ ለተግባራዊነቱ መረባረብ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና “የጋራ ራዕያችንን የምናሳካበት የበለጸገች አፍሪካን እውን የምናደርግበት ነው” ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
15ኛው የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የንግድ ሚኒስትሮች ጉባዔ በአፍሪካ ህብረት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
👍29❤6👎4👏1
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የከተማዋ ፖሊስ ሠራዊት አባላት ዕውቅና ሰጡ
*************************
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የመዲናዋ የፖሊስ ሠራዊት አባላት ዕውቅና ሰጥተዋል፡
ከንቲባዋ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው “ለከተማችን ሰላም ፖሊሳዊ ሥነ-ምግባር በመላበስ፣ የሌሊት ቁር እና የቀትር ጸሐይን በመቋቋም በሰብዓዊነት እና በጀግንነት እስከ ህይወት መስዋዕትነት በማገልገል በተሰራዉ ሥራ እና በተገኘዉ ውጤት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የከተማችን ፖሊስ ሠራዊት አባላት ዕውቅና ሰጥተናል” ብለዋል፡፡
ለከተማዋ ሰላም እና ደህንነት መረጋገጥ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅርበት እየሰሩ ላሉ የጸጥታ አካላትም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
*************************
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የመዲናዋ የፖሊስ ሠራዊት አባላት ዕውቅና ሰጥተዋል፡
ከንቲባዋ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው “ለከተማችን ሰላም ፖሊሳዊ ሥነ-ምግባር በመላበስ፣ የሌሊት ቁር እና የቀትር ጸሐይን በመቋቋም በሰብዓዊነት እና በጀግንነት እስከ ህይወት መስዋዕትነት በማገልገል በተሰራዉ ሥራ እና በተገኘዉ ውጤት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የከተማችን ፖሊስ ሠራዊት አባላት ዕውቅና ሰጥተናል” ብለዋል፡፡
ለከተማዋ ሰላም እና ደህንነት መረጋገጥ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅርበት እየሰሩ ላሉ የጸጥታ አካላትም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
👏20👍12❤10👎5