📌"ንግስት" የነፍስጡሮች የፋሽን ሾው ሊካሄድ ነው
ታዋቂ ኤቨንትስ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው "ንግስት" የተሰኘ የነፍስጡሮች የፋሽን ሾው ውድድር በአዲሱ ዓመት መስከረም 11 2017 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በዚህ የነፍስጡሮች ፋሽን ውድድር ለመውለድ የተዘጋጁ ነፍሰ ጡሮች በዲዛይነሮች በተዘጋጁ ቅንጡ አልባሳት የተዘጋጁላቸውን ልብሶች በመጠቀም ተውበው የሚታዩበት ነው ተብሏል።
በውድድሩ ላይ ነፍሰጡር ተወዳዳሪዎች ምቾትን ተጎናጽፈው እራሳቸውን የሚገልጹበት፣ ለተለያዩ ስሜቶች ተጋላጭ የሆነውን ይህንን የእርግዝና ጊዜ በተዝናኖት የሚያሳልፉበት፣ ብሎም ከትዳር አጋራቸው ጋር በሚጠየቁት የእርግዝና ነክ ጥያቄዎቸ አማካኝነት እየተዳኙ ተወዳድረው ሽልማቶችን የሚያገኙበት እንደሆነም ተነግሯል።
የፕሮግራሙ ዓላማ የውድድሩ አላማ በኢትዮጵያ በስፋት እየተስተዋለ ስለሚገኘው የእናቶችን በእርግዝና እና በወሊድ ወቅት ህይወት ማለፍን አስመልክቶ ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑ ተገልጿል።
ነፍሰ ጡርነት ውበት መሆኑን ለሌሎች በማስገንዘብ እና የጤና ክትትል የማያደርጉ ነፍሰ ጡር እናቶችን ክትትላቸውን እንዲያደርጉ መንገድን የሚያመላክት መሆኑም ተመላክቷል።
በሀገራችን በዓመት በአማካይ እስከ አስር ሺህ እናቶች በወሊድ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡ ተገልጿል።
በዚህ ፋሽን ሾው ላይ ጤነኛ እና ፍቃደኛ የሆኑ ማንኛውም እናቶች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ታዋቂ ኤቨንትስ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው "ንግስት" የተሰኘ የነፍስጡሮች የፋሽን ሾው ውድድር በአዲሱ ዓመት መስከረም 11 2017 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በዚህ የነፍስጡሮች ፋሽን ውድድር ለመውለድ የተዘጋጁ ነፍሰ ጡሮች በዲዛይነሮች በተዘጋጁ ቅንጡ አልባሳት የተዘጋጁላቸውን ልብሶች በመጠቀም ተውበው የሚታዩበት ነው ተብሏል።
በውድድሩ ላይ ነፍሰጡር ተወዳዳሪዎች ምቾትን ተጎናጽፈው እራሳቸውን የሚገልጹበት፣ ለተለያዩ ስሜቶች ተጋላጭ የሆነውን ይህንን የእርግዝና ጊዜ በተዝናኖት የሚያሳልፉበት፣ ብሎም ከትዳር አጋራቸው ጋር በሚጠየቁት የእርግዝና ነክ ጥያቄዎቸ አማካኝነት እየተዳኙ ተወዳድረው ሽልማቶችን የሚያገኙበት እንደሆነም ተነግሯል።
የፕሮግራሙ ዓላማ የውድድሩ አላማ በኢትዮጵያ በስፋት እየተስተዋለ ስለሚገኘው የእናቶችን በእርግዝና እና በወሊድ ወቅት ህይወት ማለፍን አስመልክቶ ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑ ተገልጿል።
ነፍሰ ጡርነት ውበት መሆኑን ለሌሎች በማስገንዘብ እና የጤና ክትትል የማያደርጉ ነፍሰ ጡር እናቶችን ክትትላቸውን እንዲያደርጉ መንገድን የሚያመላክት መሆኑም ተመላክቷል።
በሀገራችን በዓመት በአማካይ እስከ አስር ሺህ እናቶች በወሊድ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡ ተገልጿል።
በዚህ ፋሽን ሾው ላይ ጤነኛ እና ፍቃደኛ የሆኑ ማንኛውም እናቶች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌መብራት በመጥፋቱ ቴአትር ሳይቀረብ ቀረ!
በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የቴአትር ቤት ዛሬ ነሐሴ 16 2016 ዓ.ም መብራት በመጥፋቱ ምክንያት ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ይቀርብ የነበረው "ጎዶን ጥበቃ" የተሰኘው ተውኔት ሳይቀርብ እንደቀረ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የ"ጎዶን ጥበቃ " ተውኔት አዘጋጅ የሆነው ዳግም ሲሳይ በማህበራዊ ትስስር ገፁ " ዛሬ ትርኢት ባለመኖሩ ይቅርታ እንጠይቃለን።ምክንያቱ ምን ይሆን ቢሉ "መብራት የለም" ነው" ብሏል።
አሁን ላይ እንደ ሀገር አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ብቸኛው የቴአትር አግልግሎት ሰጪ "የቴአትር ቤት" እንደሆነ ይታወቃል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በአንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የቴአትር ቤት ዛሬ ነሐሴ 16 2016 ዓ.ም መብራት በመጥፋቱ ምክንያት ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ይቀርብ የነበረው "ጎዶን ጥበቃ" የተሰኘው ተውኔት ሳይቀርብ እንደቀረ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የ"ጎዶን ጥበቃ " ተውኔት አዘጋጅ የሆነው ዳግም ሲሳይ በማህበራዊ ትስስር ገፁ " ዛሬ ትርኢት ባለመኖሩ ይቅርታ እንጠይቃለን።ምክንያቱ ምን ይሆን ቢሉ "መብራት የለም" ነው" ብሏል።
አሁን ላይ እንደ ሀገር አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት ብቸኛው የቴአትር አግልግሎት ሰጪ "የቴአትር ቤት" እንደሆነ ይታወቃል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"አባስሽው" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ተለቀቀ
የድምጻዊ ሻሎም ደሳለኝ "አባስሽው" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ዛሬ አመሻሹን በምነው ሸዋ ኢንተርቴይመንት ዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቋል።
የሙዚቃው ግጥምና ዜማ በሻሎም ደሳለኝ የተሰራ ሲሆን አሬንጅመንት ሚክሲንጉን ላይ መኳንንት አዲሱ ተሳትፏል።የሙዚቃው ቪዲዮው በአምሃ ዱግማ ዳይሬክት ተደርጓል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ ሻሎም ደሳለኝ "አባስሽው" የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃ ዛሬ አመሻሹን በምነው ሸዋ ኢንተርቴይመንት ዩቲዩብ ቻናል በኩል ተለቋል።
የሙዚቃው ግጥምና ዜማ በሻሎም ደሳለኝ የተሰራ ሲሆን አሬንጅመንት ሚክሲንጉን ላይ መኳንንት አዲሱ ተሳትፏል።የሙዚቃው ቪዲዮው በአምሃ ዱግማ ዳይሬክት ተደርጓል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌"ሲቢኢ ብር ኤክስፖ 2017" ተከፈተ!
ታሜሶል ኮሙኒኬሽን እና ሊየን ቢዝነስ ግሩፕ ከአሴነቲክ ሶሉሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "ሲቢኢ ብር ኤክስፖ 2017" ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፍቷል።
በመክፈቻው ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሃብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች ተመርቆ ተጀምሯል፡፡
"ሲቢኢ ብር ኤክስT 2017" ኤግዚቢሽን እና ባዛር ከዛሬ ነሐሴ 16 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ሞ ለተከታታይ 21 ቀናት ይቆያል።
በዚህ ኤክስፖ ላይ ከአስር በላይ መንደሮች የተዘጋጁ ሲሆን ከሸመታና ከጉብኝት በተጨማሪ በየቀኑ ከ35 በላይ ተወዳጅ ደሞጻዊያን የሚያቀነቅኑበት ልዩ የሙዚቃና የመዝናኛ ፌስቲቫልም ተዘጋጅቷል።
እስከ እንቁጣጣሽ ዋዜማ ድረስ በተከታታይ በሚከናወነው ፌስቲቫል ላይ የመድረክ የሙዚቃ ክዋኒያቸውን ከሚያቀርቡ ድምጻዊያን መካከል አብርሃም ገብረ መድህን፣ መሰሉ ፈንታሁን ፣ ዳዊት ፅጌ ፣ አንዱዓለም ጎሣ፣ ኃይለየሱስ ግርማ፣ ጌቴ አንለይ፣ ሃይማኖት ግርማ፣ ተአምር ግዛው ፣አምሳል ምትኬና ሌሎችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።
በኤክስፖ መክፈቻ እና መዝጊያ ላይ ከሚኖረው የሙዚቃ ዝግጅት በተጨማሪ ከነገ ስቲያ ቅዳሜ ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ድምጻዊ አብርሃም ገብረ መድህንን ጨምሮ እውቅ ድምጻዊያን በታዋቂ ባንድ በመታጀብ የሚያቀነቅነበትን ልዩ ኮንሰርት ተዘጋጅቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ታሜሶል ኮሙኒኬሽን እና ሊየን ቢዝነስ ግሩፕ ከአሴነቲክ ሶሉሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "ሲቢኢ ብር ኤክስፖ 2017" ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፍቷል።
በመክፈቻው ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሃብቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች ተመርቆ ተጀምሯል፡፡
"ሲቢኢ ብር ኤክስT 2017" ኤግዚቢሽን እና ባዛር ከዛሬ ነሐሴ 16 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ሞ ለተከታታይ 21 ቀናት ይቆያል።
በዚህ ኤክስፖ ላይ ከአስር በላይ መንደሮች የተዘጋጁ ሲሆን ከሸመታና ከጉብኝት በተጨማሪ በየቀኑ ከ35 በላይ ተወዳጅ ደሞጻዊያን የሚያቀነቅኑበት ልዩ የሙዚቃና የመዝናኛ ፌስቲቫልም ተዘጋጅቷል።
እስከ እንቁጣጣሽ ዋዜማ ድረስ በተከታታይ በሚከናወነው ፌስቲቫል ላይ የመድረክ የሙዚቃ ክዋኒያቸውን ከሚያቀርቡ ድምጻዊያን መካከል አብርሃም ገብረ መድህን፣ መሰሉ ፈንታሁን ፣ ዳዊት ፅጌ ፣ አንዱዓለም ጎሣ፣ ኃይለየሱስ ግርማ፣ ጌቴ አንለይ፣ ሃይማኖት ግርማ፣ ተአምር ግዛው ፣አምሳል ምትኬና ሌሎችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።
በኤክስፖ መክፈቻ እና መዝጊያ ላይ ከሚኖረው የሙዚቃ ዝግጅት በተጨማሪ ከነገ ስቲያ ቅዳሜ ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ድምጻዊ አብርሃም ገብረ መድህንን ጨምሮ እውቅ ድምጻዊያን በታዋቂ ባንድ በመታጀብ የሚያቀነቅነበትን ልዩ ኮንሰርት ተዘጋጅቷል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሙዚቀኞች ጥሪ አቀረበ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሙዚቃ ስራዎቻቸውን አየር መንገዱ በሚያቀርበው የአውሮፕላን ውስጥ የመዝናኛ ቻናሎች ምርጫ ውስጥ እንዲካተትላችሁ ለሙዚቀኞች ጥሪውን አቅርቧል።
አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገፆቹ "ክቡራን መንገደኞቹ አዝናኝ የበረራ ቆይታ ይኖራቸው ዘንድ የተለያዩ የመዝናኛ አማራጮችን የሚያቀርበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የሙዚቃ ስራዎች 140 ወደሚጠጉ ዓለም-አቀፍ መዳረሻዎቹ ለሚጓዙ መንገደኞቹ ተደራሽ የሚሆኑበትን አማራጭ ይዞ ብቅ ብሏል።
በመሆኑም የሙዚቃ ስራዎቻችሁ አየር መንገዱ በሚያቀርበው የአውሮፕላን ውስጥ የመዝናኛ ቻናሎች ምርጫ ውስጥ እንዲካተትላችሁ የምትፈልጉ የጥበብ ባለሙያዎች በሙሉ ደረጃቸውን እና ጥራታቸውን የጠበቁ ሙዚቃዎቻችሁን ይዛችሁ በመቅረብ የዕድሉ ተሳታፊ እንድትሆኑ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ለተጨማሪ መረጃ እና ቀጠሮ ለማስያዝ በስልክ ቁጥሮቻችን 0115178079 እና 0115178097 ይደውሉ። አሊያም በኢሜል አድራሻዎቻችን HiwotGe@ethiopianairlines.com ወይም
HilinaBel@ethiopianairlines.com ይፃፉልን " ብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሙዚቃ ስራዎቻቸውን አየር መንገዱ በሚያቀርበው የአውሮፕላን ውስጥ የመዝናኛ ቻናሎች ምርጫ ውስጥ እንዲካተትላችሁ ለሙዚቀኞች ጥሪውን አቅርቧል።
አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገፆቹ "ክቡራን መንገደኞቹ አዝናኝ የበረራ ቆይታ ይኖራቸው ዘንድ የተለያዩ የመዝናኛ አማራጮችን የሚያቀርበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የተዘጋጁ የሙዚቃ ስራዎች 140 ወደሚጠጉ ዓለም-አቀፍ መዳረሻዎቹ ለሚጓዙ መንገደኞቹ ተደራሽ የሚሆኑበትን አማራጭ ይዞ ብቅ ብሏል።
በመሆኑም የሙዚቃ ስራዎቻችሁ አየር መንገዱ በሚያቀርበው የአውሮፕላን ውስጥ የመዝናኛ ቻናሎች ምርጫ ውስጥ እንዲካተትላችሁ የምትፈልጉ የጥበብ ባለሙያዎች በሙሉ ደረጃቸውን እና ጥራታቸውን የጠበቁ ሙዚቃዎቻችሁን ይዛችሁ በመቅረብ የዕድሉ ተሳታፊ እንድትሆኑ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ለተጨማሪ መረጃ እና ቀጠሮ ለማስያዝ በስልክ ቁጥሮቻችን 0115178079 እና 0115178097 ይደውሉ። አሊያም በኢሜል አድራሻዎቻችን HiwotGe@ethiopianairlines.com ወይም
HilinaBel@ethiopianairlines.com ይፃፉልን " ብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ከ31 ዓመታት በኃላ ለንባብ የሚበቃው መጽሐፍ
የረ/ፕ ሙሉጌታ ጀዋሬ "ወጀብ" የተሰኘ ልቦለድ መጽሐፍ ከሰላሳ አንድ ዓመታት በኃላ ከነገ ስቲያ ለንባብ ሊበቃ እንደሆነ ኤቨንት ድረገፅ ሰምቷል።
በ1980ዎቹ አጋማሽ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የነበረውን የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሰረት አድርጎ የተፃፈው መፅሀፉ የሕትመት ሂደቱን አጠናቆ የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እሁድ ነሐሴ 19 ቀን 2016ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል ተብሏል።
"ወጀብ" የተሰኘው ቀዳሚው መፅሀፍ የመጀመሪያው ቅፅ ሲሆን ሁለተኛው የመፅሀፉ ቅፅ የአንባቢያኑን ግብረ መልስ ጠብቆ ለንባብ እንዲበቃ ይደጋል ተብሏል።
"ወጀብ" መጽሐፍ በ399 ገፆች የተቀነበበው በ550 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ይቀርባል።
ድርሰቱ የተመሠረተበት እውነተኛ ታሪክ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተከሰተበት ወቅት የነበረውን የተማሪዎች አካዳሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ የሕይወት እውነታዎችን በተራቀቀ አቀራረብ እንዲሁም በግልጽ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡
በዋናነትም በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች እንቅስቃሴ ሂደት ውስጥ እምብዛም ትኩረት ያልተሰጠውን የ1980ዎቹን ጉልህ የታሪክ ክፍተት እንደሚሞላም ተጠቁሟል።
በመፀሀፉ ውስጥ ያለውን ታሪክ መነሻ ያደረገ አዲስ ሙዚቃም መሰናዳቱ የተገለፀ ሲሆን በግጥም ሙሉጌታ ጀዋሬ እንዲሁም በዜማ አለማየሁ ደመቀ እንደተሳተፉበትና የፊታችን እሁድ ከመጽሐፉ ምርቃት ጎን ለጎን ሙዚቃው እንደሚለቀቅ ተገልጿል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የረ/ፕ ሙሉጌታ ጀዋሬ "ወጀብ" የተሰኘ ልቦለድ መጽሐፍ ከሰላሳ አንድ ዓመታት በኃላ ከነገ ስቲያ ለንባብ ሊበቃ እንደሆነ ኤቨንት ድረገፅ ሰምቷል።
በ1980ዎቹ አጋማሽ በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የነበረውን የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሰረት አድርጎ የተፃፈው መፅሀፉ የሕትመት ሂደቱን አጠናቆ የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እሁድ ነሐሴ 19 ቀን 2016ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል ተብሏል።
"ወጀብ" የተሰኘው ቀዳሚው መፅሀፍ የመጀመሪያው ቅፅ ሲሆን ሁለተኛው የመፅሀፉ ቅፅ የአንባቢያኑን ግብረ መልስ ጠብቆ ለንባብ እንዲበቃ ይደጋል ተብሏል።
"ወጀብ" መጽሐፍ በ399 ገፆች የተቀነበበው በ550 ብር የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን ይቀርባል።
ድርሰቱ የተመሠረተበት እውነተኛ ታሪክ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተከሰተበት ወቅት የነበረውን የተማሪዎች አካዳሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ የሕይወት እውነታዎችን በተራቀቀ አቀራረብ እንዲሁም በግልጽ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡
በዋናነትም በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች እንቅስቃሴ ሂደት ውስጥ እምብዛም ትኩረት ያልተሰጠውን የ1980ዎቹን ጉልህ የታሪክ ክፍተት እንደሚሞላም ተጠቁሟል።
በመፀሀፉ ውስጥ ያለውን ታሪክ መነሻ ያደረገ አዲስ ሙዚቃም መሰናዳቱ የተገለፀ ሲሆን በግጥም ሙሉጌታ ጀዋሬ እንዲሁም በዜማ አለማየሁ ደመቀ እንደተሳተፉበትና የፊታችን እሁድ ከመጽሐፉ ምርቃት ጎን ለጎን ሙዚቃው እንደሚለቀቅ ተገልጿል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌“መንግስቱ ኃ/ማርያም: የሥደተኛው መሪ ትረካዎች” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ነገ ለንባብ ይበቃል
በደራሲ ይታገሱ ጌትነት የተዘጋጀው "መንግስቱ ኃ/ማርያም:የሥደተኛው መሪ ትረካዎች" የተሰኘ መጽሐፍ ነገ ነሐሴ 18 2016 ዓ.ም ለአንባቢያን እንደሚቀርብ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
መጽሐፉ የቀድሞው የኢትዮጵያን ፕሬዝዳንት ኮ/ል መንግሥቱ ኃ/ማርያም ከልጅነት አንስቶ ዛሬ እስካሉበት የስደት ዘመን ድረስ የተጓዙባቸውን ግላዊ ታሪኮች፣ የሕይወት ገጠመኞች እና ወቅታዊና ነባር ፖለቲካዊ ግምገማዎችን አካትቶ ይዟል፡፡
የዚህ መጽሐፍ ዐቢይ ትኩረቱም እንደሰው የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያምን ማንነነት መመልከትና ያልተደመጠውን ድምጽ መሥማት ነው ተብሏል።
የመጽሐፉ ጸሐፊ ይታገሱ ጌትነት"በሕይወቴ ፈጸምኳቸው ከምላቸው በርካታ ቁም ነገሮች ውስጥ ምናልባት ይኽኛው ዐብዩ ይሆናል ብዬ አምናለሁ"በማለት ተናግሯል።
በተጨማሪም"በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉ ቁምነገሮች ለታሪክ አጥኚዎች ግብአት፣ ለከያንያን የመነሻ ሀሳብ፣ ለፖለቲከኞች ትምህርት፣ ለጋዜጠኞች መረጃ፣ ለወጣቶች የሕይወት ልምድን፣ ለሌችም እንደሙያቸውና ማንነታቸው የሚወስዱት ቁምነገር አያጡበትም" ብሏል።
የመጽሐፉ አሳታሚና አከፋፋይ ዋሊያ መጽሐፍ መደብር ሲሆን ከነገ ጀምሮ በበርካታ መጻሕፍት መደብሮች ልታገኙ ትችላላችሁ ተብላችኋል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በደራሲ ይታገሱ ጌትነት የተዘጋጀው "መንግስቱ ኃ/ማርያም:የሥደተኛው መሪ ትረካዎች" የተሰኘ መጽሐፍ ነገ ነሐሴ 18 2016 ዓ.ም ለአንባቢያን እንደሚቀርብ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
መጽሐፉ የቀድሞው የኢትዮጵያን ፕሬዝዳንት ኮ/ል መንግሥቱ ኃ/ማርያም ከልጅነት አንስቶ ዛሬ እስካሉበት የስደት ዘመን ድረስ የተጓዙባቸውን ግላዊ ታሪኮች፣ የሕይወት ገጠመኞች እና ወቅታዊና ነባር ፖለቲካዊ ግምገማዎችን አካትቶ ይዟል፡፡
የዚህ መጽሐፍ ዐቢይ ትኩረቱም እንደሰው የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያምን ማንነነት መመልከትና ያልተደመጠውን ድምጽ መሥማት ነው ተብሏል።
የመጽሐፉ ጸሐፊ ይታገሱ ጌትነት"በሕይወቴ ፈጸምኳቸው ከምላቸው በርካታ ቁም ነገሮች ውስጥ ምናልባት ይኽኛው ዐብዩ ይሆናል ብዬ አምናለሁ"በማለት ተናግሯል።
በተጨማሪም"በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉ ቁምነገሮች ለታሪክ አጥኚዎች ግብአት፣ ለከያንያን የመነሻ ሀሳብ፣ ለፖለቲከኞች ትምህርት፣ ለጋዜጠኞች መረጃ፣ ለወጣቶች የሕይወት ልምድን፣ ለሌችም እንደሙያቸውና ማንነታቸው የሚወስዱት ቁምነገር አያጡበትም" ብሏል።
የመጽሐፉ አሳታሚና አከፋፋይ ዋሊያ መጽሐፍ መደብር ሲሆን ከነገ ጀምሮ በበርካታ መጻሕፍት መደብሮች ልታገኙ ትችላላችሁ ተብላችኋል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌በእረፍት ቀንዎ ቴአትር ይመለከቱ !
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 የፍቅር ካቴና
ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍 "እሳት ወይ አበባ"
ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና የቦሌው ዓለም ሲኒማ አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እነዚህን ተውኔቶች ለታዳሚያን ያቀርባሉ።
📍 የፍቅር ካቴና
ድርሰትና ዝግጅት: አለልኝ መኳንት ፅጌ
ቀን: አርብ
ሰዓት: 12:00
ቦታ: ዓለም ሲኒማ
📍 "እሳት ወይ አበባ"
ድርሰት: ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እንደጻፈው
ዳንስና ዳንስ ቅንብር: ሽፈራው ታሪኩ ቢረጋ
ቀን: አርብ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባሎች እና ሚስቶች
ድርሰት: ውዱ አለን
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ባቡሩ
ድርሰት: አርኖልድ ሪድሊ
አዘጋጅ:ራሔል ተሾመ መሐመድ
ቀን: ቅዳሜ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 ሸምጋይ
ድርሰት:ታደለ አያሌው
አዘጋጅ: ሳሙኤል ተስፋዬ
ቀን: እሁድ
ሰዓት: 8:00
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
📍 እምዩ ብረቷ
ድርሰት: ቤልቶልት ብሬሽት
አዘጋጅ: ማንያዘዋል እንዳሻው
ቀን: እሁድ
ሰዓት:11:30
ቦታ: ብሔራዊ ቴአትር
የእናንተው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ መልካም የእረፍት ቀን ይሁንላችሁ ይላል !
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የድምጻዊ መሳይ ተፈራ የሙዚቃ አልበም ምርቃት !
የድምጻዊ መሳይ ተፈራ ካሣ "የልቤን" የሙዚቃ አልበም የምርቃት ሥነሥርዓት በርካታ ዝነኛ ሙዚቀኞች በተገኙበት ዛሬ አመሻሹን በማርዮት ሆቴል ውስጥ እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ መሳይ ተፈራ ካሣ "የልቤን" የሙዚቃ አልበም የምርቃት ሥነሥርዓት በርካታ ዝነኛ ሙዚቀኞች በተገኙበት ዛሬ አመሻሹን በማርዮት ሆቴል ውስጥ እንደሚካሄድ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የጁፒተር ብራና ንባብ ቡድን ውይይት
ዛሬ በጁፒተር ብራና የንባብ ቡድን "በትውልዶች መካከል የሚደረግ ወግ " በሚል አብይ ርዕስ ውይይት ይካሄዳል። የዕለቱም እንግዳ የህግ ባለሙያ ታምራት ኪዳነማርያም ናቸው።
ቀን፡ ቅዳሜ ነሀሴ 18 ፣ 2016
ሰዓት፡ ከቀኑ 9፡45 – 12፡00
ቦታ፡ ጁፒተር ሆቴል ካዛንቺስ ቅርንጫፍ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ዛሬ በጁፒተር ብራና የንባብ ቡድን "በትውልዶች መካከል የሚደረግ ወግ " በሚል አብይ ርዕስ ውይይት ይካሄዳል። የዕለቱም እንግዳ የህግ ባለሙያ ታምራት ኪዳነማርያም ናቸው።
ቀን፡ ቅዳሜ ነሀሴ 18 ፣ 2016
ሰዓት፡ ከቀኑ 9፡45 – 12፡00
ቦታ፡ ጁፒተር ሆቴል ካዛንቺስ ቅርንጫፍ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ ተማሪዎቹን አስመረቀ !
ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ ዛሬ ነሐሴ 18 2016 ዓ.ም በተለያየ የሙያ ዘርፍ ያስተማራቸውን ተማሪዎችን በአምባሳደር ቴአትር ቤት አስመርቋል።
በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ በመሆን የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ማዕከል ስራ አስፈጻሚ ሃሰን ሁሴን (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም የኮሌጁ ዲን ቴዎድሮስ አበበ (ረዳት ፕሮፌሰር) እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የኮሎጁ ዲን ቴዎድሮስ አበበ (ረዳት ፕሮፌሰር) የ"እንኳን ደስ ያላችሁ" መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ "ኮሌጃችን በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ በዲግሪ መርሃ ግብር ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመርቋል" ብለዋል። አያይዘውም ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ የመክፈል አቅም ለሌላቸው ዜጎች ነጻ የትምሕርት ዕድል እየሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በኮሮና ቫይረስ ወቅት ትምሕርት ላይ የነበሩ፣ በኋላም በሌሎች ተጽዕኖዎች መሃል ሆነው ለተማሩ ተማሪዎች ምስጋናቸውን አቅረበዋል።
በመጀመሪያ ዲግሪ፤ አካውንቲንግና ፋይናንስ፣ ማኔጅመንት፣ በማስተርስ፤ ቢዝነስ ማኔጅመንትና ሂዩማን ሪሶርስ ማኔጅመንት፣ እንዲሁም በደረጃ 4 በሰባት የቴክኒክ እና ሞያ ስልጠና ዘርፎች 850 ተማሪዎች የተመረቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 54 በመቶ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
በዛሬ በተካሄደው የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዋንጫ እና የሜዳልያ ሽልማት ከኮሌጁ ዲን እና ከዕለቱ የክብር ዕንግዳ ተበርክቷል።
ኮሌጁ በማኔጅመንት 418 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 315ቱ ሴቶች፣203ቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው።
በማስተርስ ደረጃ በኤክስቴንሽንና በመደበኛ ትምህርት ወንድ 109 ሴት 82 ተማሪዎችን አጠቃላይ 191 ተማሪዎች ማስመረቁን ተቋሙ ገልጿል።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ ዛሬ ነሐሴ 18 2016 ዓ.ም በተለያየ የሙያ ዘርፍ ያስተማራቸውን ተማሪዎችን በአምባሳደር ቴአትር ቤት አስመርቋል።
በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ የክብር እንግዳ በመሆን የኢንተርፕረነርሺፕ ልማት ማዕከል ስራ አስፈጻሚ ሃሰን ሁሴን (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም የኮሌጁ ዲን ቴዎድሮስ አበበ (ረዳት ፕሮፌሰር) እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የኮሎጁ ዲን ቴዎድሮስ አበበ (ረዳት ፕሮፌሰር) የ"እንኳን ደስ ያላችሁ" መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ "ኮሌጃችን በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ በዲግሪ መርሃ ግብር ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመርቋል" ብለዋል። አያይዘውም ሲልከን ቫሊ ኮሌጅ የመክፈል አቅም ለሌላቸው ዜጎች ነጻ የትምሕርት ዕድል እየሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በኮሮና ቫይረስ ወቅት ትምሕርት ላይ የነበሩ፣ በኋላም በሌሎች ተጽዕኖዎች መሃል ሆነው ለተማሩ ተማሪዎች ምስጋናቸውን አቅረበዋል።
በመጀመሪያ ዲግሪ፤ አካውንቲንግና ፋይናንስ፣ ማኔጅመንት፣ በማስተርስ፤ ቢዝነስ ማኔጅመንትና ሂዩማን ሪሶርስ ማኔጅመንት፣ እንዲሁም በደረጃ 4 በሰባት የቴክኒክ እና ሞያ ስልጠና ዘርፎች 850 ተማሪዎች የተመረቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 54 በመቶ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
በዛሬ በተካሄደው የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዋንጫ እና የሜዳልያ ሽልማት ከኮሌጁ ዲን እና ከዕለቱ የክብር ዕንግዳ ተበርክቷል።
ኮሌጁ በማኔጅመንት 418 ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 315ቱ ሴቶች፣203ቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው።
በማስተርስ ደረጃ በኤክስቴንሽንና በመደበኛ ትምህርት ወንድ 109 ሴት 82 ተማሪዎችን አጠቃላይ 191 ተማሪዎች ማስመረቁን ተቋሙ ገልጿል።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌 ደራሲው የላዳ ሹፌር ነገ መጽሐፉን ያስመርቃል!
ጌታቸው ከበደ ይባላል። የላድ ታክሲ ሹፌር ነው። ከስራውም ጎን ለጎን በሥነጽሑፉም ላይ ተሳትፎ ያደርጋል።
ለረጅም ጊዜያት ሲጽፍው የቆየው የልቦለድ መጽሐፉ ቀኑ ደርሶለት ለህትመት ብርሃን በቅቷል።መጽሐፉንም ነገ እንደሚያስመርቅ ኤቨንት አዲስ ድረገጽ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የጌታቸው ከበደ አዲስ መጽሐፍ "የወርቅ መርዝ" የተሰኘ ርዕስ ያለው ሲሆን በዘውግ ደረጃ ረጅም ልቦለድ ነው።
በ236 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ በ413 ብር ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።በውስጡም 18 ምዕራፎችን ይዟል።
"የወርቅ መርዝ" ነገ ነሐሴ 19 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር ) አዳራሽ ውስጥ በድምቀት ይመረቃል።
በዚህ የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣አርቲስት ሽፈራው ታሪኩ፣ገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ እና ሌሎችም ይገኛሉ ተብሏል።
ደራሲው ስለመጽሐፉ ርዕስ በመግቢያው የሚከተለውን ብሏል" ይህ መጽሐፍ "የወርቅ መርዝ" ተብሎ ሲሰየም በወርቅ የተመሰለው ፍቅር ሲሆን በመርዝ የተመሰለው ደግሞ ፍቅርን ተከትለው የመጡትን አሉታዊ ተፅእኖዎች ነው"።
የሥነጽሑፍ ቤተሰብ የሆነ ሁሉ በነገው የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ እንዲገኙለት ጥሪውን አስተላልፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ጌታቸው ከበደ ይባላል። የላድ ታክሲ ሹፌር ነው። ከስራውም ጎን ለጎን በሥነጽሑፉም ላይ ተሳትፎ ያደርጋል።
ለረጅም ጊዜያት ሲጽፍው የቆየው የልቦለድ መጽሐፉ ቀኑ ደርሶለት ለህትመት ብርሃን በቅቷል።መጽሐፉንም ነገ እንደሚያስመርቅ ኤቨንት አዲስ ድረገጽ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የጌታቸው ከበደ አዲስ መጽሐፍ "የወርቅ መርዝ" የተሰኘ ርዕስ ያለው ሲሆን በዘውግ ደረጃ ረጅም ልቦለድ ነው።
በ236 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ በ413 ብር ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።በውስጡም 18 ምዕራፎችን ይዟል።
"የወርቅ መርዝ" ነገ ነሐሴ 19 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር ) አዳራሽ ውስጥ በድምቀት ይመረቃል።
በዚህ የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ ጸሐፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣አርቲስት ሽፈራው ታሪኩ፣ገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ እና ሌሎችም ይገኛሉ ተብሏል።
ደራሲው ስለመጽሐፉ ርዕስ በመግቢያው የሚከተለውን ብሏል" ይህ መጽሐፍ "የወርቅ መርዝ" ተብሎ ሲሰየም በወርቅ የተመሰለው ፍቅር ሲሆን በመርዝ የተመሰለው ደግሞ ፍቅርን ተከትለው የመጡትን አሉታዊ ተፅእኖዎች ነው"።
የሥነጽሑፍ ቤተሰብ የሆነ ሁሉ በነገው የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ እንዲገኙለት ጥሪውን አስተላልፏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የወጣቷ ድምጻዊት ሔለን አበራ የሙዚቃ ድግስ!
ወጣቷ ድምጻዊት ሔለን አበራ በመድረክ ላይ በቀጥታ የሙዚቃ ስራዎቿን የምታቀርብበት የሙዚቃ ድግስ ነገ ነሐሴ 19 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ሳር ቤት አካባቢ በሚገኘው ተምሳሌት ኪቺን ውስጥ ይካሄዳል።
በዚህ የሙዚቃ ዝግጅት ልዩ ልዩ የሙዚቃ ስራዎችን እንደምታቀርብ ድምጻዊት አስታውቃለች።
ድምጻዊት ሔልን አበራ በአዲሱ ዓመት የጃዝ ጣዕም ያለው የሙዚቃ አልበሟን ለአድማጮች እንደምታደርስ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ የተናገረች ሲሆን ነገ የሚካሄደው የሙዚቃ ዝግጅትም የአልበሟ መደረሻ እንደሆነ ገልጻለች።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ወጣቷ ድምጻዊት ሔለን አበራ በመድረክ ላይ በቀጥታ የሙዚቃ ስራዎቿን የምታቀርብበት የሙዚቃ ድግስ ነገ ነሐሴ 19 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ሳር ቤት አካባቢ በሚገኘው ተምሳሌት ኪቺን ውስጥ ይካሄዳል።
በዚህ የሙዚቃ ዝግጅት ልዩ ልዩ የሙዚቃ ስራዎችን እንደምታቀርብ ድምጻዊት አስታውቃለች።
ድምጻዊት ሔልን አበራ በአዲሱ ዓመት የጃዝ ጣዕም ያለው የሙዚቃ አልበሟን ለአድማጮች እንደምታደርስ ለኤቨንት አዲስ ድረገፅ የተናገረች ሲሆን ነገ የሚካሄደው የሙዚቃ ዝግጅትም የአልበሟ መደረሻ እንደሆነ ገልጻለች።
https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የባቡጂ የቀብር ሥነሥርዓት
አርቲስት ጌታቸው እጅጉ (ባቡጂ) ከትላንትና በስቲያ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ባቡጂ ሼፉ 2፣ ወደ ልጅነት፣ ጀማሪ ሌባ፣ እድሜ ለሴት የተሰኙና ሌሎች ከ60 በላይ ፊልሞች ላይ በመተወን በሙያው የራሱን አስተዋፅዖ ያበረክተው አርቲስት ጌታቸው እጅጉ (ባቡጂ) ነሐሴ 18 2016 ዓ.ም በመኖሪያ ቤት ሕይወቱ ማለፉ ይታወሳል።
የአርቲስት ጌታቸው እጅጉ(ባቡጂ) የቀብር ሥነሥርዓት
ዛሬ ነሐሴ 20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ላይ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት ይፈፀማል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት ጌታቸው እጅጉ (ባቡጂ) ከትላንትና በስቲያ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ባቡጂ ሼፉ 2፣ ወደ ልጅነት፣ ጀማሪ ሌባ፣ እድሜ ለሴት የተሰኙና ሌሎች ከ60 በላይ ፊልሞች ላይ በመተወን በሙያው የራሱን አስተዋፅዖ ያበረክተው አርቲስት ጌታቸው እጅጉ (ባቡጂ) ነሐሴ 18 2016 ዓ.ም በመኖሪያ ቤት ሕይወቱ ማለፉ ይታወሳል።
የአርቲስት ጌታቸው እጅጉ(ባቡጂ) የቀብር ሥነሥርዓት
ዛሬ ነሐሴ 20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ላይ በቅዱስ ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት ይፈፀማል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
Event Addis Media
Photo
📌አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ አረፈ
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ማረፉን ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከጋዜጠኛ ግርማ ፍስሃ ያገኘው መረጀ ያመለክታል።
ስለ አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ከተወዳጅ ሚዲያ ያገኘው የሚከተለውን ይመስላል።
"አርቲስት ኩራባቸው የ1979 ከአዲስ አበባ የቴአትር አርትስ ዲፓርትመንት የተመረቀ ሲሆን ባለፉት 35 አመታት ከትወና እስከ ዝግጅት ሙያዊ አደራውን በሚገባ የተወጣ ሰው ነው፡፡
ኩራባቸው በተለይ በአርትስ ቲቪ በተሰራው "እረኛዬ" በተባለው የቲቪ ተከታታይ ድራማ ድንቅ የትወና ብቃቱን አሳይቷል፡፡
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ የተወለደው በ1957 ዓ.ም በሐረር ከተማ ልዩ ስሙ ሸንኮር በሚባለው መንደር ውስጥ ነው።
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ በትወና በመድረክ ቴአትሮች ላይ ከ1982 ዓ ም ጀምሮ ከተሳተፈባቸው በጥቂቱ በህፃናትና ወጣቶች ቴአትር 'የዝናቧ እመቤት ' እና 'የገንፎ ተራራ' ቴአትሮች ፤ በሀገር ፍቅር ቴአትር 'የጨረቃ ቤት' ፣ 'ዓይነ ሞራ' ፣ 'ንጉሥ ሊር' ፣ 'ፍሬህይወት' ፣ 'ጥሎሽ' ፣ 'አሉ' ፣ 'ጣውንቶቹ' ፣ 'ከራስ በላይ ራስ' እና 'የሸክላ ጌጥ' ቴአትሮች ፤ በቴአትርና ባህል አዳራሽ 'የጫጉላ ሽርሽር' ቴአትር ፤ በራስ ቴአትር 'ቅርጫው' ቴአትር ይገኙበታል።
ከዳይሬክቲንግ ሥራዎቹ ካዘጋጃቸው የመድረክ ቴአትሮች በሀገር ፍቅር ቴአትር 'ስጦታ'፣'ጥሎሽ'እና 'መዳኛ' ቴአትሮች ፤ በቴአትርና ባህል አዳራሽ 'ሶስና'፣'አንድ ክረምት'፣ጥቁሩ መናኝ' እና የጫጉላ ሽርሽር'(ዝግጅት በተዋንያን ነበር) ቴአትሮች ፤ በራስ ቴአትር 'ትንታግ' የተሰኘ ቴአትር በማዘጋጀት ተሳትፏል።
ካዘጋጃቸው ሙዚቃዊ ድራማዎች መካከል በተለይ በአንጋፋዋ አርቲስት አስናቀች ወርቁ ህይወት ላይ ተመስርቶ የተፃፈውና ያዘጋጀው 'አስናቀች ኢትዮጵያ' የተሰኘው ሥራ ስራ ይጠቀሳል።
'የተዋቡ እጆች'የተሰኘ ፊልም አዘጋጅቷል።
በበርካታ የሬድዮ ድራማዎች ላይ በተለይም ደራሲ ሀይሉ ፀጋዬ በፃፋቸውና በቅዳሜ መዝናኛ ፕሮግራም በተላለፉት በአብዛኞቹ ተሳትፏል።
ለሁለት ለሁለት ሳምንታት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀረቡ 'ጩኒና ቾምቤ'የተሰኘ የህፃናት ቴአትር እና 'የማለዳ ጤዛ' የተሰኘው ድራማ ይገኙበታል።
የቴሌቪዥን ድራማዎች 'ገመና 1' እና 'ገመና 2' እና "እረኛዬ" ድራማዎች ብዙ አድናቂዎች ያፈሩለት ስራዎች ናቸው።
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ከወ/ሮ አስቴር ታደሰ ጋር በ1985 ዓ. ም በጋብቻ ተሳስሮ ሁለት ወንዶች እና አንዲት ሴት ልጆች አፍርቷል።
@EventAddis1
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ማረፉን ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ከጋዜጠኛ ግርማ ፍስሃ ያገኘው መረጀ ያመለክታል።
ስለ አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ከተወዳጅ ሚዲያ ያገኘው የሚከተለውን ይመስላል።
"አርቲስት ኩራባቸው የ1979 ከአዲስ አበባ የቴአትር አርትስ ዲፓርትመንት የተመረቀ ሲሆን ባለፉት 35 አመታት ከትወና እስከ ዝግጅት ሙያዊ አደራውን በሚገባ የተወጣ ሰው ነው፡፡
ኩራባቸው በተለይ በአርትስ ቲቪ በተሰራው "እረኛዬ" በተባለው የቲቪ ተከታታይ ድራማ ድንቅ የትወና ብቃቱን አሳይቷል፡፡
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ የተወለደው በ1957 ዓ.ም በሐረር ከተማ ልዩ ስሙ ሸንኮር በሚባለው መንደር ውስጥ ነው።
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ በትወና በመድረክ ቴአትሮች ላይ ከ1982 ዓ ም ጀምሮ ከተሳተፈባቸው በጥቂቱ በህፃናትና ወጣቶች ቴአትር 'የዝናቧ እመቤት ' እና 'የገንፎ ተራራ' ቴአትሮች ፤ በሀገር ፍቅር ቴአትር 'የጨረቃ ቤት' ፣ 'ዓይነ ሞራ' ፣ 'ንጉሥ ሊር' ፣ 'ፍሬህይወት' ፣ 'ጥሎሽ' ፣ 'አሉ' ፣ 'ጣውንቶቹ' ፣ 'ከራስ በላይ ራስ' እና 'የሸክላ ጌጥ' ቴአትሮች ፤ በቴአትርና ባህል አዳራሽ 'የጫጉላ ሽርሽር' ቴአትር ፤ በራስ ቴአትር 'ቅርጫው' ቴአትር ይገኙበታል።
ከዳይሬክቲንግ ሥራዎቹ ካዘጋጃቸው የመድረክ ቴአትሮች በሀገር ፍቅር ቴአትር 'ስጦታ'፣'ጥሎሽ'እና 'መዳኛ' ቴአትሮች ፤ በቴአትርና ባህል አዳራሽ 'ሶስና'፣'አንድ ክረምት'፣ጥቁሩ መናኝ' እና የጫጉላ ሽርሽር'(ዝግጅት በተዋንያን ነበር) ቴአትሮች ፤ በራስ ቴአትር 'ትንታግ' የተሰኘ ቴአትር በማዘጋጀት ተሳትፏል።
ካዘጋጃቸው ሙዚቃዊ ድራማዎች መካከል በተለይ በአንጋፋዋ አርቲስት አስናቀች ወርቁ ህይወት ላይ ተመስርቶ የተፃፈውና ያዘጋጀው 'አስናቀች ኢትዮጵያ' የተሰኘው ሥራ ስራ ይጠቀሳል።
'የተዋቡ እጆች'የተሰኘ ፊልም አዘጋጅቷል።
በበርካታ የሬድዮ ድራማዎች ላይ በተለይም ደራሲ ሀይሉ ፀጋዬ በፃፋቸውና በቅዳሜ መዝናኛ ፕሮግራም በተላለፉት በአብዛኞቹ ተሳትፏል።
ለሁለት ለሁለት ሳምንታት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀረቡ 'ጩኒና ቾምቤ'የተሰኘ የህፃናት ቴአትር እና 'የማለዳ ጤዛ' የተሰኘው ድራማ ይገኙበታል።
የቴሌቪዥን ድራማዎች 'ገመና 1' እና 'ገመና 2' እና "እረኛዬ" ድራማዎች ብዙ አድናቂዎች ያፈሩለት ስራዎች ናቸው።
አርቲስት ኩራባቸው ደነቀ ከወ/ሮ አስቴር ታደሰ ጋር በ1985 ዓ. ም በጋብቻ ተሳስሮ ሁለት ወንዶች እና አንዲት ሴት ልጆች አፍርቷል።
@EventAddis1
📌የአርቲስት ኩራባቸው ደነቀ የቀብር ሥነሥርዓት
የአርቲስት ኩራባቸው ደነቀ የቀብር ሥነሥርዓት ነገ ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ከቀኑ 5:00 እስከ 6:00 ይፈፀማል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአርቲስት ኩራባቸው ደነቀ የቀብር ሥነሥርዓት ነገ ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም በቀጨኔ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ከቀኑ 5:00 እስከ 6:00 ይፈፀማል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ካናል-ፕላስ የኢትዮጵያን ገበያ ለቆ ሊወጣ ነው
የፈረንሳዩ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናል ካናል ፕላስ (Canal +) የኢትዮጵያ ገበያን ለቆ ሊወጣ መሆኑን መሠረት ሚድያ ዘግቧል።
ከሶስት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ቻናሉ ለበርካታ ተጠቃሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም በበቂ ሁኔታ ገበያውን ተቀላቅሎ ትርፍ ማግኘት ስላልቻለ ውሳኔው ላይ እንደደረሰ ታውቋል።የስፖርት ቻናሉ ከተቋረጠ በርካታ ግዜም ተቆጥሯል።
"የስፖርት ቻናሉ መቋረጥን ተከትሎ ሌሎቹ ቻናሎች በቅርብ ሳምንታት ይቋረጣሉ። ይህም ማለት ኤጀንት ከነበረው ብሩህ Plc ጋር ያለውን ስራውን ያቆማል" ብሎ አንድ ጉዳዩን የሚያውቅ ምንጭ መረጃ ሰጥቷል።
አክሎም "ዋናው እና ግልፁ ምክንያት ገበያውን በደንብ ሰብሮ መግባት አለመቻሉ ነው" ብሏል።
ካናል ፕላስ የኢትዮጵያ ስራውን የጀመረው ከኢዩቴልሳት ጋር ስምምነት ተፈራርሞ የነበረ ሲሆን ስርጭቶቹንም በኢዩቴልሳት 7ሲ ቻናሎች ላይ ሲያስተላልፍ ቆይቷል።
ካናል ፕላስ በኢትዮጵያ ከስታር ታይምስ እና ዲ ኤስ ቲቪ ቀጥሎ ሶስተኛው የሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናል መሆን ችሎ ነበር።
📍መረጃው የመሰረት ሚዲያ ነው።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የፈረንሳዩ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናል ካናል ፕላስ (Canal +) የኢትዮጵያ ገበያን ለቆ ሊወጣ መሆኑን መሠረት ሚድያ ዘግቧል።
ከሶስት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ቻናሉ ለበርካታ ተጠቃሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም በበቂ ሁኔታ ገበያውን ተቀላቅሎ ትርፍ ማግኘት ስላልቻለ ውሳኔው ላይ እንደደረሰ ታውቋል።የስፖርት ቻናሉ ከተቋረጠ በርካታ ግዜም ተቆጥሯል።
"የስፖርት ቻናሉ መቋረጥን ተከትሎ ሌሎቹ ቻናሎች በቅርብ ሳምንታት ይቋረጣሉ። ይህም ማለት ኤጀንት ከነበረው ብሩህ Plc ጋር ያለውን ስራውን ያቆማል" ብሎ አንድ ጉዳዩን የሚያውቅ ምንጭ መረጃ ሰጥቷል።
አክሎም "ዋናው እና ግልፁ ምክንያት ገበያውን በደንብ ሰብሮ መግባት አለመቻሉ ነው" ብሏል።
ካናል ፕላስ የኢትዮጵያ ስራውን የጀመረው ከኢዩቴልሳት ጋር ስምምነት ተፈራርሞ የነበረ ሲሆን ስርጭቶቹንም በኢዩቴልሳት 7ሲ ቻናሎች ላይ ሲያስተላልፍ ቆይቷል።
ካናል ፕላስ በኢትዮጵያ ከስታር ታይምስ እና ዲ ኤስ ቲቪ ቀጥሎ ሶስተኛው የሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናል መሆን ችሎ ነበር።
📍መረጃው የመሰረት ሚዲያ ነው።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌የአንደኛው "ሚዲያ አዋርድ" ተሸላሚዎች !
አንደኛው "የሚዲያ አዋርድ" የሽልማት ሥነሥርዓት ዛሬ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ካዛንቺስ በሚገኘው በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ተከናውኗል።
በዚህ መሰረት የተሸላሚዎች ዝርዝርም ታውቋል።
በምርጥ የቴሌቪዥን መዝናኛ ፕሮግራም ሴት አቅራቢ: አስካለ ተስፋዬ
በምርጥ ዜና ዘጋቢ ዘርፍ: ግርማ ፍሰሃ
ምርጥ የስፖርት ጋዜጠኛ: መንሱር አብዱልቀኒ
በምርጥ ዶክመንተሪ አዘጋጅ: አክሊሉ ሲራጅ
በምርጥ የሬድዮ ሴት ዜና አንባቢ: ለምለም ዮሐንስ
በምርጥ የሬድዮ ወንድ ዜና አንባቢ: ሶዶ ለማ
በምርጥ የቴሌቪዥን ሴት የዜና አንባቢ: የሸዋ ማስረሻ
በምርጥ የቴሌቪዥን ወንድ የዜና አንባቢ: ሠለሞን ኃይለኢየሱስ
በምርጥ የቴሌቪዥን መዝናኛ ፕሮግራም ወንድ አቅራቢ :ሀብተማርያም መንግስቴ
በምርጥ የአምድ ፀሃፊ:አክሲያ ኢታሎ
በምርጥ የምርመራ ዘገባ: ክብረት ካህሳይ
በምርጥ ዲጄ : ዲጄ ኪንግስተን (ወዝወዝ አዲስ)
ልዩ ተሸላሚ: የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ ዳኜ አበራ
ምርጥ የትምህርት ፕሮግራም: የእርቅ ማዕድ የሬድዮ ፕሮግራም
ምርጥ የሬድዮ ፕሮግራም: ታዲያስ አዲስ
በህዝብ ድምፅ ብቻ የተመረጠ የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ: አንዋር ጀማል
የህይወት ዘመን ተሸላሚ: መዓዛ ብሩ
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አንደኛው "የሚዲያ አዋርድ" የሽልማት ሥነሥርዓት ዛሬ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ካዛንቺስ በሚገኘው በኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ተከናውኗል።
በዚህ መሰረት የተሸላሚዎች ዝርዝርም ታውቋል።
በምርጥ የቴሌቪዥን መዝናኛ ፕሮግራም ሴት አቅራቢ: አስካለ ተስፋዬ
በምርጥ ዜና ዘጋቢ ዘርፍ: ግርማ ፍሰሃ
ምርጥ የስፖርት ጋዜጠኛ: መንሱር አብዱልቀኒ
በምርጥ ዶክመንተሪ አዘጋጅ: አክሊሉ ሲራጅ
በምርጥ የሬድዮ ሴት ዜና አንባቢ: ለምለም ዮሐንስ
በምርጥ የሬድዮ ወንድ ዜና አንባቢ: ሶዶ ለማ
በምርጥ የቴሌቪዥን ሴት የዜና አንባቢ: የሸዋ ማስረሻ
በምርጥ የቴሌቪዥን ወንድ የዜና አንባቢ: ሠለሞን ኃይለኢየሱስ
በምርጥ የቴሌቪዥን መዝናኛ ፕሮግራም ወንድ አቅራቢ :ሀብተማርያም መንግስቴ
በምርጥ የአምድ ፀሃፊ:አክሲያ ኢታሎ
በምርጥ የምርመራ ዘገባ: ክብረት ካህሳይ
በምርጥ ዲጄ : ዲጄ ኪንግስተን (ወዝወዝ አዲስ)
ልዩ ተሸላሚ: የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ ዳኜ አበራ
ምርጥ የትምህርት ፕሮግራም: የእርቅ ማዕድ የሬድዮ ፕሮግራም
ምርጥ የሬድዮ ፕሮግራም: ታዲያስ አዲስ
በህዝብ ድምፅ ብቻ የተመረጠ የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ: አንዋር ጀማል
የህይወት ዘመን ተሸላሚ: መዓዛ ብሩ
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ሶስተኛው የሺህ ጋብቻ ካርኒቫል ኤክስፖ
ያሜንት ኤቨንትስ ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የሚዘጋጀው የየሺህ ጋብቻ 2017 መርሐግብር ለሶስተኛ ጊዜ ይካሄዳል ተብሏል።
ይህንም አስመልክቶ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ያሜንት ኤቨንትስ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት አድርጓል።
በ2017 የሺህ ጋብቻ ካርኒቫል ኤክስፖ ላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጋብቻቸውን የሚፈፅሙ ጥንዶች የሚሳተፍበት መሆኑ ለየት ያደርገዋል ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ያሜንት ኤቨንትስ ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የሚዘጋጀው የየሺህ ጋብቻ 2017 መርሐግብር ለሶስተኛ ጊዜ ይካሄዳል ተብሏል።
ይህንም አስመልክቶ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ያሜንት ኤቨንትስ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት አድርጓል።
በ2017 የሺህ ጋብቻ ካርኒቫል ኤክስፖ ላይ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጋብቻቸውን የሚፈፅሙ ጥንዶች የሚሳተፍበት መሆኑ ለየት ያደርገዋል ተብሏል።
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
📌ተዋናይት ፍናን ህድሩ እና ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ
ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ ተዋናይት ፍናን ህድሩን የብራንድ አምባሳደር በማድረግ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ዛሬ ነሐሴ 23 2016 ዓ.ም በሐያት ሪንጀሲ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የአንድ ዓመት ቆይታ አለው የተባለ ሲሆን ኢንፊንክስ ኢትዮጵያ ተዋናይት ፍናን ከብራንዱ ጋር በቅርበት በመስራት በተለይም ወጣቱን ከብራንዱ ጋር በማስተዋወቅ የራሷን ድርሻ ትወጣለች ብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል።
ተዋናይት ፍናን በፊልሙ ኢንደስትሪ በተለይም በወጣቱ ዘንድ ያገኘችውን ተቀባይነት እና ያላት የፈጠራ ችሎታ ከኢንፊኒከስ ብራንድ ጋር አብሮ ለመስራት ምቹ እንደሚያደርገው የተገለፀ ሲሆን ኢንፊኒከስ ከሚታወቅበት የስልክ ገበያ በተጨማሪ ወደ ቲቪ፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ዋች፣ ኤር ፖድ እና መሰል ምርቶችን ወደ ገበያው ለማቅረብ ያለውን ዓላማ በመደገፍ ረገድ ጉልህ ተሳትፎ ይኖራታል ተብሏል።
ኢንፊኒከስ ዓለም አቀፍ የኤሌከትሮኒክስ አምራች ኩባንያ ሲሆን በተለይም በሚያመርታቸው የስማርት ስልኮች አለም አቀፍ ተቀባይነትን ያገኘ ብራንድ ነው::
በምርቶቹ አዳዲስ ቴከኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ የሚተወቀው ኢንፊኒከስ አሁን ደግሞ በቲቪ፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ዋች፣ ኤር ፖድ እና የመሳሰሉት ምርቶቹ ወደ ገበያው እየመጣ ይገኛል፡፡
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ ተዋናይት ፍናን ህድሩን የብራንድ አምባሳደር በማድረግ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ዛሬ ነሐሴ 23 2016 ዓ.ም በሐያት ሪንጀሲ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የአንድ ዓመት ቆይታ አለው የተባለ ሲሆን ኢንፊንክስ ኢትዮጵያ ተዋናይት ፍናን ከብራንዱ ጋር በቅርበት በመስራት በተለይም ወጣቱን ከብራንዱ ጋር በማስተዋወቅ የራሷን ድርሻ ትወጣለች ብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል።
ተዋናይት ፍናን በፊልሙ ኢንደስትሪ በተለይም በወጣቱ ዘንድ ያገኘችውን ተቀባይነት እና ያላት የፈጠራ ችሎታ ከኢንፊኒከስ ብራንድ ጋር አብሮ ለመስራት ምቹ እንደሚያደርገው የተገለፀ ሲሆን ኢንፊኒከስ ከሚታወቅበት የስልክ ገበያ በተጨማሪ ወደ ቲቪ፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ዋች፣ ኤር ፖድ እና መሰል ምርቶችን ወደ ገበያው ለማቅረብ ያለውን ዓላማ በመደገፍ ረገድ ጉልህ ተሳትፎ ይኖራታል ተብሏል።
ኢንፊኒከስ ዓለም አቀፍ የኤሌከትሮኒክስ አምራች ኩባንያ ሲሆን በተለይም በሚያመርታቸው የስማርት ስልኮች አለም አቀፍ ተቀባይነትን ያገኘ ብራንድ ነው::
በምርቶቹ አዳዲስ ቴከኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ የሚተወቀው ኢንፊኒከስ አሁን ደግሞ በቲቪ፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ዋች፣ ኤር ፖድ እና የመሳሰሉት ምርቶቹ ወደ ገበያው እየመጣ ይገኛል፡፡
ለተጨማሪው :https://news.1rj.ru/str/EventAddis1