TEMARI-NET – Telegram
TEMARI-NET
4.11K subscribers
910 photos
17 videos
167 files
288 links
This Channel is created to disseminate proper, timely information and news for Students
Download Telegram
#Repost #ExitExam

👉የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች መረጃ አሰጣጥ


፨ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

ጉዳዩ- የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎችን መረጃ አሰጣጥን ይመለከታል!


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀገራዊ የቅድመ-ምረቃ መውጫ ፈተና ከሰኔ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ተወስኖ የአፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 919/2014 ወጥቶ ተግባር ላይ ውሏል፡፡ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 12 (12.3) ላይ የመውጫ ፈተና ውጤት በተማሪዎች ሰርተፍኬት (Temporary Degree) ወይም ትራንስክሪፕት ላይ አልፏል (PASS) ወይም ወድቋል (FAIL) በሚል እንዲቀመጥ እና ከዚህ ደብዳቤ ጋር አባሪ በተደረገው ሰርተፍኬት ፎርማት መሠረት እንዲፈጸም እናሳውቃለን፡፡ (ትምህርት ሚኒስቴር)



@TEMARI_NET1
2
🎓 Congratulations! 🎉

ከ30 በላይ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች በሳምንቱ መጨረሻ ማለትም ሰኔ 14 እና 15/2017 ዓ.ም ያስመርቃሉ።

🎓 ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ
🎓 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ጅማ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ዲላ ዩኒቨርሲቲ
🎓 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
🎓 አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
🎓 አምቦ ዩኒቨርሲቲ
🎓 መቐለ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ወልድያ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ
🎓 ራያ ዩኒቨርሲቲ
🎓 አክሱም ዩኒቨርሲቲ
🎓 ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
🎓 ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ
🎓 እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
🎓 አሶሳ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ሰመራ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ
🎓ወሎ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ጂንካ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ
🎓 መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ቦረና ዩኒቨርሲቲ
🎓 አርሲ ዩኒቨርሲቲ
🎓 ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
🎓 መቱ ዩኒቨርሲቲ
🎓 የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ


፨ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ 🥳

@TEMARI_Net1
9
ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎች እና የዋንጫ ተሸላሚዋ

ፌቨን ጉርጁ አውግቸው በ2017 ዓ.ም ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች እጅግ ከፍተኛውን ውጤት በማምጣት ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎች እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች፡፡

የሳይበር ደህንነት የትምህርት መስክ ተማሪዋ ፌቨን፤ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 4.00 በማምጣት ከትምህርት ክፍሏ፣ ከፋኩልቲዋ፣ ከኮሌጇ እንዲሁም ከአጠቃላይ የዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች ከፍተኛ የሆነውን ውጤት አስመዝግባለች፡፡

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን፤ ከተመራቂዎቹ መካከል 111ዱ የሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ተመራቂዎች ናቸው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በሳይበር ደህንነት የትምህርት መስክ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡

#tikvahuniversity

@TEMARI_Net1
🔥5👏21
በርካታ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በልዩ ልዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች እያስመረቁ ነው።

ከ25 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ፡፡

ተመራቂዎቹ በተለያዩ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁና የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ የቅድመ-ምረቃ መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም የድኅረ-ምረቃ እና የስፔሻሊቲ ፕሮግራም ሰልጣኞች ናቸው፡፡

እንኳን ደስ አላችሁ!

ምስል፦ መቀሌ፣ጅማ፣ ባህርዳር፣ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲዎች

@TEMARI_Net1
በርካታ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በልዩ ልዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች እያስመረቁ ነው።

ከ25 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች በዛሬው ዕለት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ፡፡

ተመራቂዎቹ በተለያዩ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁና የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ የቅድመ-ምረቃ መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም የድኅረ-ምረቃ እና የስፔሻሊቲ ፕሮግራም ሰልጣኞች ናቸው፡፡

እንኳን ደስ አላችሁ!

ምስል፦ መቀሌ፣ጅማ፣ ባህርዳር፣ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲዎች

@TEMARI_Net1
2
መንትዮች ተመራቂዎች 🎉

ዮሐንስ ደረጀ እና ያዕቆብ ደረጀ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሶፍትዌር ምህንድስና ዛሬ ተመርቀዋል።

መንትዮቹ ከልጅነታቸው ጀምረው በአንድ ክፍል ፊደል ቆጥረው፣ በአንድ ሁለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረው በጅማ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ ተምረው በተመሳሳይ ውጤት እና ደረጃ ለማጠናቀቅ ችለዋል። #JiT

#tikvahuniversity
3
Fully Funded Leadership Conference in the USA 2025

Conference Dates: Oct. 30 - Nov. 2, 2025

Location: Harvard Kennedy School

Link: https://scholarshipscorner.website/harvrd-public-policy-leadership-conference/

Benefits: All expenses are covered by Harvard Kennedy School — including travel, accommodation, and meals during the conference.

Deadline: 7 July, 2025.

Credit: The President and Fellows of Harvard College. Harvard Kennedy School
The content is based on and adapted from information available on the official website. Details are subject to change. For any credit or content inquiries, please contact us

@TEMARI_Net1
ይህ ተመራቂ ለእናቱ ያለውን ፍቅርለመግለፅ የሞከረበት ምስል ነው።እናት ከሰል ሽጣ ልጇን አስተምራ ዛሬ አስመረቀች። እሱም በምርቃት ቦታው በጓደኞቹ ፊት አመሠግንሻለሁ ብሎ ክሰል ራሱ ላይ አድርጎ ፍቅሩን መግለፁ ከምስሉ ጋር የወጣው ሃሳብ ያስረዳል።።


@TEMARI_NET1
7
#DillaUniversity
#ClassOf2025
#CommencementPhotos

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ከወሰዱ የ2017 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ አጠቃላይ ተማሪዎች ውስጥ ከ75 በመቶ በላይ የሚሆኑት ማለፋቸውን ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,576 ተማሪዎች አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ ሁለት ተማሪዎች በሦስተኛ ዲግሪ እና 100 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው።

በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል የማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ምሩቅ የሆነው ዳንኤል ግርማ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.96 በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

#tikvahuniversity