ሻምፒዮኑ ማንቸስተር ሲቲ በብራይተን አልቢዮን 2ለ1 ተሸነፈ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከሜዳው ውጭ ብራይተን አልቢዮንን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ 2ለ1 ተሸንፏል።
ማንቸስተር ሲቲ ኮቫቲች በግሩም ሁኔታ ያቀበለውን ኳስ በመቀበል ሃላንድ በ23ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ እስከ 78ኛው ደቂቃ ድረስ 1ለ0 መምራት ችሎ ነበር።
ሆኖም ለብራይተን አልቢዮን በ2ኛው መደበኛ የጨዋታ ክፍ ጊዜ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ፔድሮ በ78ኛው ደቂቃ የአቻነቷን ግብ አስቆጠረ።
ከ5 ደቂቃ በኋላ በ83ኛው ደቂቃ ደግሞ ኦሪሌ 2ኛዋን ግብ በማስቆጠር ብራይተኖች ሲቲን በሜዳቸው 2ለ1 ማሸነፍ ችለዋል።
ብራይተን በ11 ጨዋታ አሁን በሊጉ ያለውን ደረጃ ከፍ ማድረግ ችሏል።
ሲቲ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ማሸነፍ ባለመቻሉ የሊጉ መሪ መሆን የሚችልበትን ዕድል አምክኗል።
ሊጉን በ25 ነጥብ እየመራ ያለው ሊቨር ፑል ዛሬ ማታ 5 ሰዓት በሜዳው አስቶን ቪላን ይገጥማል።
በላሉ ኢታላ
****
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 11ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከሜዳው ውጭ ብራይተን አልቢዮንን የገጠመው ማንቸስተር ሲቲ 2ለ1 ተሸንፏል።
ማንቸስተር ሲቲ ኮቫቲች በግሩም ሁኔታ ያቀበለውን ኳስ በመቀበል ሃላንድ በ23ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ግብ እስከ 78ኛው ደቂቃ ድረስ 1ለ0 መምራት ችሎ ነበር።
ሆኖም ለብራይተን አልቢዮን በ2ኛው መደበኛ የጨዋታ ክፍ ጊዜ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው ፔድሮ በ78ኛው ደቂቃ የአቻነቷን ግብ አስቆጠረ።
ከ5 ደቂቃ በኋላ በ83ኛው ደቂቃ ደግሞ ኦሪሌ 2ኛዋን ግብ በማስቆጠር ብራይተኖች ሲቲን በሜዳቸው 2ለ1 ማሸነፍ ችለዋል።
ብራይተን በ11 ጨዋታ አሁን በሊጉ ያለውን ደረጃ ከፍ ማድረግ ችሏል።
ሲቲ የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ ማሸነፍ ባለመቻሉ የሊጉ መሪ መሆን የሚችልበትን ዕድል አምክኗል።
ሊጉን በ25 ነጥብ እየመራ ያለው ሊቨር ፑል ዛሬ ማታ 5 ሰዓት በሜዳው አስቶን ቪላን ይገጥማል።
በላሉ ኢታላ
👍37👏6❤5
ዛሬ የበሰቃን ሐይቅ ድብቅ ውበት ገልጠናል፤ የተገለጠው ምሥጢርም 'ቤኑና መንደር' ይሰኛል
**
ከመተሃራ ከተማ አቅራቢያ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ በቅርብ ርቀት የሚገኘው የቤኑና መንደር' ከእሳተ ገሞራ ቅሪት መልክዓ ምድር ገጽታው ወደ ሰላምን የሚያጎናፅፍ የመዝናኛ መዳረሻ እና አረንጓዴ የእርሻ ምድርነት በአስደናቂ አኳኋን ተለውጧል ሲል የጠቅላይ ሚንስትር ጽህፈት ቤት ገልጿል።
#PMOEthiopia
**
ከመተሃራ ከተማ አቅራቢያ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ በቅርብ ርቀት የሚገኘው የቤኑና መንደር' ከእሳተ ገሞራ ቅሪት መልክዓ ምድር ገጽታው ወደ ሰላምን የሚያጎናፅፍ የመዝናኛ መዳረሻ እና አረንጓዴ የእርሻ ምድርነት በአስደናቂ አኳኋን ተለውጧል ሲል የጠቅላይ ሚንስትር ጽህፈት ቤት ገልጿል።
#PMOEthiopia
👍43👏11❤10
"ለማየት እንደሚናፈቅ ሩቅ ምድር ግን ደግሞ በይቻላል መንፈስ ዕውን መሆን የቻለ፤
ምስራቃዊቷ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ከፍታ ማሳያ፤ የተፈጥሮ ውበት ምስጢር፣ ሩቅ የሚያስቡ ብሩህ አዕምሮዎች ትሩፋት እና የሚሰሩ እጆች ድምር ውጤት፤ የመቻል ልክ፡፡
በሰቃ!"
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ምስራቃዊቷ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ከፍታ ማሳያ፤ የተፈጥሮ ውበት ምስጢር፣ ሩቅ የሚያስቡ ብሩህ አዕምሮዎች ትሩፋት እና የሚሰሩ እጆች ድምር ውጤት፤ የመቻል ልክ፡፡
በሰቃ!"
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
❤26👍15👏4
ጎግል ፕሌይ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል ጀመረ
*************
የጎግል ፕሌይ (Google Play) አልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል ጀምሯል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልእክት፤ የጎግል ፕሌይ የአልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል መጀመሩ ለኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ ተጽእኖ የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ይህ ምዕራፍ የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ተሰጥኦ ባለቤቶች መተግበሪያዎቻቸውን በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ ዲጂታል መድረኮች ላይ እንዲያትሙ አዲስ እድሎችን እንደሚከፍትም ገልፀዋል።
መንግስት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለመገንባት በርካታ ተነሳሽነቶችን በመተግበር እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህ አዲስ ጅማሮ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ነው ብለዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gsDZmRkvic1LCDhw1sF8pWdG84jyF4GK7VesH511NbRnMmkTnsUQ5YXZnrdroMrFl
*************
የጎግል ፕሌይ (Google Play) አልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል ጀምሯል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ጉዳዩን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልእክት፤ የጎግል ፕሌይ የአልሚዎች ምዝገባ ኢትዮጵያውያን አልሚዎችን መቀበል መጀመሩ ለኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ ተጽእኖ የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ይህ ምዕራፍ የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ተሰጥኦ ባለቤቶች መተግበሪያዎቻቸውን በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ ዲጂታል መድረኮች ላይ እንዲያትሙ አዲስ እድሎችን እንደሚከፍትም ገልፀዋል።
መንግስት የዲጂታል ኢኮኖሚውን ለመገንባት በርካታ ተነሳሽነቶችን በመተግበር እየሰራ መሆኑን ገልጸው ይህ አዲስ ጅማሮ የተከናወኑ ተግባራት ውጤት ነው ብለዋል።
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0gsDZmRkvic1LCDhw1sF8pWdG84jyF4GK7VesH511NbRnMmkTnsUQ5YXZnrdroMrFl
👍17❤15