Event Addis Media – Telegram
Event Addis Media
9.62K subscribers
6.12K photos
14 videos
4 files
4.75K links
Connect with Addis artistic community!

Website: https://eventaddis.com

Contact: @Tmanaye
Download Telegram
📌የአእምሮ እድገት ውስንነት ቀንን (CP-day) አስመልክቶ የፊታችን መስከረም 26 የእግር ጉዞ መርሐ-ግብር መዘጋጀቱ ተገለፀ

ስለ ሲፒ ጉዳት ይመለከተኛል በሚል በዛሬው እለት በእዝነት አካል ጉዳተኛ ህጻናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት ውስጥ የግንዛቤ ማስጨበጥ መርሐ-ግብር የተካሄደ ሲሆን  ይህን አስመልክቶ የፊታችን መስከረም 26 የእግር ጉዞ መርሐ-ግብርም መዘጋጀቱ ተገልጿል።

ይህንንም የእግር ጉዞ ይፋ ለማድረግ እና የቲሸርት ምረቃ መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን 10000 የሚሆኑ ቲሸርቶች መዘጋጀታቸው ተገልጿል

ቲሸርቱ ከዛሬ ጀምሮ ለሽያጭ የቀረበ ሲሆን የአንዱ ቲሸርት ዋጋ 400 ብር ነው ትብሏል
የCP ጉዳተኛ ህፃናት ራሳቸውን ችለው መቀመጥ፥ መቆም፥ መመገብ፥ ንፅህናቸውን መጠበቅ፥ መናገር አንዳንዱም ማየት የማይችሉ፥ እዲሁም በየቀኑ በተደጋጋሚ seizure የሚከሰትባቸው ህፃናት ናቸው።

እዝነት እነዚህ ህፃናት እንደማንኛውም ዜጋ ማግኘት ያለባቸውን እንከብካቤ እያገኙ ጤንነታቸው እና ምቾታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ የሚጥር ማእከል እንደመሆኑ መጠን የCP ጉዳት ምንነትን አስመልክቶ የማሕበረሰቡ ግንዛቤ ከፍ እንዲል ለማድረግ የአይምሮ ውስንነት ቀንን (CP-day) ተንተርሶ ይህን የእግር ጉዞ መርሐ-ግብር ለማዘጋጀት መዘጋጀቱን የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዘቢባ አህመድ ገልጸዋል።

ወ/ሮ ዘቢባ አክለው እንደገለጹት ህብረተሰቡ በሐገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የአለም ሴሬብራል ፓልሲ ቀንን በማስመልከት በተዘጋጀው በዚህ የእግር ጉዞ መርሐግብር ላይ በመሳተፍ ለአካል ጉዳተኛ ህጻናት በተለይም ለሲፒ ጉዳተኛ ህጻናት አለኝታ በመሆን ከድርጅቱ ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮፕላስ የተሰኘ ስልክ ለተጠቃሚዎች ቀረበ

አምስተኛ ትውልድ(5ጂ) ኢንተርኔት ማስጠቀም ይችላል የተባለው አዲሱ የኢንፊኒክስ ምርት ለተጠቃሚዎች ነሐሴ 4 2016 ዓ.ም ይፋ ተደርጓል።

ኢንፊኒክስ ያስተዋወቀው አዲስ ስልክ “ኖት 40 ፕላስ” የሚባል ሲሆን፣ 5G ኔትዎርክን የሚያስጠቅም፤ 108 ሜጋ ፒክስል ጥራት ያለው ካሜራና 100 ዋት ፈጣን ቻርጀር፣ እንዲሁም 20 ዋት ያለገመድ ቻርጅ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ እንዳለው ተነግሯል።

በተጨማሪም፣ በጌመሮችና ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ስራዎችን  በስልካቸው በሚከውኑ ሰዎች ተመራጭ የሆነው ”ሜዲቴክ ዲመንሲቲ 7020” የተሰኘ ፕሮሰሰር የተገጠመለት “ፈጣን ስልክ ነው” ተብሏል።

እንደዚሁም 100 ዋት ፈጣን ቻርጀር እና 20 ዋት ያለገመድ ቻርጅ ማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ነውም ተብሏል።

የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ ስልክ የዘመኑ የመጨረሻ የኔትዎርክ ቴክኖሎጂ የሆነው 5G ማስጠቀም የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል።

በምርቱ ይፋ ማድርጊያ ዝግጅት የተለያዩ የመዝናኛ መርሃግብሮች ተካሂደዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ በተዘጋጁ ውድድሮችም አዲሱን የ”ኖት 40 ፕሮ ፕላስ” ስልክን ጨምሮ የተለያዩ ሽልማቶች ለተሳታፊዎች እንደተበረከቱ ለማወቅ ተችሏል።

ኢንፊኒክስ ቲቪ፣ ላፕቶፕ፣ ኤርፖድ፣ ብሉቱዝ ስፒከር፣ ስማርት ዋች እና አዲሱ “ኖት 40” ስልኮች ለዝግጅቱ ታዳሚ ለዕይታ ቀረበዋል።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ዛሬ በኢትዮጵያ ቡክ ፎረም

ዛሬ ነሐሴ 5 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 እስከ 4:00 በኢትዮጵያ ቡክ ፎረም መቼቱን በ1990ዎቹ መጀመሪያ በተካሄደው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ላይ በማድረግ ከጦርነቱ የተመለሰ ታዳጊን ሕይወት በቤተሰቡ እንዲሁም አጠቃላይ ማህበራዊ ሕይወቱ በኩል ሀገራዊ ሁነትን በሚዳስሰው የይፍቱሥራ ምትኩ ሁለተኛ የልቦለድ ሥራ “ወድቆ የተገኘ ሐገር” ላይ የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም አሰናኞች እና ተሳታፊዎች ውይይት ያደርጋሉ። ።

የውይይቱ ሊንክ :
https://www.clubhouse.com/invite/aXOcqz2XL8Xa4gAjZloWJwwDBE4u2jvaKb:i17x1sSmUCL6GgF-BVAMSOBYYNniedPZSK-uPINmSsc

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ከበደች ትቀኛለች የግጥም ሠርክ"

በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት (ወመዘክር) ቅዳሜ ነሐሴ 11 2016 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ “ከበደች ትቀኛለች” በሚል ርዕስ ገጣሚ፣ ቀራጺ እና ሠዓሊ ከበደች ተክለአብ ስራዎቿን የምታቀርብበት የግጥም ሠርክ ዝግጀት ይካሄዳል፡፡

ሁላችሁም በአክብሮት ተጋብዛችኋል!

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ከቡሉምበርግ ሚዲያ ኢኒሼቲቭ አፍሪካ ጋር በመተባበር የፋይናሻል ጋዜጠኝነት ስልጠና ሊሰጡ ነው፡፡

ስልጠናውን በተመለከተ የፕሮግራም ትውውቅ በዛሬው ዕለት የተካሔደ ሲሆን፤ ስልጠናው በዩኒቨርሲቲዎቹ የጋዜጠኝነት ተማሪዎች እንዲሁም በሥራ ላይ ላሉ ጋዜጠኞች የፋይናሻል ዘገባ ግንዛቤያቸውን የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ የካፒታል ገበያ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የሚያደርገው ስልጠናው፤ ፍላጎት ላላቸው ጋዜጠኞች ለተከታታይ ስድስት ወራት እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ወንደወሰን ሙሉጌታ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው በተለይ ወቅቱ የሚጠይቀውን የፋይናንሻል ጋዜጠኝነት ዕውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው የዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አረጋ ይርዳው (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

የፋይናሻል ጋዜጠኝነት ቁጥራዊ መረጃን በትክክል መርምሮ ከመዘገብ ባለፈ የኢኮኖሚ መረጃን በግልጽ ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል፡፡

📍መረጃው ኢፕድ ነው

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በፊልም ባለሞያዋ ቅድስት ይልማ ወላጅ አባት የተጻፈው "ሱራ" የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ሐሙስ ይመረቃል።

በፊልም ባለሞያዋ ቅድስት ይልማ ወላጅ አባት አቶ ይልማ እሸቴ የተጻፈው "ሱራ" የተሰኘ መጽሐፍ የፊታችን ሐሙስ ነሐሴ 9 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት እንደሚመረቅ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በመጽሐፍ ምርቃቱ ላይ መምህርና ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣ አርቲስት አዜብ ወርቁ ፣አርቲስት ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ገጣሚ ይታገሱ ጌትነት፣ ጋዜጠኛ ቢኒያም ከበደ፣ሀያሲ ቴዎድሮስ አጥላውና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ቡሄ ፌስት" ቅዳሜ ይካሄዳል

"ቡሄ ፌስት'' የተሰኘ የቡሄ የፌስቲቫል ዝግጅት የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 11 2016 ዓ.ም በጉለሌ እፅዋት ማዕከል ውስጥ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያደረሱት መረጃ ያመለክታል።                                  
  
ፕሮግራሙ ከቀኑ 7:00 ጀምሮ የሚካሄደው ሲሆን የመግቢያ ዋጋው 1000 ብር ነው ተብሏል።

መርሐግብሩ ሙልሙል መጋገር ፣የቡሄ ጭፈራ፣እራት እና ቁርስ፣ መግቢያ ትኬት ፣አስጎብኚ፣ ፎቶና ሌሎችም ፓኬጆችን ይዟል።

በእነዚህ ማህበራዊ ድረገጾች ይከታተሉን ቤተሰብም ይሁኑን:
Telegram, Instagram, Tiktok, LinkedIn, Facebook

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በመጽሐፍ ላይ በተጣለው ተጨማሪ እሴት ታክስ ላይ የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር  ቅሬታውን አሰማ

መንግስት ከሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል ባደረገው አዋጅ በመፅሐፍ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ የጣለ ሲሆን ይህም የንባብ ባህልን በከፍተኛ ሁኔታ የሚጎዳ እንደሆነ ማህበሩ አመላክቷል።

በዚህ አዋጅ ውስጥ ቀደም ሲል በነበረው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ነፃ ተደርገው የነበሩትን በማካተት የተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲከፈልባቸው አዋጁ የደነገገ ሲሆን ከእነዚህም አንዱ መጻሕፍት መሆናቸውም ተገቢነት የለውም ብሏል።

አዋጁ በሀገሪቱ ያለውን የማንበብ ባህል ካለበት ደረጃ አኳያ ይበልጥ የሚጎዳ ሲሆን የኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ላይም ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያደርስ ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር መፅሐፍ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ መጣሉ የመፅሐፍ ዋጋ እንዲንር የሚያደርግ ብሎም በትውልድ የአዕምሮ ልማት ላይ እጅግ ከባድ ጉዳት የሚያደርስ ነው ሲል ገልጿል።

ይህንን አስመልክቶም ማህበሩ ዛሬ ነሐሴ 8 2016 ዓ.ም  ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው እና ያገባናል ከሚሉ አካላት ጋር በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ውይይት አካሄዷል።

መረጃው የአረዳ ኤፍ ኤም 95.1 ነው።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌አላቲኖስ የፊልም ውይይት ዛሬ ይካሄዳል

አላቲኖስ ኢትዮጵያዊ ፊልም ሰሪዎች ማሕበር ፒያሳ በሚገኘው የሩሲያ ሳይንስና ባህል ማዕከል (ፑሽኪን) አዳራሽ ውስጥ በሚያዘጋጀው የፊልም ውይይት መርሐግብር ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ጀምሮ" Understanding Abbas kiarostaml"በሚል ርዕስ ውይይት ይካሄዳል።በዕለቱም መነሻ ሀሳብ በአብኔዘር ሰኔ  ይቀርባል ተብሏል።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ሱራ" መጽሐፍ ዛሬ ይመረቃል

በደራሲ ይልማ እሸቴ የተጻፈው "ሱራ" የተሰኘ መጽሐፍ ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ 9 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 11:00 ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ውስጥ ይመረቃል።

በመጽሐፍ ምርቃቱ ላይ መምህርና ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣ አርቲስት አዜብ ወርቁ ፣አርቲስት ድርብወርቅ ሰይፉ ፣ገጣሚ ይታገሱ ጌትነት፣ ጋዜጠኛ ቢኒያም ከበደ፣ሀያሲ ቴዎድሮስ አጥላውና ሌሎችም ሀሳቦቻቸውን ያጋራሉ ተብሏል። አቶ ይልማ እሸቴ የፊልም ባለሞያዋ ቅድስት ይልማ ወላጅ አባት ናቸው።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
Event Addis Media
Photo
📌 “ሲቢኢ ብር ኤክስፖ 2017" አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት የእንቁጣጣሽ ኤግዚቢሽንና ባዛር ቀጣይ ሳምንት ይከፈታል።

ታሜሶል ኮሙኒኬሽን እና ሊየን ቢዝነስ ግሩፕ ከአሴነቲክ ሶሉሽን ጋር በመተባበር  ያዘጋጁት የእንቁጣጣሽ ዋዜማ ኤግዚቢሽንና ባዛር በሚቀጥለው ሳምንት ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ይከፈታል።

"ሲቢኢ ብር ኤክስT 2017" በሚል ስያሜ የተሰየመው እና ከነሐሴ 15 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ሞ ለተከታታይ 21 ቀናት በሚቆየው ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በዓይነቱ ልዩ የሆነና ደረጃውን የጠበቀ ብሎም ለሻጭ፣ ለጎብኚና ለሸማች ምቹ እንዲሆን ከስነ-ውበታዊ ጉዳዮች ጀምሮ የተለያዩ ሥራዎችን በመስራት ሲዘጋጅ መቆየቱን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።

በዚህ ኤክስፖ ላይ ከአስር በላይ መንደሮች የተዘጋጁ ሲሆን ከሸመታና ከጉብኝት በተጨማሪ በየቀኑ ከ35 በላይ ተወዳጅ ደሞጻዊያን የሚያቀነቅኑበት ልዩ የሙዚቃና የመዝናኛ ፌስቲቫልም ተዘጋጅቷል።

እስከ እንቁጣጣሽ ዋዜማ ድረስ በተከታታይ በሚከናወነው ፌስቲቫል ላይ የመድረክ የሙዚቃ ክዋኒያቸውን ከሚያቀርቡ ድምጻዊያን መካከል  አብርሃም ገብረ መድህን፣ መሰሉ ፈንታሁን ፣ ዳዊት ፅጌ ፣ አንዱዓለም ጎሣ፣ ኃይለየሱስ ግርማ፣ ጌቴ አንለይ፣ ሃይማኖት ግርማ፣ ተአምር ግዛው ፣አምሳል ምትኬና ሌሎችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።

በኤክስፖ መክፈቻ እና መዝጊያ ላይ ከሚኖረው የሙዚቃ ዝግጅት በተጨማሪ ቅዳሜ ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ድምጻዊ አብርሃም ገብረ መድህንን ጨምሮ እውቅ ድምጻዊያን በታዋቂ ባንድ በመታጀብ የሚያቀነቅነበትን ልዩ ኮንሰርትን ተዘጋጅቷል።

ከአራት መቶ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ድርጀቶች የሚሳተፋበት “ሲቢኢ ብር ኤክስፖ 2017" ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይጎበኘዋል ተበሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለጎቢኚዎች ወደ ኤግዚቢሽን ማዕከል በሲቢኢ ብር በኩል በቆረጡት የ100 ብር ትኬት አማካኝነት የሚያገኙትን የዕጣ ቁጥር በመጠቀም እንደ እድላቸው ሀያ የ5 ሺህ ፣አምስት የ10ሺ፣ ሶስት የ50ሺ፣ ሁለት የ100 ሺ ብር ዋጋ ያላቸውን ኩፖኖችን በማሸነፍ ከእግዚቢሽኑ የፈለጉትን ዕቃ መሸመት የሚችሉበት የዕጣ ጨዋታ ተዘጋጅቷል።

ከኩፖኖቹ በተጨማሪ አንድ የኤሌክትሪክ ባይክ እና 2.3 ሚሊዮን ብር ዋጋ የሚያወጣ ቢዋይዲ አዲስ የቤት አውቶሞቢል መኪና ለባለዕድለኞች በሽልማትነት መቅረቡን ተገልጿል።

ለተጨማሪው:@EventAddis1
📌ሁለት አልበሞች በተመሳሳይ ቀን

የሚካኤል በላይነህ እና የቬሮኒካ አዳነ የሙዚቃ አልበሞች በተመሳሳይ ቀን ለአድማጮች ይደርሳል ተብሏል ።

የድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ "አንድ ቃል"  እና የድምጻዊት ቬሮኒካ አዳነ"መጠሪያዬ" የተሰኘ ርዕስ የተሰጣቸው ሁለት የሙዚቃ አልበሞች በሚቀጥለው ሳምንት ነሐሴ 17 2016 ዓ.ም እንደሚለቀቁ ኤቨንት አዲስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በእረፍት ቀንዎ ፊልም ይመልከቱ !

እነዚህ ሶስት የፊልም ማሳያዎች(ሲኒማ ቤቶች) ዛሬን ጨምሮ በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት እነዚህን ፊልሞች ለተመልካቾች ያቀርባሉ: ምስሎቹን ይመልከቱ።

የሲኒማ ቤቶቹ አድራሻ:

✔️ለም ሆቴል አካባቢ: ቫምዳስ ሲኒማ

✔️ጉርድ ሾላ አካባቢ : ሴንቸሪ ሲኒማ

✔️ቦሌ አካባቢ : ዓለም ሲኒማ

መልካም የእረፍት ቀናት ይሁንላችሁ !

https://news.1rj.ru/str/EventAddis1

https://news.1rj.ru/str/EventAddis1

ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በእረፍት ቀንዎ ቴአትር ይመለከቱ !

አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር  እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።

📍 የፍቅር ካቴና

ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ

📍 "እሳት ወይ አበባ"

ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር

📍 ባሎች እና ሚስቶች

ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር

📍 ባቡሩ

ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር

📍 ሸምጋይ

ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር

📍 እምዩ ብረቷ

ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር

የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በታይም መጽሔት ‘የዓመቱ ታዳጊ ሳይንቲስት"

ትውልደ ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ተመራማሪ ሄማን በቀለ በታይም መጽሔት ‘የዓመቱ ታዳጊ ሳይንቲስት’ ተብሎ ተሰየመ

የቆዳ ካንሰርን ማከምና መከላከል የሚችል ሳሙና ለመስራት ምርምር በማድረግ ላይ የሚገኘው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሄማን በቀለ በታይም መጽሔት የዓመቱ የላቀ ተጽዕኖ ፈጣሪ ታዳጊ ተብሎ ተሰየመ።

ሄማን ባለፈው ጥቅምት ወር ከምርምር ስራው ጋር በተያያዘ በተካሄደ የወጣት ሳይንቲስቶች ውድድር ላይ ተሳትፎ 25ሺ ዶላር መሸለሙን መዘገባችን ይታወሳል።

የ15 ዓመቱ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ታዳጊ ሄማን በቀለ በአሜሪካ ቨርጂኒያ የሚኖር ሲሆን፣ የ10ኛ ክፍል ተማሪ ነው።

የአራት ዓመት ልጅ እያለ ከወላጆቹ ጋር ወደ አሜሪካ ያቀናው ሄማን ለስኬቱ በመምህርነት ሙያ ላይ የተሰማሩት እናቱና በዓለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ የሚሰሩት አባቱ ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ለመጽሔቱ ተናግሯል።

ሄማን ከመጽሄቱ ጋር በነበረው ቆይታ ብዙ ሰዎች ሁሉም ነገር ተፈጥሮ እንዳለቀ አድርጎ የማሰብ አዝማሚያ እንደሚያሳዩ ገልጾ፣ እነዚህን ሰዎች ሲመክርም ‘ሀሳብ አያልቅም፤ በፈጠራ ላይ እንበርታ፤ ዓለማችንን የተሻለች ለማድረግ እንጣር’ ብሏል።

ሄማን ከሰባት ዓመቱ ጀምሮ በሚያካሂደው የምርምር ስራና ለጉዳዩ ባለው ከፍተኛ ፍላጎት በተማረኩት ተባባሪ ፕሮፌሰርና ሞለኪዩላር ባዮሎጂስት በሆኑት ቪቶ ሬቤካ ድጋፍና ክትትል ባልቲሞር በሚገኘው ጆን ሆፕኪንስ የማህበረሰብ ጤና  ላብራቶሪ ውስጥ የምርምር ስራውን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝም መጽሔቱ ዘግቧል።

ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1