የ"ማያዬ" አልበም ምርቃት ሰኔ 22 ይካሄዳል
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ማያዬ" የአልበም ምርቃት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም አመሸሻ ላይ በማሪዮት ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
በዚህ የአልበም ምርቃት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ከለምለም ኃ/ሚካኤል በተጨማሪም ድምጻዊያኑ ግርማ ተፈራ ካሣ ፣ ግዛቸው ተሾመ ፣ ኤደን አይሸሹም እና ሌሎችም የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ማያዬ" የተሰኘ የመጀመሪያ አልበም ባሳለፍነው ወር ግንቦት 9 2016 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ የዩቲዩብ ቻናል እና በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች በኩል ለአድማጮች እንደደረሰ ይታወሳል።
ለተጨማሪ: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ማያዬ" የአልበም ምርቃት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም አመሸሻ ላይ በማሪዮት ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
በዚህ የአልበም ምርቃት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ከለምለም ኃ/ሚካኤል በተጨማሪም ድምጻዊያኑ ግርማ ተፈራ ካሣ ፣ ግዛቸው ተሾመ ፣ ኤደን አይሸሹም እና ሌሎችም የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ማያዬ" የተሰኘ የመጀመሪያ አልበም ባሳለፍነው ወር ግንቦት 9 2016 ዓ.ም በናሆም ሪከርድስ የዩቲዩብ ቻናል እና በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች በኩል ለአድማጮች እንደደረሰ ይታወሳል።
ለተጨማሪ: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ዶሳይስ" የተሰኘ መጽሐፍ ቅዳሜ ይመረቃል
የደራሲና ገጣሚ ኩሪ አየለ "ዶሳይስ" የተሰኘ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሐፍ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ውስጥ ይመረቃል።
በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል ፣የሻው ተሰማ ፣ሳሙኤል ተስፋዬ ፣ ሔኖክ በሪሁን እና ሌሎችም ይገኛሉ ተብሏል።
ደራሲና ገጣሚ ኩሪ አየለ ከዚህ ቀደም "ቁርጥራጭ ትንፋሾች" እና "የተሰነቀሩ ጥማቶች" የተሰኙ የግጥም መጻሕፍትን ለአንባቢያን አድርሳለች።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የደራሲና ገጣሚ ኩሪ አየለ "ዶሳይስ" የተሰኘ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሐፍ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ውስጥ ይመረቃል።
በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል ፣የሻው ተሰማ ፣ሳሙኤል ተስፋዬ ፣ ሔኖክ በሪሁን እና ሌሎችም ይገኛሉ ተብሏል።
ደራሲና ገጣሚ ኩሪ አየለ ከዚህ ቀደም "ቁርጥራጭ ትንፋሾች" እና "የተሰነቀሩ ጥማቶች" የተሰኙ የግጥም መጻሕፍትን ለአንባቢያን አድርሳለች።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የቡና አውደርዕይ በሐዋሳና ጅማ ከተሞች ሊካሄድ ነው
የቡና ላኪዎችና አቅራቢዎች በቀጥታ ትስስር ሊያገናኝ የሚችል የቡና አውደርዕይ ሊያዘጋጅ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የቡና አውደርዕይ በሐዋሳ ከተማ ከሰኔ 21 እስከ 22 ቀን 2016 ዓም እንዲሁም በጅማ ከሰኔ 26 እስከ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል።
አውደርዕዩ በዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ይበልጥ ለማሳደግ ያግዛል ያሉት ዶክተር አዱኛ፤ከኤግዚቢሽኑ ጎን ለጎን የተለያዩ ፓናል ውይይት ይደረጋል ብለዋል።
እስካሁን ከ300 በላይ አቅራቢዎች በአውደርዕዩ ለመሳተፍ ተመዝግበው የምርት ናሙና አቅርበዋል። ከመቶ በላይ ላኪዎችም ለመሳተፍ ፍላጎት ማሳየታቸውን ጠቁመዋል።
📍መረጃው የኢፕድ ነው ።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የቡና ላኪዎችና አቅራቢዎች በቀጥታ ትስስር ሊያገናኝ የሚችል የቡና አውደርዕይ ሊያዘጋጅ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የቡና አውደርዕይ በሐዋሳ ከተማ ከሰኔ 21 እስከ 22 ቀን 2016 ዓም እንዲሁም በጅማ ከሰኔ 26 እስከ 27 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል።
አውደርዕዩ በዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ይበልጥ ለማሳደግ ያግዛል ያሉት ዶክተር አዱኛ፤ከኤግዚቢሽኑ ጎን ለጎን የተለያዩ ፓናል ውይይት ይደረጋል ብለዋል።
እስካሁን ከ300 በላይ አቅራቢዎች በአውደርዕዩ ለመሳተፍ ተመዝግበው የምርት ናሙና አቅርበዋል። ከመቶ በላይ ላኪዎችም ለመሳተፍ ፍላጎት ማሳየታቸውን ጠቁመዋል።
📍መረጃው የኢፕድ ነው ።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አራት ደራሲያን የተጋበዙበት"ቆይታ ከደራሲያን ጋር" የተሰኘ የመጻሕፍት ውይይት ቅዳሜ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም በ’ክለብ ሀውስ’ መተግበሪያ የመጻሕፍት ውይይት አራተኛ ዙር መርሐግብር ከደራሲያን እና ተጋባዥ እንግዶች ጋር የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 11:30 ድረስ ፊትለፊት ውይይት እንደሚካሄድ ኤቨንት ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዚህ የውይይት መርሐግብር ላይ "የሦስት ትውልዶች ወግ በመጻሕፍት፣ ንባብና ሌሎች ርዕስ ጉዳዮች "በሚል ርዕስ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ፣ ከዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ ፣ ከደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ እና ከፕ/ር ጴጥሮስ ቶጃ ጋር ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ፊትለፊት በሚገኘው ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
ዝግጅቱ ላይ ለመታደም አስቀድሞ መመዝገብ የሚያስፈልግ ሲሆን ለመመዝገብ ሊንኩን ተጠቀሙ https://cutt.ly/KesyFuqf ተብላችኋል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም በ’ክለብ ሀውስ’ መተግበሪያ የመጻሕፍት ውይይት አራተኛ ዙር መርሐግብር ከደራሲያን እና ተጋባዥ እንግዶች ጋር የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 11:30 ድረስ ፊትለፊት ውይይት እንደሚካሄድ ኤቨንት ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዚህ የውይይት መርሐግብር ላይ "የሦስት ትውልዶች ወግ በመጻሕፍት፣ ንባብና ሌሎች ርዕስ ጉዳዮች "በሚል ርዕስ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ፣ ከዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ ፣ ከደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ እና ከፕ/ር ጴጥሮስ ቶጃ ጋር ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ፊትለፊት በሚገኘው ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
ዝግጅቱ ላይ ለመታደም አስቀድሞ መመዝገብ የሚያስፈልግ ሲሆን ለመመዝገብ ሊንኩን ተጠቀሙ https://cutt.ly/KesyFuqf ተብላችኋል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ኦሎምፒክ" የተሰኘ ግዙፍ የሙዚቃ ኮንሰርት በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ ሊካሄድ ነው
በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ "ኦሎምፒክ" የተሰኘ ግዙፍ ኮንሰርት ሊካሄድ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ሌብል ዋን ኢንተርቴይመንት እንደሰማሁ ከሆነ በዚህ ግዙፍ ኮንሰርት ላይ አንጋፋዎቹ ድምጻዊያን ንዋይ ደበበ ፣ ዳዊት መለሠ፣ ሸዋዳኝ ኃይሉ ፣ታደለ ሮባ ከወጣቶቹ ድምጻዊያን አንዱዓለም ጎሳ ፣ ሔለን በሪሔ እና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
ሐምሌ 9 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ይካሄዳል የተባለው ኮንሰርቱ መግቢያው ከ500 ብር ጀምሮ እንደሆነ ድረገጻችን ከአዘጋጆቹ ሰምቷል።
ለረጅም ጊዜያት ከኃይማኖታዊና መንግስታዊ ዝግጅቶች ውጪ ያልተካሄደበት መስቀል አደባባይ ይህንን የሙዚቃ ኮንሰርት በቅርቡ ያስተናግዳል ተብሏል።
የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በፈረንሳይ አዘጋጅነት ከሐምሌ 19 2016 ዓ.ም ጀምሮ በፓሪስ ከተማ እንደሚካሄድ ይታወሳል።
📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ!
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ "ኦሎምፒክ" የተሰኘ ግዙፍ ኮንሰርት ሊካሄድ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ሌብል ዋን ኢንተርቴይመንት እንደሰማሁ ከሆነ በዚህ ግዙፍ ኮንሰርት ላይ አንጋፋዎቹ ድምጻዊያን ንዋይ ደበበ ፣ ዳዊት መለሠ፣ ሸዋዳኝ ኃይሉ ፣ታደለ ሮባ ከወጣቶቹ ድምጻዊያን አንዱዓለም ጎሳ ፣ ሔለን በሪሔ እና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
ሐምሌ 9 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ይካሄዳል የተባለው ኮንሰርቱ መግቢያው ከ500 ብር ጀምሮ እንደሆነ ድረገጻችን ከአዘጋጆቹ ሰምቷል።
ለረጅም ጊዜያት ከኃይማኖታዊና መንግስታዊ ዝግጅቶች ውጪ ያልተካሄደበት መስቀል አደባባይ ይህንን የሙዚቃ ኮንሰርት በቅርቡ ያስተናግዳል ተብሏል።
የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በፈረንሳይ አዘጋጅነት ከሐምሌ 19 2016 ዓ.ም ጀምሮ በፓሪስ ከተማ እንደሚካሄድ ይታወሳል።
📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ!
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ሚዲያ አዋርድ" የተሰኘ ሽልማት ሊካሄድ ነው
በኢትዮጵያ ሚዲያዎች ላይ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ እና በጋዜጦች ላይ የሚሰሩ የሚዲያ ባለሞያዎችን የሚሸልመዉ "ሚዲያ አዋርድ" በወርሐ ነሐሴ ይካሄዳል ተብሏል።
የአዋርዱ አዘጋጆች ከባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ የተላለፉ ፕሮግራሞች እና ለሰባት ወራት በስራ ላይ የነበሩ የሚዲያ ባለሞያዎች ብቻ በእጩነት እንደቀረቡ ያነሱ ሲሆን በአዋርዱ ላይ የቀረቡት ሁሉም እጩዎች መስፈርቶችን ያሟሉት ብቻ ናቸዉ ተብሏል።
አሸናፊዎች በዳኞች እና በህዝብ ድምፅ የሚመረጡ ሲሆን ህዝቡ በመጀመሪያ ዙር በኦንላይ ethio-mediaaward.com በመግባት ድምፅ መስጠት ይችላልም ብለዋል።
አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የመጀመሪያው ‘የሚዲያ አዋርድ’ የህይወት ዘመን ተሸላሚ እንደሆነች አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
የመጀመሪያዉ የሽልማት ፕሮግራም ዘርፎች
1.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ወንድ ዜና አንባቢ
2. የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ሴት ዜና አንባቢ
3.የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ ሴት ዜና አንባቢ
4. የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ ወንድ ዜና አንባቢ
5.የዓመቱ ምርጥ የስፖርት ፕሮግራም
6.የዓመቱ የህዝብ ምርጫ/ምርጥ ጋዜጠኛ
7.የዓመቱ ምርጥ አይደል ሾዉ
8.የዓመቱ ምርጥ ዶክመንተሪ
9.የዓመቱ ምርጥ የዜና ዘገባ
10.የዓመቱ ምርጥ አርቲክል/ፕሪንት ሚዲያ
11.የዓመቱ ምርጥ ዲጄ
12.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ
13.የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ ጣቢያ
14.የዓመቱ ምርጥ ጋዜጣ
15.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራም
16.የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ የመዝናኛ ፕሮግራም
17.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራም ወንድ አቅራቢ
18.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራም ሴት አቅራቢ
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በኢትዮጵያ ሚዲያዎች ላይ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ እና በጋዜጦች ላይ የሚሰሩ የሚዲያ ባለሞያዎችን የሚሸልመዉ "ሚዲያ አዋርድ" በወርሐ ነሐሴ ይካሄዳል ተብሏል።
የአዋርዱ አዘጋጆች ከባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ የተላለፉ ፕሮግራሞች እና ለሰባት ወራት በስራ ላይ የነበሩ የሚዲያ ባለሞያዎች ብቻ በእጩነት እንደቀረቡ ያነሱ ሲሆን በአዋርዱ ላይ የቀረቡት ሁሉም እጩዎች መስፈርቶችን ያሟሉት ብቻ ናቸዉ ተብሏል።
አሸናፊዎች በዳኞች እና በህዝብ ድምፅ የሚመረጡ ሲሆን ህዝቡ በመጀመሪያ ዙር በኦንላይ ethio-mediaaward.com በመግባት ድምፅ መስጠት ይችላልም ብለዋል።
አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የመጀመሪያው ‘የሚዲያ አዋርድ’ የህይወት ዘመን ተሸላሚ እንደሆነች አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
የመጀመሪያዉ የሽልማት ፕሮግራም ዘርፎች
1.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ወንድ ዜና አንባቢ
2. የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ሴት ዜና አንባቢ
3.የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ ሴት ዜና አንባቢ
4. የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ ወንድ ዜና አንባቢ
5.የዓመቱ ምርጥ የስፖርት ፕሮግራም
6.የዓመቱ የህዝብ ምርጫ/ምርጥ ጋዜጠኛ
7.የዓመቱ ምርጥ አይደል ሾዉ
8.የዓመቱ ምርጥ ዶክመንተሪ
9.የዓመቱ ምርጥ የዜና ዘገባ
10.የዓመቱ ምርጥ አርቲክል/ፕሪንት ሚዲያ
11.የዓመቱ ምርጥ ዲጄ
12.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ
13.የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ ጣቢያ
14.የዓመቱ ምርጥ ጋዜጣ
15.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራም
16.የዓመቱ ምርጥ የሬዲዮ የመዝናኛ ፕሮግራም
17.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራም ወንድ አቅራቢ
18.የዓመቱ ምርጥ የቴሌቪዥን የመዝናኛ ፕሮግራም ሴት አቅራቢ
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ጋዜጠኛ ዮሴፍ ኃይሌ አረፈ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ ዮሴፍ ኃይሌ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት በተወለደ 44 ዓመቱ አርፏል፡፡
ጋዜጠኛ ዮሴፍ ኃይሌ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን መዝናኛ ቻናል ከሪፖርተር እስከ ረዳት ኤዲተርነት ላለፉት 15 ዓመታት አገልግሏል፡፡
የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት በርካታ ዓመታትን ያገለገለው ዮሴፍ ኃይሌ፤ በተለይም የብዙዎች ትዝታ የሆነውን እንደ “ታላቅ ፊልም” ያሉ ስራዎችን ለስርጭት እንዲስማሙ አድርጎ በማቅረብ ይታወቃል፡፡
📍መረጃው የኢቢሲ መዝናኛ ቻናል ነው።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ ዮሴፍ ኃይሌ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት በተወለደ 44 ዓመቱ አርፏል፡፡
ጋዜጠኛ ዮሴፍ ኃይሌ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን መዝናኛ ቻናል ከሪፖርተር እስከ ረዳት ኤዲተርነት ላለፉት 15 ዓመታት አገልግሏል፡፡
የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት በርካታ ዓመታትን ያገለገለው ዮሴፍ ኃይሌ፤ በተለይም የብዙዎች ትዝታ የሆነውን እንደ “ታላቅ ፊልም” ያሉ ስራዎችን ለስርጭት እንዲስማሙ አድርጎ በማቅረብ ይታወቃል፡፡
📍መረጃው የኢቢሲ መዝናኛ ቻናል ነው።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የገጣሚና ደራሲ ኤፍሬም ስዩም "ምልኪና ቡና " የተሰኘ አዲስ የግጥም መድብል ገበያ ላይ ውሏል።
“ሶሊያና” በተሰኘው የግጥም መድብሉ ዕውቅናን ያገኘው ደራሲው ዘጠነኛ መፅሐፉን ለንባብ አብቅቷል።
በግጥም መድብሉ ላይ የተካተቱት ግጥምች በ2012 እና ከዛም ቀደም ብለው የተፃፉ ሲሆኑ መፅሐፉ በ216 ገፆች የተቀነበበ ነው።
ደራሲው ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የመሰንበቻ መሰናዶ ጋር በነበረው ቆይታ ለስድስት ዓመታት መፅሐፍ ከማሳተም ርቆ የቆየ መሆኑን ገልፆል::
አሁን ግን ወደ አራት ስራዎች እጁ ላይ እንዳሉ ተናግሮ "ምልኪና ቡና" የተሰኘው ስራው ከአራቱ አንዱ ሲሆን በቀጣይ ሌሎቹም ለንባብ እንደሚበቁ አሳውቋል።
በግጥም መድብሉ ላይ በርካታ ሃሳቦች እንደተነሱት የሚገልጸው ኤፍሬም የተዋጡ ሃሳቦችን በግጥም መልክ ማውጣት ተችሏል ብሏል።
ደራሲው አያይዞም የግጥም ስራዎቹን በድምፅ በማስቀረፅ ለአንባቢያን እንደሚያቀርብም አስታውቋል።
📍መረጃው የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ነው።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
“ሶሊያና” በተሰኘው የግጥም መድብሉ ዕውቅናን ያገኘው ደራሲው ዘጠነኛ መፅሐፉን ለንባብ አብቅቷል።
በግጥም መድብሉ ላይ የተካተቱት ግጥምች በ2012 እና ከዛም ቀደም ብለው የተፃፉ ሲሆኑ መፅሐፉ በ216 ገፆች የተቀነበበ ነው።
ደራሲው ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 የመሰንበቻ መሰናዶ ጋር በነበረው ቆይታ ለስድስት ዓመታት መፅሐፍ ከማሳተም ርቆ የቆየ መሆኑን ገልፆል::
አሁን ግን ወደ አራት ስራዎች እጁ ላይ እንዳሉ ተናግሮ "ምልኪና ቡና" የተሰኘው ስራው ከአራቱ አንዱ ሲሆን በቀጣይ ሌሎቹም ለንባብ እንደሚበቁ አሳውቋል።
በግጥም መድብሉ ላይ በርካታ ሃሳቦች እንደተነሱት የሚገልጸው ኤፍሬም የተዋጡ ሃሳቦችን በግጥም መልክ ማውጣት ተችሏል ብሏል።
ደራሲው አያይዞም የግጥም ስራዎቹን በድምፅ በማስቀረፅ ለአንባቢያን እንደሚያቀርብም አስታውቋል።
📍መረጃው የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ነው።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሸነን አፍሪካ የፋሽን እና የስፖርት ፌስቲቫል
ሸነን አፍሪካ የመጀመሪያው ዓመት የፋሽን እና የስፖርት ፌስቲቫል ከአርብ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በዚህ ኩነት ላይ የአፍሪካ የቀድሞ ከዋክብት እና በአውሮፓ ታላላቅ ክለባት በመጫወት ላይ የሚገኙ ተጨዋቾችን ጨምሮ ፣ሥመ ጥር ታዋቂ ሰዎች፣የፊልም እና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ ዲዛይነሮችና ሞዴሎች እንደሚገኙ ተነግሯል።
ዝግጅቱ ከፊታችን አርብ ሰኔ 21 እስከ እሁድ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ስታዲየም እና በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
በዚህ ፌስቲቫል ከሚገኙት መካከል ቶማስ ፓርቲ ካኑ፣ ዳንኤል አሞካቺ፣ማማዱ ሳአኮ፤አዳማ ትራኦሬ፣ታሪቦ ዌስት፣ ሄነሪ ካማራ ይኖራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሸነን አፍሪካ የመጀመሪያው ዓመት የፋሽን እና የስፖርት ፌስቲቫል ከአርብ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
በዚህ ኩነት ላይ የአፍሪካ የቀድሞ ከዋክብት እና በአውሮፓ ታላላቅ ክለባት በመጫወት ላይ የሚገኙ ተጨዋቾችን ጨምሮ ፣ሥመ ጥር ታዋቂ ሰዎች፣የፊልም እና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች፣ ዲዛይነሮችና ሞዴሎች እንደሚገኙ ተነግሯል።
ዝግጅቱ ከፊታችን አርብ ሰኔ 21 እስከ እሁድ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በአዲስ አበባ ስታዲየም እና በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።
በዚህ ፌስቲቫል ከሚገኙት መካከል ቶማስ ፓርቲ ካኑ፣ ዳንኤል አሞካቺ፣ማማዱ ሳአኮ፤አዳማ ትራኦሬ፣ታሪቦ ዌስት፣ ሄነሪ ካማራ ይኖራሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
Event Addis Media
Photo
የሐሙስ መረጃዎች
የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥሎው ይቀርባሉ!
📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ!
1.የድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሣሁን(ቴዲ አፍሮ) የሙዚቃ ኮንሰርት የፊታችን እሁድ ሰኔ 23 2016 ዓ.ም 17 ሺ ተመልካቾችን በሚያስተናግደው የሙዚቃ እና ሌሎች የመዝናኛ ዘርፎች ማቅረቢያ በሆነው በዱባዩ ኮካኮላ አሬና ስታዲየም ውስጥ ይካሄዳል። ድምጻዊው ለዚህ የሙዚቃ ዝግጅቱ ከቀናት በፊት ዱባይ መግባቱ ይታወሳል።
2. የድምጻዊ አብዱ ኪያር "ፓፓፓ" የተሰኘ አልበም ነገ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም በራሱ ዩቲዩብ ቻናል እና በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል። በአልበሙ ላይ በቅንብር ስማገኘሁ ሳሙኤል፣ ኪሩቤል ተስፋዬ፣ ካሙዙ ካሳ እና ዳዊት ቦስኮ ተሳትፈዋል። ሚክሲንጉን የሰሩት ስማገኘሁ ሳሙኤል እና ኪሩቤል ተስፋዬ ሲሆኑ ማስተሪንግ ደግሞ በአበጋዝ ክብረወርቅ ተሰርቷል።
3.የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ማያዬ" የአልበም ምርቃት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም አመሸሻ ላይ በማሪዮት ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
በዚህ የአልበም ምርቃት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ከለምለም ኃ/ሚካኤል በተጨማሪም ድምጻዊያኑ ግርማ ተፈራ ካሣ ፣ ግዛቸው ተሾመ ፣ ኤደን አይሸሹም እና ሌሎችም የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
4.በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ "ኦሎምፒክ" የተሰኘ ግዙፍ ኮንሰርት የፊታችን ሐምሌ 9 2016 ዓ.ም ሊካሄድ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ሌብል ዋን ኢንተርቴይመንት እንደሰማሁ ከሆነ በዚህ ግዙፍ ኮንሰርት ላይ አንጋፋዎቹ ድምጻዊያን ንዋይ ደበበ፣ዳዊት መለሠ፣ ሸዋንዳኝ ኃይሉ፣ታደለ ሮባ ከወጣቶቹ ድምጻዊያን አንዱዓለም ጎሳ፣ሔለን በሪሔ እና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
5.የድምጻዊ ማስተዋል እያዩ "እመጣለሁ " የተሰኘ የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች ይደርሳል። የሙዚቃ ቪዲዮው ዳይሬክተር ነፃዓለም አብዲ ሲሆን የሙዚቃው ግጥምና ዜማ በአቡዲ ተሰርቷል።የሙዚቃ ቅንብሩ ደግሞ በሚካኤል ኃይሉ ተከውኗል።
6.የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም በ’ክለብ ሀውስ’ መተግበሪያ የመጻሕፍት ውይይት አራተኛ ዙር መርሐግብር ከደራሲያን እና ተጋባዥ እንግዶች ጋር የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 11:30 ድረስ በአካል ውይይት ይካሄዳል።በዚህ የውይይት መርሐግብር ላይ "የሦስት ትውልዶች ወግ በመጻሕፍት፣ ንባብና ሌሎች ርዕስ ጉዳዮች"በሚል ርዕስ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ፣ ከዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ፣ ከደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ እና ከፕ/ር ጴጥሮስ ቶጃ ጋር ከእስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ፊትለፊት በሚገኘው ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
7.በዛጎል መጻሕፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጽሐፍ ውይይት የፊታችን ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት ከዶ/ር ስንታየሁ ካሣ እና ከደራሲ በሁሉም አለበል ጋር "ታሪክ የምትስመክርልን ካሣ ገብረማርያም " እና "የተዳፈነዉ ታሪክ: ራስ ጉግሳ ወሌ" በተሰኙ መጻሕፍት ላይ ውይይት ይካሄዳል።የዕለቱ አወያይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው። ይህ መርሐግብር ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 10:30 ይካሄዳል።
8.የደራሲና ገጣሚ ኩሪ አየለ "ዶሳይስ" የተሰኘ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሐፍ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ውስጥ ይመረቃል።በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል ፣መምህር የሻው ተሰማ ፣ አርቲስት ሳሙኤል ተስፋዬ ፣ አርቲስት ሔኖክ በሪሁን እና ሌሎችም ይገኛሉ ተብሏል።
9.የደራሲ ዓላማውም ታዬ " communication coach" የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በልደታ ክ/ከተማ አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል። መጽሐፉ በ100 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ከተመረቀ በኃላ በጃፋር መጻሕፍት መደብር እና በሌሎችም አማራጮች ለአንባቢያን ይደርሳል ተብሏል።
10.በሠዓሊ ዳዊት ገረሱ "አሁን " በተሰኘው የሥዕል አውደርዕይ ላይ ነገ አርብ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ስድሰት ኪሎ በሚገኘው በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ ሙዚየም ውስጥ ውይይት ይካሄዳል። በዕለቱም መምህር በቀለ መኮንን፣ሐሌታ ይረጋ ፣ ነፃነት ገብረሚካኤል ሀሳቦቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
አዘጋጅ: ናቲ ማናዬ
ቀን: ሰኔ 20 2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በድረገጻችን በተሻለ አቀራረብ ያንብቡ:
https://eventaddis.com
ቴሌግራም: @EventAddis1
የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥሎው ይቀርባሉ!
📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ!
1.የድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሣሁን(ቴዲ አፍሮ) የሙዚቃ ኮንሰርት የፊታችን እሁድ ሰኔ 23 2016 ዓ.ም 17 ሺ ተመልካቾችን በሚያስተናግደው የሙዚቃ እና ሌሎች የመዝናኛ ዘርፎች ማቅረቢያ በሆነው በዱባዩ ኮካኮላ አሬና ስታዲየም ውስጥ ይካሄዳል። ድምጻዊው ለዚህ የሙዚቃ ዝግጅቱ ከቀናት በፊት ዱባይ መግባቱ ይታወሳል።
2. የድምጻዊ አብዱ ኪያር "ፓፓፓ" የተሰኘ አልበም ነገ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም በራሱ ዩቲዩብ ቻናል እና በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል። በአልበሙ ላይ በቅንብር ስማገኘሁ ሳሙኤል፣ ኪሩቤል ተስፋዬ፣ ካሙዙ ካሳ እና ዳዊት ቦስኮ ተሳትፈዋል። ሚክሲንጉን የሰሩት ስማገኘሁ ሳሙኤል እና ኪሩቤል ተስፋዬ ሲሆኑ ማስተሪንግ ደግሞ በአበጋዝ ክብረወርቅ ተሰርቷል።
3.የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል "ማያዬ" የአልበም ምርቃት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም አመሸሻ ላይ በማሪዮት ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
በዚህ የአልበም ምርቃት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ከለምለም ኃ/ሚካኤል በተጨማሪም ድምጻዊያኑ ግርማ ተፈራ ካሣ ፣ ግዛቸው ተሾመ ፣ ኤደን አይሸሹም እና ሌሎችም የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
4.በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ "ኦሎምፒክ" የተሰኘ ግዙፍ ኮንሰርት የፊታችን ሐምሌ 9 2016 ዓ.ም ሊካሄድ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከአዘጋጆቹ ሌብል ዋን ኢንተርቴይመንት እንደሰማሁ ከሆነ በዚህ ግዙፍ ኮንሰርት ላይ አንጋፋዎቹ ድምጻዊያን ንዋይ ደበበ፣ዳዊት መለሠ፣ ሸዋንዳኝ ኃይሉ፣ታደለ ሮባ ከወጣቶቹ ድምጻዊያን አንዱዓለም ጎሳ፣ሔለን በሪሔ እና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
5.የድምጻዊ ማስተዋል እያዩ "እመጣለሁ " የተሰኘ የሙዚቃ ቪዲዮ በቅርቡ ለተመልካቾች ይደርሳል። የሙዚቃ ቪዲዮው ዳይሬክተር ነፃዓለም አብዲ ሲሆን የሙዚቃው ግጥምና ዜማ በአቡዲ ተሰርቷል።የሙዚቃ ቅንብሩ ደግሞ በሚካኤል ኃይሉ ተከውኗል።
6.የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም በ’ክለብ ሀውስ’ መተግበሪያ የመጻሕፍት ውይይት አራተኛ ዙር መርሐግብር ከደራሲያን እና ተጋባዥ እንግዶች ጋር የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 11:30 ድረስ በአካል ውይይት ይካሄዳል።በዚህ የውይይት መርሐግብር ላይ "የሦስት ትውልዶች ወግ በመጻሕፍት፣ ንባብና ሌሎች ርዕስ ጉዳዮች"በሚል ርዕስ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ፣ ከዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ፣ ከደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ እና ከፕ/ር ጴጥሮስ ቶጃ ጋር ከእስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ፊትለፊት በሚገኘው ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
7.በዛጎል መጻሕፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጽሐፍ ውይይት የፊታችን ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት ከዶ/ር ስንታየሁ ካሣ እና ከደራሲ በሁሉም አለበል ጋር "ታሪክ የምትስመክርልን ካሣ ገብረማርያም " እና "የተዳፈነዉ ታሪክ: ራስ ጉግሳ ወሌ" በተሰኙ መጻሕፍት ላይ ውይይት ይካሄዳል።የዕለቱ አወያይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው። ይህ መርሐግብር ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 10:30 ይካሄዳል።
8.የደራሲና ገጣሚ ኩሪ አየለ "ዶሳይስ" የተሰኘ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መጽሐፍ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ውስጥ ይመረቃል።በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል ፣መምህር የሻው ተሰማ ፣ አርቲስት ሳሙኤል ተስፋዬ ፣ አርቲስት ሔኖክ በሪሁን እና ሌሎችም ይገኛሉ ተብሏል።
9.የደራሲ ዓላማውም ታዬ " communication coach" የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በልደታ ክ/ከተማ አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል። መጽሐፉ በ100 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ከተመረቀ በኃላ በጃፋር መጻሕፍት መደብር እና በሌሎችም አማራጮች ለአንባቢያን ይደርሳል ተብሏል።
10.በሠዓሊ ዳዊት ገረሱ "አሁን " በተሰኘው የሥዕል አውደርዕይ ላይ ነገ አርብ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ስድሰት ኪሎ በሚገኘው በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ ሙዚየም ውስጥ ውይይት ይካሄዳል። በዕለቱም መምህር በቀለ መኮንን፣ሐሌታ ይረጋ ፣ ነፃነት ገብረሚካኤል ሀሳቦቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
አዘጋጅ: ናቲ ማናዬ
ቀን: ሰኔ 20 2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በድረገጻችን በተሻለ አቀራረብ ያንብቡ:
https://eventaddis.com
ቴሌግራም: @EventAddis1
«የመኸር ለሊት ሕልም» የተሰኘ ተውኔት ዛሬ ይቀርባል
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ የማታ ተማሪዎች የተዘጋጀው «የመኸር ለሊት ሕልም» የተሰኘ ተውኔት ዛሬ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም 5 ኪሎ በሚገኘው ፋርማ ግቢ ውስጥ ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ ለታዳሚያን ይቀርባል ተብሏል።
"የመኸር ለሊት ህልም" ድርሰት ዋሊያም ሼኪስፒር ፣ትርጉም በላይነህ አቡኔ፣ አዘጋጅ ናፖሊዮን አለሙ።
ተዋናኒያን ተስፋአብ ለገሰ ፣ፍቅር ተስፋዬ ፣አድኖን ነጋሽ ፣ትዝታ ማናዬ እና ሌሎችም ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ይገኛሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ የማታ ተማሪዎች የተዘጋጀው «የመኸር ለሊት ሕልም» የተሰኘ ተውኔት ዛሬ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም 5 ኪሎ በሚገኘው ፋርማ ግቢ ውስጥ ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ ለታዳሚያን ይቀርባል ተብሏል።
"የመኸር ለሊት ህልም" ድርሰት ዋሊያም ሼኪስፒር ፣ትርጉም በላይነህ አቡኔ፣ አዘጋጅ ናፖሊዮን አለሙ።
ተዋናኒያን ተስፋአብ ለገሰ ፣ፍቅር ተስፋዬ ፣አድኖን ነጋሽ ፣ትዝታ ማናዬ እና ሌሎችም ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ይገኛሉ ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት ትዕግሥት ግርማ የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማህበር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና ተሾመች
አለምአቀፋዊ ማህበር የሆነው የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማህበር አርቲስት ትዕግሥት ግርማን የበጎ ፍቃድ አምባሳደር አድርጎ እንደሾመ ዛሬ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም በቤስት ዌስተርን ፕላስ ሆቴል በተካሄደ የፊርማ ሥነሥርዓት ወቅት ገልጿል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማህበር ምስረታውን ካደረገበት ጊዜ እንስቶ ዘር፣ ቀለም ሀይማኖትም ሆነ ማንነት ያልገደበው ሰብዓዊ ድጋፍ እና አገልግሎትን በኢትዮጵያ የተለያዩ አከባቢዎች እየተዘዋወር በመስጠት ላይ የሚገኝ ማህበር ነው ተብሏል።
ማህበሩ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች 35 የሚሆኑ የህክምና ጉዞዎችን በማድረግ ሰብዓዊነትን ባስቀደመ ተግባሩ ከ25 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሰብዓዊ ግልጋሎት ሰጥቷል።
በቀጣይም ማህበሩ አቅም ለሌላቸው ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ እና የሕክምና አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች ሙያዊ ፍቅር እና አክብሮት የታነጸ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት፤ የህክምና አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የድጋፍ ስራዎችን በአቅም ግንባታ እና በግብዓት ማሟላት ያተኮረ ስራን ለመስራት አቅዷል፡፡
በእዚህ መነሻነትም ማህበሩ ከእዚህ ቀደም ከሰራቸው የሰብዓዊነት ስራዎች በተጨማሪ በእዚህ ወቅት እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን እና ወደፊት ሊከውን ያቀዳቸውን ውጥኖቹን መነሻ በማድረግ ተወዳጇን ተዋናይት እና የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ አርቲስት ትዕግስት ግርማን የበጎ አድራጎት አምባሳደር አድርጎ ሾሟል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አለምአቀፋዊ ማህበር የሆነው የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማህበር አርቲስት ትዕግሥት ግርማን የበጎ ፍቃድ አምባሳደር አድርጎ እንደሾመ ዛሬ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም በቤስት ዌስተርን ፕላስ ሆቴል በተካሄደ የፊርማ ሥነሥርዓት ወቅት ገልጿል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማህበር ምስረታውን ካደረገበት ጊዜ እንስቶ ዘር፣ ቀለም ሀይማኖትም ሆነ ማንነት ያልገደበው ሰብዓዊ ድጋፍ እና አገልግሎትን በኢትዮጵያ የተለያዩ አከባቢዎች እየተዘዋወር በመስጠት ላይ የሚገኝ ማህበር ነው ተብሏል።
ማህበሩ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች 35 የሚሆኑ የህክምና ጉዞዎችን በማድረግ ሰብዓዊነትን ባስቀደመ ተግባሩ ከ25 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሰብዓዊ ግልጋሎት ሰጥቷል።
በቀጣይም ማህበሩ አቅም ለሌላቸው ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ እና የሕክምና አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች ሙያዊ ፍቅር እና አክብሮት የታነጸ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት፤ የህክምና አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የድጋፍ ስራዎችን በአቅም ግንባታ እና በግብዓት ማሟላት ያተኮረ ስራን ለመስራት አቅዷል፡፡
በእዚህ መነሻነትም ማህበሩ ከእዚህ ቀደም ከሰራቸው የሰብዓዊነት ስራዎች በተጨማሪ በእዚህ ወቅት እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን እና ወደፊት ሊከውን ያቀዳቸውን ውጥኖቹን መነሻ በማድረግ ተወዳጇን ተዋናይት እና የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ አርቲስት ትዕግስት ግርማን የበጎ አድራጎት አምባሳደር አድርጎ ሾሟል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የበዓሉ ግርማ "ቤርሙዳ" ቴአትር ዛሬ አይቀርብም
በውድነህ ክፍሌ ተደርሶ በተሻለ አሰፍ የተዘጋጀውና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ የመጣው "በዓሉ ግርማ ቤርሙዳ" ቴአትር ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም "በአንድ ተዋናይ መቅረት" ምክንያት እንደማይቀርብ የተውኔቱ አዘጋጅ ውድነህ ክፍሌ አስታውቋል።
የተውኔቱ አዘጋጅ ውድነህ ክፍሌ ተውኔቱ ስለማይቀርብበት ምክንያት በማህበራዊ ትስስር ገፁ የሚከተለውን ብሏል።
"ሰሞኑን በ'በዓሉ ግርማ -ቤርሙዳ' ቴአትር እየገጠመን ያለውም ይኸው ነው።ባለፈው ሳምንት ማለትም ሰኔ 13 ተዋናይት ሳምራዊት ገ/ስላሴ የድምጽ መዘጋት ገጥሟት ነበር። ቴአትሩ አይታይም ከተባለ በኋላ በተአምር ለተመልካች ቀረበ "
"በእዚህኛው ሳምንት ደግሞ ተዋናይ ሰለሞን ሀጎስ ከምሽቱ 1፡30 ላይ እንዲህ የሚል መልዕክት ላከልን"በድንገተኛ የስራ ጥሪ ምክንያት ለጥናት በመግባቴ የነገው የመድረክ ተውኔት አይኖረንም ። አመሰግናለሁ" የሚል። እንግዲህ የሀገር ፍቅር ቴአትር ሱሉሉታ ወደሚገኘው ልህቀት ስፍራ ለጥናት ልኮት ነው። 'መውጣት ስለማይቻል አይገኝም' የሚል መልእክት የደረሰን። "
"የትኛውም ተዋናይ ችግር ሊገጥመው ይችላል። ቀድሞ መፍትሄ መፈለግ ግን ከባለሙያው ይጠበቃል።"
"ለማንኛውም በዛሬው ዕለት አንደኛ አመታችንን እናከብራለን ብላችሁ ለጠበቃችሁት የ"በዓሉ ግርማ ቤርሙዳ" ቴአትር አባላት ያው በቴክኒክ ምክንያት ኬካችን ለሌላ ጊዜ ተሸጋግሯል" ብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በውድነህ ክፍሌ ተደርሶ በተሻለ አሰፍ የተዘጋጀውና በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ የመጣው "በዓሉ ግርማ ቤርሙዳ" ቴአትር ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም "በአንድ ተዋናይ መቅረት" ምክንያት እንደማይቀርብ የተውኔቱ አዘጋጅ ውድነህ ክፍሌ አስታውቋል።
የተውኔቱ አዘጋጅ ውድነህ ክፍሌ ተውኔቱ ስለማይቀርብበት ምክንያት በማህበራዊ ትስስር ገፁ የሚከተለውን ብሏል።
"ሰሞኑን በ'በዓሉ ግርማ -ቤርሙዳ' ቴአትር እየገጠመን ያለውም ይኸው ነው።ባለፈው ሳምንት ማለትም ሰኔ 13 ተዋናይት ሳምራዊት ገ/ስላሴ የድምጽ መዘጋት ገጥሟት ነበር። ቴአትሩ አይታይም ከተባለ በኋላ በተአምር ለተመልካች ቀረበ "
"በእዚህኛው ሳምንት ደግሞ ተዋናይ ሰለሞን ሀጎስ ከምሽቱ 1፡30 ላይ እንዲህ የሚል መልዕክት ላከልን"በድንገተኛ የስራ ጥሪ ምክንያት ለጥናት በመግባቴ የነገው የመድረክ ተውኔት አይኖረንም ። አመሰግናለሁ" የሚል። እንግዲህ የሀገር ፍቅር ቴአትር ሱሉሉታ ወደሚገኘው ልህቀት ስፍራ ለጥናት ልኮት ነው። 'መውጣት ስለማይቻል አይገኝም' የሚል መልእክት የደረሰን። "
"የትኛውም ተዋናይ ችግር ሊገጥመው ይችላል። ቀድሞ መፍትሄ መፈለግ ግን ከባለሙያው ይጠበቃል።"
"ለማንኛውም በዛሬው ዕለት አንደኛ አመታችንን እናከብራለን ብላችሁ ለጠበቃችሁት የ"በዓሉ ግርማ ቤርሙዳ" ቴአትር አባላት ያው በቴክኒክ ምክንያት ኬካችን ለሌላ ጊዜ ተሸጋግሯል" ብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ዛሬ ሲኒማ ግቡ ፣ ፊልም ተመልከቱ !
እነዚህ አራት የፊልም ማሳያዎች(ሲኒማ ቤቶች) ዛሬን ጨምሮ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት እነዚህን ፊልሞች ለተመልካቾች ያቀርባሉ: ምስሎቹን ይመልከቱ።
የሲኒማ ቤቶቹ አድራሻ:
📍ሲኤምሲ ሚካኤል አካባቢ : ጋስት ሲኒማ
📍ለም ሆቴል አካባቢ: ቫምዳስ ሲኒማ
📍ጉርድ ሾላ አካባቢ : ሴንቸሪ ሲኒማ
📍ቦሌ አካባቢ : ዓለም ሲኒማ
መልካም የእረፍት ቀናት !
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
እነዚህ አራት የፊልም ማሳያዎች(ሲኒማ ቤቶች) ዛሬን ጨምሮ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት እነዚህን ፊልሞች ለተመልካቾች ያቀርባሉ: ምስሎቹን ይመልከቱ።
የሲኒማ ቤቶቹ አድራሻ:
📍ሲኤምሲ ሚካኤል አካባቢ : ጋስት ሲኒማ
📍ለም ሆቴል አካባቢ: ቫምዳስ ሲኒማ
📍ጉርድ ሾላ አካባቢ : ሴንቸሪ ሲኒማ
📍ቦሌ አካባቢ : ዓለም ሲኒማ
መልካም የእረፍት ቀናት !
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"አሁን" የተሰኘ የሥነጥበብ ውይይት ዛሬ ይካሄዳል
በሠዓሊ ዳዊት ገረሱ "አሁን " በተሰኘው የሥዕል አውደርዕይ ላይ ዛሬ አርብ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ስድሰት ኪሎ በሚገኘው በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ ሙዚየም ውስጥ ውይይት ይካሄዳል። በዕለቱም መምህር በቀለ መኮንን፣ሐሌታ ይረጋ ፣ ነፃነት ገብረሚካኤል ሀሳቦቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
ይህ የሠዓሊ ዳዊት ገረሡ "አሁን" የተሰኘ የሥዕል አውድርዕይ ከግንቦት 23 እስከ ሰኔ 14 2016 ዓ.ም በእይታ ላይ ቆይቷል።
ሠዓሊ ዳዊት ገረሱ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥነጥበባትና ዲዛይን ት/ቤት በ1993 ዓ.ም አግኝቷል። በርካታ የሥዕል አውደርዕዮችን በግልና በቡድን በተለያዩ ጋለሪዎች አሳይቷል::
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በሠዓሊ ዳዊት ገረሱ "አሁን " በተሰኘው የሥዕል አውደርዕይ ላይ ዛሬ አርብ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ስድሰት ኪሎ በሚገኘው በገብረክርስቶስ ደስታ ዘመናዊ ሙዚየም ውስጥ ውይይት ይካሄዳል። በዕለቱም መምህር በቀለ መኮንን፣ሐሌታ ይረጋ ፣ ነፃነት ገብረሚካኤል ሀሳቦቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።
ይህ የሠዓሊ ዳዊት ገረሡ "አሁን" የተሰኘ የሥዕል አውድርዕይ ከግንቦት 23 እስከ ሰኔ 14 2016 ዓ.ም በእይታ ላይ ቆይቷል።
ሠዓሊ ዳዊት ገረሱ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥነጥበባትና ዲዛይን ት/ቤት በ1993 ዓ.ም አግኝቷል። በርካታ የሥዕል አውደርዕዮችን በግልና በቡድን በተለያዩ ጋለሪዎች አሳይቷል::
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የማስታወቂያ ምልክቶች ላይ ውይይት ተካሄደ
የአዲስ አበባ ከተማ ባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከዕይታዊ ጥበባት እና ከኪነ-ህንጻ ውበት አኳያ በከተማዋ እየተስተዋሉ ያሉ የማስታወቂያና የምልክት/ሳይንኤጅ/ አጠቃቀም ችግርን ለመቅረፍ ከዲዛይንና ግንባታ ፈቃድ ቢሮ፣ ከዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች ጋር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአለ የሥዕልና ዲዛይን ትምህርት ቤት ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ የሥዕልና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዳይሬክተር አቶ አገኘሁ አዳነና የዲዛይን ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ኦስማን ሃሰን መነሻ ሃሳብ ቀርቧል፡፡
እንደ አቶ አገኘሁ አዳነ የትኛውም የማስታወቂያ ቀለም ውህደት እና የአንድ ትርጉም አመላካች ጉዳይና ይዘት በሳይንሳዊ፣ በቀለማትና በተፈጥሮ ስሪት መልክ መሆን እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
አክለውም በከተሞች ላይ የሚታዩ የሳይንኤጅ አጠቃቀም ችግሮች የማስታወቂያ አጠቃቀም መመሪያ አለመኖር ዋነኛ ችግር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
📍መረጃው የአ/አ/ባ/ኪ/ቱ/ቢ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአዲስ አበባ ከተማ ባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከዕይታዊ ጥበባት እና ከኪነ-ህንጻ ውበት አኳያ በከተማዋ እየተስተዋሉ ያሉ የማስታወቂያና የምልክት/ሳይንኤጅ/ አጠቃቀም ችግርን ለመቅረፍ ከዲዛይንና ግንባታ ፈቃድ ቢሮ፣ ከዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች ጋር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአለ የሥዕልና ዲዛይን ትምህርት ቤት ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ የሥዕልና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዳይሬክተር አቶ አገኘሁ አዳነና የዲዛይን ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ኦስማን ሃሰን መነሻ ሃሳብ ቀርቧል፡፡
እንደ አቶ አገኘሁ አዳነ የትኛውም የማስታወቂያ ቀለም ውህደት እና የአንድ ትርጉም አመላካች ጉዳይና ይዘት በሳይንሳዊ፣ በቀለማትና በተፈጥሮ ስሪት መልክ መሆን እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
አክለውም በከተሞች ላይ የሚታዩ የሳይንኤጅ አጠቃቀም ችግሮች የማስታወቂያ አጠቃቀም መመሪያ አለመኖር ዋነኛ ችግር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
📍መረጃው የአ/አ/ባ/ኪ/ቱ/ቢ ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ አዲስ ቻናልና የ"አዲስ ታለንት ሾው"ውድድር ማስጀመር መርሐግብር ዛሬ ይካሄዳል
አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ አዲሱን የቋንቋዎች ቻናል (AMN PLUS) እንዲሁም “አዲስ ታለንት ሾው” የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ውድድር ማስጀመሪያ መርሀግብር በዛሬው ዕለት ይካሄዳል ተብሏል።
በዛሬው ዕለት በይፋ የሚጀምረው አዲሱ ቻናል (AMN PLUS) ተጨማሪ ቋንቋዎች ለተመልካች ተደራሽ የሚሆኑበት ነው።
በተጨማሪም ዛሬ በሚጀመረው በ"አዲስ ታለንት ሾው" በድራማዎች፣ ዳንስ፣ አጭር ፊልምና የህፃናት ታለንት ሾው ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው የአዲስ አበባ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ተወዳዳሪዎቹ በሰፈራቸው ስም ተወክለው በክፍለ ከተሞች መካከል ውድድር እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
በተጨማሪም ከእያንዳንዱ ክፍለ ከተማ 20 ተወዳዳሪዎች ይካተቱበታል ተብሏል።
አዲስ ታለንት ሾው የድሮ ሙዚቃና ድራማን በአዲስ መልክ ለውድድሩ እንደሚጠቀምም ተነግሯል።
በዓድዋ ድል መታሰቢያ በሚካሄደው ዝግጅት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የተቋሙ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ።
"የትውልድ ድምጽ" የሚል መሪ ቃል ያለው አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በአዲስ ቴሌቪዥን በሰባት ቋንቋዎች መረጃዎችን ለተመልካች እንደሚያቀርብ ይታወቃል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ አዲሱን የቋንቋዎች ቻናል (AMN PLUS) እንዲሁም “አዲስ ታለንት ሾው” የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ውድድር ማስጀመሪያ መርሀግብር በዛሬው ዕለት ይካሄዳል ተብሏል።
በዛሬው ዕለት በይፋ የሚጀምረው አዲሱ ቻናል (AMN PLUS) ተጨማሪ ቋንቋዎች ለተመልካች ተደራሽ የሚሆኑበት ነው።
በተጨማሪም ዛሬ በሚጀመረው በ"አዲስ ታለንት ሾው" በድራማዎች፣ ዳንስ፣ አጭር ፊልምና የህፃናት ታለንት ሾው ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው የአዲስ አበባ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ተወዳዳሪዎቹ በሰፈራቸው ስም ተወክለው በክፍለ ከተሞች መካከል ውድድር እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
በተጨማሪም ከእያንዳንዱ ክፍለ ከተማ 20 ተወዳዳሪዎች ይካተቱበታል ተብሏል።
አዲስ ታለንት ሾው የድሮ ሙዚቃና ድራማን በአዲስ መልክ ለውድድሩ እንደሚጠቀምም ተነግሯል።
በዓድዋ ድል መታሰቢያ በሚካሄደው ዝግጅት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የተቋሙ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ።
"የትውልድ ድምጽ" የሚል መሪ ቃል ያለው አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በአዲስ ቴሌቪዥን በሰባት ቋንቋዎች መረጃዎችን ለተመልካች እንደሚያቀርብ ይታወቃል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📍የቅዳሜ የሥነጽሑፍ ውይይቶች
1.የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም በ’ክለብ ሀውስ’ መተግበሪያ የመጻሕፍት ውይይት አራተኛ ዙር መርሐግብር ከደራሲያን እና ተጋባዥ እንግዶች ጋር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 11:30 ድረስ በአካል ውይይት ያካሂዳል።በዚህ የውይይት መርሐግብር ላይ "የሦስት ትውልዶች ወግ በመጻሕፍት፣ ንባብና ሌሎች ርዕስ ጉዳዮች"በሚል ርዕስ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ፣ ከዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ፣ ከደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ እና ከፕ/ር ጴጥሮስ ቶጃ ጋር ከእስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ፊትለፊት በሚገኘው ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
2.በዛጎል መጻሕፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጽሐፍ ውይይት ዛሬ ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት ከዶ/ር ስንታየሁ ካሣ እና ከደራሲ በሁሉም አለበል ጋር "ታሪክ የምትመሰክርልን ካሣ ገብረማርያም " እና "የተዳፈነዉ ታሪክ: ራስ ጉግሳ ወሌ" በተሰኙ መጻሕፍት ላይ ውይይት ይካሄዳል።የዕለቱ አወያይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው። ይህ መርሐግብር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 10:30 ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
1.የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም በ’ክለብ ሀውስ’ መተግበሪያ የመጻሕፍት ውይይት አራተኛ ዙር መርሐግብር ከደራሲያን እና ተጋባዥ እንግዶች ጋር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 11:30 ድረስ በአካል ውይይት ያካሂዳል።በዚህ የውይይት መርሐግብር ላይ "የሦስት ትውልዶች ወግ በመጻሕፍት፣ ንባብና ሌሎች ርዕስ ጉዳዮች"በሚል ርዕስ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ፣ ከዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ፣ ከደራሲ ይፍቱስራ ምትኩ እና ከፕ/ር ጴጥሮስ ቶጃ ጋር ከእስጢፋኖስ ቤተክርስትያን ፊትለፊት በሚገኘው ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ይካሄዳል ተብሏል።
2.በዛጎል መጻሕፍት ባንክ የሚዘጋጀው "ነገረ መጻሕፍት" የመጽሐፍ ውይይት ዛሬ ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ይካሄዳል። በዚህ ሳምንት ከዶ/ር ስንታየሁ ካሣ እና ከደራሲ በሁሉም አለበል ጋር "ታሪክ የምትመሰክርልን ካሣ ገብረማርያም " እና "የተዳፈነዉ ታሪክ: ራስ ጉግሳ ወሌ" በተሰኙ መጻሕፍት ላይ ውይይት ይካሄዳል።የዕለቱ አወያይ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው። ይህ መርሐግብር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 22 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 እስከ 10:30 ይካሄዳል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1