ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ የሚዛን አማን የአየር ማረፊያና የደንቢ ሎጅ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ተመለከቱ
*************
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ የሚዛን አማን ሀገር አቀፍ የአየር ማረፊያና የደንቢ ሎጅ ግንባታ የስራ እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ ሌሎች የክልል፤ የቤንች ሸኮ ዞን እንዲሁም የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በግንባታ ላይ የሚገኙ ሰራተኞችን በስፍራው ተገኝተው አበረታተዋል።
አመራሮቹ የሚዛን አማን ሀገር አቀፍ የአየር ማረፊያ የስራ ሁኔታን ተዘዋዉረው መጎብኘታቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት እየተገነቡ ከሚገኙ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነው በቤንች ሸኮ ዞን እየተገነባ የሚገኘው የደንቢ ሎጅ ግንባታ የስራ እንቅስቃሴም ምልከታ ተደርጎበታል።
*************
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ የሚዛን አማን ሀገር አቀፍ የአየር ማረፊያና የደንቢ ሎጅ ግንባታ የስራ እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ ሌሎች የክልል፤ የቤንች ሸኮ ዞን እንዲሁም የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በግንባታ ላይ የሚገኙ ሰራተኞችን በስፍራው ተገኝተው አበረታተዋል።
አመራሮቹ የሚዛን አማን ሀገር አቀፍ የአየር ማረፊያ የስራ ሁኔታን ተዘዋዉረው መጎብኘታቸውን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት እየተገነቡ ከሚገኙ ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆነው በቤንች ሸኮ ዞን እየተገነባ የሚገኘው የደንቢ ሎጅ ግንባታ የስራ እንቅስቃሴም ምልከታ ተደርጎበታል።
👍24❤4
የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራን በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን ኮሚቴው ገለፀ
************
የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ኮሚቴ የከተማዋን ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን ገለፀ፡፡
በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ኮሚቴ በጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት የስራ ሂደትን ገምግሟል።
በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን ሰብሳቢነት በተካሄደው የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ኮሚቴ የግምገማ መድረክ በከተማው እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የስራ ሂደት አፈፃፀም ግምገማ መደረጉን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ባለው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ በአራት ኪሎ ሜትር ላይ ስራው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን እና በአጠቃላይ ፕሮጀክቱን በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱ ተገልጿል።
************
የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ኮሚቴ የከተማዋን ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን ገለፀ፡፡
በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ኮሚቴ በጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት የስራ ሂደትን ገምግሟል።
በሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን ሰብሳቢነት በተካሄደው የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ኮሚቴ የግምገማ መድረክ በከተማው እየተካሄደ ያለው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የስራ ሂደት አፈፃፀም ግምገማ መደረጉን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ባለው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ በአራት ኪሎ ሜትር ላይ ስራው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን እና በአጠቃላይ ፕሮጀክቱን በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ መታቀዱ ተገልጿል።
👍32
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከእስያ በማገናኘት የጎላ አበርክቶ እንዳለው ተገለፀ
***************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከእስያ በማገናኘት የጎላ አበርክቶ እንዳለው የሲንጋፖር የጉዞና ጭነት አገልግሎት ወኪሎች ገለፁ፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሲንጋፖር ለሀገሪቱ ለተጓዦች፣ የጉዞና የጭነት አገልግሎት ወኪሎች የማበረታቻ ሽልማት መስጠቱ ይታወቃል፡፡
ኢነርጂያ፣ ሲንጋፖር ፖስት ኃ/የተ/የግ/ ማህበር፣ ኤርሰርቭ ግሩፕ፣ ሲቲስቴት ትራቭል፣ እና ኤር ፍራይት ሲንጋፖር እውቅና የተሰጣቸው ተቋማት ናቸው።
የሲቲስቴት ተራቭል ዋና ዳይሬክተር አልበርቶ ሆ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሲንጋፖር ያዘጋጀው ሁነት አየር መንገዱ ምን ያህል ታላቅና እንዴት ውጤታማ እንደሆነ ለመረዳት አስችሎኛል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከሲንጋፖር ለማስተሳሰር የሚያደርገው አስደናቂ እንቅስቃሴ አድናቆት የሚቸረው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0UW31kyh9nzYLdKWTNyJGx9JXWPxYxGH51vjHrty2U58RGvbAAft5SXgfecRNewQFl
***************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከእስያ በማገናኘት የጎላ አበርክቶ እንዳለው የሲንጋፖር የጉዞና ጭነት አገልግሎት ወኪሎች ገለፁ፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሲንጋፖር ለሀገሪቱ ለተጓዦች፣ የጉዞና የጭነት አገልግሎት ወኪሎች የማበረታቻ ሽልማት መስጠቱ ይታወቃል፡፡
ኢነርጂያ፣ ሲንጋፖር ፖስት ኃ/የተ/የግ/ ማህበር፣ ኤርሰርቭ ግሩፕ፣ ሲቲስቴት ትራቭል፣ እና ኤር ፍራይት ሲንጋፖር እውቅና የተሰጣቸው ተቋማት ናቸው።
የሲቲስቴት ተራቭል ዋና ዳይሬክተር አልበርቶ ሆ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሲንጋፖር ያዘጋጀው ሁነት አየር መንገዱ ምን ያህል ታላቅና እንዴት ውጤታማ እንደሆነ ለመረዳት አስችሎኛል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከሲንጋፖር ለማስተሳሰር የሚያደርገው አስደናቂ እንቅስቃሴ አድናቆት የሚቸረው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0UW31kyh9nzYLdKWTNyJGx9JXWPxYxGH51vjHrty2U58RGvbAAft5SXgfecRNewQFl
👍26❤5
ሩድ ቫኔስትሮይ ማንቺስተር ዩናይትድን መልቀቁ ተነገረ
**************
የማንቺስተር ዩናይትድ ረዳት አሰልጣኝ የነበረው ሩድ ቫኔስትሮይ ከክለቡ መልቀቁ ተነግሯል።
ሩድ ቫኔስትሮይ በክለቡ በረዳት አሰልጣኝነት ሲያገለግል የነበረ ሲሆን አሰልጣኝ ቴን ሃግ ከለቀቁ በኋላ ደግሞ በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት ያለፉትን አራት ጨዋታዎች መርቷል።
አዲሱ የማንቺስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ክለቡን በይፋ መቀላቀሉ የተገለፀ ሲሆን፤ ሩድ ቫኔስትሮይ የአሰልጣኞች ስታፍ አባል ሆኖ እንደማይቀጥልም ክለቡ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል፡፡
**************
የማንቺስተር ዩናይትድ ረዳት አሰልጣኝ የነበረው ሩድ ቫኔስትሮይ ከክለቡ መልቀቁ ተነግሯል።
ሩድ ቫኔስትሮይ በክለቡ በረዳት አሰልጣኝነት ሲያገለግል የነበረ ሲሆን አሰልጣኝ ቴን ሃግ ከለቀቁ በኋላ ደግሞ በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት ያለፉትን አራት ጨዋታዎች መርቷል።
አዲሱ የማንቺስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ክለቡን በይፋ መቀላቀሉ የተገለፀ ሲሆን፤ ሩድ ቫኔስትሮይ የአሰልጣኞች ስታፍ አባል ሆኖ እንደማይቀጥልም ክለቡ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል፡፡
👍29❤5👏3