Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለፉት ተከታታይ አመታት በተለይም ባለፈው አመት ከፍተኛ ፈተና ገጥሞታል፤

👉 በአገር ውስጥ ጦርነት በውጭ የራሺያና ዩክሬን ጦርነት፣ ድርቅና ኮሮኖ በኢኮኖሚው ላይ ድቆሳ ያሳደሩበት አመት ነበር፤

👉 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በቀላሉ የማይሰበር መሆኑን በያዘው የዕድገት መስመር የሚቀጥል መሆኑን እያስመሰከረ፣

👉 126 ነጥበ 7 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፤ የነፍሰ ወከፍ ገቢ አንድ ሺህ 212 ደርሷል፤

👉 በምሰራቅ አፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚ አንዱ ሆኗል፤ ከሰሀራ በታች ካሉ አገራት ሶስት ኢኮኖሚ መካከል አንዱ ሆኗል፤

👉 ባለፈው አመት ጂዲፒው 6 ነጥብ4 እድገት አስመዝግቧል፤ በዚህ አመት ቢያንስ 7 ነጥብ 5 በመቶ እናድጋለነ፣

👉 በግብርናው ዘርፍ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል፤

👉 ዘንድሮ አማራ ክልል የጀመረውን ተሞክሮ ወደ ሌሎች ክልሎች አሻግረን 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንጠብቃለን፤

👉 ስለዚህም ሩዝ ወደ አገር ውስጥ ማስገባት አያስፈልገንም፤

👉 ሩዝ በሚቀጥሉት አመታት እንደ ስንዴው ወደ ውጭ ገበያ የማቅረብ ደረጃ ይደርሳል፤

👉 በበቆሎም ከፍተኛ ምርት ነው የተገኘው፤

👉 ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን በላይ አዳዲስ የቡና ችግኝ ተተክሏል፤

👉 የቡና ምርተ ዘንድሮ ከ20 በነቶ በላይ ብልጫ ይጠበቃል፤

👉 ግብርና ላይ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ከቀጠለ ኢትዮፕያን የዳቦ ቅርጫት ማድረግ የሚቻል መሰረት አለ፤

👉 ከእርሻ ስራ አንጻር ገበሬና በሬን መለያየት አለብን፤ የጀመርነው አለ ብዙ ስራ ይጠበቅብናል፤

👉 ኢንደስትሪ 4 ነጥብ 9 በመቶ አድጓልካምናው እድገት አንጻር ቅናሽ አሳይቷል፤

👉 ለቅናሹ ምክንያት የግንባታው ዘርፍ በሲሚንቶ ምክንያት በመቀዘቀዙ ነው፤

👉 በአምራች ዘርፍ ግን የተሻለ እድገት ተገኝቷልዘንድሮም ይጠናከራል፣

👉 የአገልግሎት ዘርፉ 7 ነጥብ 6 በመቶ እድገት አስመዝግቧል፤

👉 አየር መንገድ ለአገልግሎት ዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጾ አድረጓል፤

👉 ኢትዮ ቴሌኮም ዛሬ 68 ነጥብ 9 ደንበኞች አሉት፤ ትረፋማነቱ አድጓል፤

👉 25 ነጥበ 5 ሚሊዮን ሰዎች በቴሌ ብር መጠቀም ጀምረዋል፤ 134 ቢሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ልውውጥ ተደርጓል፤

👉 የፋይናስ ዘርፉ ያለው ሀብት 2 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር ደርሷል፤

👉 82 ነጥበ 2 የባንክ ደብተሮች ያላቸው ደንበኞች ተፈጥረዋል፤

👉 በባንክ ያለው ተቀማጭ 1 ነጥብ 6 ትሪሊየን ብር ደርሷል፤

👉 ባንኮች የሰጡት ብድር ከአምናው በ29 በመቶ አድጓል፤ 353 ቢሊዮን ብር ብድር ተሰጥቷል፤

👉 ሜጋ ፕሮጀክቶቻችን በሙሉ በገባነው ቃል መሰረት ተፈጽመዋል፤ እየተፈጸሙ ነው፤

👉 የዋጋ ግሽበት የማክሮ ኢኮኖሚያችን ስብራት ነው፤

👉 ግሽበት የእኛ ብቻ ሳይሆን የዓለም ፈተና ሆኗል፤

👉 ያለፉትን አራት አመታት መረጃ ስንመለከት የኢትዮጰያ የዋጋ ግሽበት እድገት እያሳየ ሳይሆን በመቀነስ ሂደት ላይ ነው፣
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️

👉 9 ነጥብ አምስት ሚሊየን ህጻናት ተማሪዎችን በቀን ሁለት ጊዜ በትምህርት ቤት እየተመገቡ ነው፤

👉 በሚቀጥሉት አመታት አዲስ ዩኒቨርሲቲ አንከፍትም፤

👉የመንግስት ትኩረት በቀጣይ አመታት ቅድመ መደበኛ፣ አንደኛ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ይሆናል፤

👉ዩኒቨርሲቲዎች ከመንግስት በጀት መላቀቅ አለባቸው፤

👉 የኮሮና ቫይረስ እንደ ችግር ሳይሆን እንደ እድል መጠቀም በመቻላችንና መሬት ጦም አናሳድርም በማለታችን ዛሬ ስለስንዴ ኤክስፖርት ማውራት የቻልነው፤

👉የተጀመረው የሌማት ቱሩፋት በደንብ ተጋግዘን ከሰራንበት ኢትዮጵያ ውስጥ ምግብ አጀንዳ የማይሆንበት እድል ይፈጠራል፤

👉የግሽበት መሰረታዊ መፍትሄው ምርትን ማሳደግ ነው፤ የጓሮ ግብርና ፋሽን ሆኖ መቅረት የለበትም፤

👉 ከዚህ አንጻር መንግስት ቢደረግ ብሎ የሚያስበው ብክነትን መቀነስ፤ ማጋራት፣ ማምረትና ሌብነትን መቀነስ ነው፤

👉 ምንም ቢመረት ግን ሌብነት ካለ ለውጥ አይመጣም፤

👉 በአመት ከ18 ቢሊዮን ዶላይ በላይ ገንዘብ ለገቢ ምርት ታወጣለች፣

👉 ስድስት ሺህ አይነት ምርቶች ወደ አገር ውስጥ ይገባሉ፤ ከዚህ ውስጥ 38ቱ ላይ እገዳ ተጥሎባቸዋል፤

👉 ለእነዚህ 38 ምርቶች ባለፈው አመት የወጣው ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው፤ ይህ ገንዘብ ለማዳበሪያ ከወጣው ጋር ተመሳሳይ ነው፤

👉 እገዳ የተጣለበቸወ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረተ እድል ይሰጣሉ፤

👉 ምርቶቹ ለጥቁር ገበያ የተጋለጡ ናቸው፤ መሰረታዊ ሸቀጦችም አይደሉም፤

👉 አንድ አነዶቹ ምርቶች የቅንጦት እቃመ ስለሆኑ ለጊዜው እንዳይገቡ አግደናል፤ ያስፈልጉንም ማለት አይደለምና ለወደፊት ሁኔታው እየታየ ይፈቀዳል፤
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️

👉 መሬትን ህገ መንግስቱ የህዝብና የመንግስተ ነው ይላል ነገር ግን የደላሎች ሆኗል፤ ይሄንን ማስተካከል አለብን፤

👉 ቢያንስ ቢያንሰ በከተሞች ደረጃ መሬት የግለሰቦች መሆን አለበት፤

👉 ዋና ዋና በምንላቸው ዘርፎች ላይ ለመስራት የሚመጣ ኢንቨስተር ካለ ተገቢውን ድጋፍ እናደርጋለን፤

👉 በምሰራቅ አፍሪካ ትለቁ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት እድገት ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፤

👉 ውሃን መጠቀም የቻለ አገር ይለማል አይራብም፤ ከዚህ አንጻር ይሄንን ጉዳይ የሚሰራ ሚኒስቴር አቋቁመናል፤ በዚህም በርካታ ለውጥ እየመጣ ነው፤

👉 ባለፈው አመት በአገር ደረጃ ውሃና የውሃ አስተዳደርን የሰራነው ስራ በ10 አመት ያልተሰራ ስራ ነው፤ ውጤቱን ቀስ እያልን እናየዋለን፤

👉 ኢትዮጵያ ውስጥ ስራ የሰራተኛ ያለህ እያለ ይጮሃል፤ ሰራተኛው ደግሞ የስራ ያለህ ብሎ ይጮሃል፤

👉 መንግስት ይሄንን ድልድይ ሆኖ ለማገናኘት ሰራተኛና ክህሎት ሚኒስቴርነ አቋቁሟል፤

👉 ዘንድሮ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ሰው ስራ ለማስያዝ እቅድ ተየዞ እየተሰራ ነው፤

👉 ከስራ ፈላጊው ሰው ውስጥ 68 በመቶ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቀ ነው፤

👉 ከስራ ፈላጊው ሰው ውስጥ 20 በመቶ ሁለተኛ ደረጃን ያጠናቀቀ ነው፤

👉 ከስራ ፈላጊው ሰው ውስጥ 12 በመቶ ቴክኒክና ሙያን ያጠናቀቀ ነው፤

👉 ልንገነባ ያሰብነው የጫካ ቤት ይባላል፤ ለአፍሪካ ለኢትዮጵያ ኩራት የሚሆን ሳተላይት ከተማ ነው፤

👉 ለፕሮጀክቱ ገንዘብ ከፓርላማ አልጠየቅንም፤ አንጠይቅምም፤

👉 ጀምረን የተውነ ው የለም፤ ጀምረን የማንጨርሰው አይኖርም፤

👉 ለኢትዮጵያ ኩራት የሚሆን ስራ እየሰራነ እንቀጥላለን፤
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️
👉 የማያልቅ ጦርነት ውሃ በወንፊት ነው፤ ዝም ብሎ እየተዋጉ መኖር አይቻልም፤
👉 ሰላምና ብልጽግናን ለማስቀጠል ሲባል ጦርነትን ማቆም በእጅጉ ያስፈልጋል፤
👉 የሰላም መጥፎ የጦርነት ጥሩ የለውም፤
👉 ጦርነት እያሸነፍክም ቢሆን መጥፎ ነው፤ ምክንያቱም ሰው ነው የምትገለው፤
👉 የኢትዮጵያን ልዕልና የሚገዳደር ሲፈጠር ያ ነገር በሰላም የማይፈጠርበት ሁኔታ ሲፈጠር መፋለም ግዴታችን ነው፤
👉 ድርድርም ካለ ንግግርም ውይይትም ካለ ለኢትዮጵያ አንደነት ብቻ ነው፤
👉 ለኢትዮጵያ አንደነትና ጥቅም ሲባል መሄድ የማንፈልግባቸው ቦታዎች ጭምር እንሄዳለን፤
👉 ከሰላም የምታተርፈው ኢትዮጵያ ናት፤
👉 ሰላም የሚያስከፋቸው ሃይሎች የጦርነት ነጋዴዎች ናቸው፤
👉 ተነጋግረናል፤ ተስማምተናል፤ ፈርመናል፤ ከዚህ በሁዋላ የገባነውን ቃል በማክበር ሰላሙን ዘላቂ ማድረግ ነው፤
👉 የወልቃይት ህዝብ እንዲገነዘብ የምንፈልገው የሚወራው ሽረባ ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት የለበትም፤
👉 ደቡብ አፍሪካ የሄድነው ለወልቃይት ጉዳይ ለመነጋገር አይደለም፤ ቦታውም አይደለም፤
👉 የተስማማነው በኢትዮጵያ ህግና መንግስት ይፈጸም ብለን ነው፤
👉 ወልቃይት በተመለከተ ያ ህዝበ የትም ይሁን የትም እንዲወስን ዴሞክራሲያዊ እድል ከሰጠነው ብቻ ነው ዘላቂ ሰላምና መፍትሄ የሚመጣው፤
👉 ሸኔ እንኳን ለእኛ ለሚልኩት ሰዎችም አስቸጋሪ ሆኗል፤ ምንም የሚጨበጥ አላማም ማዕከልም የሌለው ነው፤
👉 ለኦሮሞ ቆሚያለሁ ይላል ኦሮሞን ይገድላል፤ ያፈናቅላል፤
👉 በሃይል የሚጣ ሰላም የለም፤ እኛ ለሰላምና ለንግግር ሁሌም በራችን ክፍት ነው፤
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️
👉ቀይ መስመር ያልነውን ሌብነት ቀይ ምንጣፍ ያደረጉ ሰዎች እየተፈጠሩ ነው፣
👉 ሳይሰሩ የሚበሉ ሳይሆን የሚሰራውንም ሰው የሚበሉ አሉ፤
👉 ሌባ ቤት ይሰራ ይሆናል እንጂ አገር አይኖረውም፣
👉 በሌብነት ቤት እንጂ አገር አይገነባም፤ አገር አልባ ቤት ደግሞ ዘላቂነት አይኖረውም፤
👉 ሌብነት ባናጠፋ እንኳን አንገቱን እናስደፋለን፤
👉 ብዙ የሚደክሙ ሰዎች ቢኖሩም አሁንም ሌቦች ስላሉ መፈተሽና ማረቅ ያስፈልጋል፤
👉 ሌብነት ብቻ ሳይሆን ስራን የሚገድሉ ሰዎችም አሉ፤
👉 የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መለያ ነጻነት እኩልነት እና ፍትሃዊነት ነው፤
👉 የኢትዮጵያን ሰላም ላገዙ ሁሉ ከፍተኛ ምስጋና እናቀርባለን፤
👉 ኢትዮጵያዊያን በመላው አለም ባሉበት አገር ሆነው ለአገራቸው ጥቅም ሊሰሩ ይገባል፤ ባሉበት አገር ፖለቲካም እንዲሳተፉ እመክራለሁ፤
ስምምነቱ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን መከላከያ ሚኒስቴር ገለጸ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የፌዴራል መንግስት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ከህወሃት ጋር በደቡብ አፍሪካ የደረሰው ስምምነት አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን በመከላከያ ሚኒስቴር የውጭ ግንኙነት እና ወታደራዊ ትብብር ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ተሾመ ገመቹ ገለጹ፡፡
በፌደራል መንግስትና በህወሃት መካከል ስለተደረሰው የሰላም ስምምነት መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ባደረጉ ኤምባሲዎች ላሉ የወታደራዊ አታሼዎች ስለ ሰላም ስምምነቱ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት የተካሄደው ጦርነት የኢትዮጵያን ሰላም ያናጋ፣ የህዝብን በሰላም የመኖር፣ ወጥቶ የመግባትና የመኖር ደህንነትን አደጋ ላይ የጣለ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ስምምነቱ ወሳኝ ምዕራፍ እና አዲስ የተስፋ ምዕራፍን የከፈተ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
የመከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የማስከበር፣ የሕዝብን ደህንነት የማስጠበቅ እና የሰብዓዊ ድጋፍ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልሎች በተቀላጠፈ መንገድ እንዲደርስ የሚደረገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ተናገሩት፡፡
የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ መኖሪያ ቀያቸው እንዲመለሱ እየተሰራ መሆኑን በመጠቆምም፤ የተደረሰው ስምምነት ተፈጻሚ እንዲሆን የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባልም ብለዋል፡፡
በዘላለም ግዛው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ወልቃይትን በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ‼️
የሚናፈሰው ወሬ ላይ የመንግሥት እጅ የለበትም። የፕሪቶሪያው ስምምነት ሰላምን በማምጣት ላይ ያተኮረ ነው እንጂ የሀገራችንን የመሬት ጉዳይ የተመለከተ አይደለም። በሀገራችን ህግ እና ስርዓት መሰረት የሚፈጸም ነው። ከሕገ መንግስቱ በፊት በጉልበት ነው የተወሰደው ላሉት፣ የኔም ፍላጎት ያ እንዳይደገም ነው።
በጉልበት ዛሬም ተመሳሳዩ ተግባር መፈጸም የለበትም። በሕግ እና በስርዓት ቢፈጸም ለወልቃይት ይጠቅማል፣ ለአማራም ለትግራይም ይጠቅማል። ረዘም ላለ ጊዜ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል። ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ንግግር ያስፈልጋል።
የተሰጣቸውን ሥራ በትክክል የማይሰሩ ሰዎች የፌደራል መንግስትን ስም እያነሱ ብዙ ሽረባ እንደሚሰሩ ግልጽ ነው። እኛ ስምምነቱ እንዳይበላሽ ብለን ነው ዝም ያልነው። ሁሉም የተሰጠውን ሥራ መስራት አለበት።
የትግራይ ሕዝብ ሕዝባችን ነው ብለናል፣ ከፍላጉቱና ከእሳቤው ውጪ ችግር ላይ ሲወድቅ እኛ ካላገዝነው ማን ያግዘዋል? መቸገሩ የሚያስታውቅ እኮ ነው። ስናሸነፍ ደግ እና ይቅር ባይ፣ ሚዛናዊ መሆን ያስፈልጋል።
የትግራይ ህዝብ ሰላም ፈላጊነቱን አሳይቷል፣ ወታደሩ ተመልሶ ድጋፉን ቀጥሎ ‘ይህንን ሰራዊት ነው ወይ ያጠቃነው?’ የሚሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ውይይቱን ማስቀጠል ያስፈልጋል። የትግራይ ህዝብ ዘላቂ ሰላምን፣ ዉሀ፣ መብራት፣ አገልግሎት እንደሚፈልግ፣ ከሌሎች ወንድም ህዝቦች ጋር ምንም ችግር እንደሌለበት አይተናል። ሰላሙ እንዳይበላሽ በታማኝነት ያለውን ሁሉ ለመስራት ዝግጁ ነኝ። እናንተም ይህንኑ እንድትደግፉ ነው የምፈልገው።
ከአማራ በኩል ብዙ ወልቃይቴዎች ተፈናቅለዋል፣ እነርሱ ሳይኖሩ ሕዝበ ውሳኔ ቢባል እንጎዳለን ተብሏል። በትግራይ በኩል አሁን ባለው ግጭት ተፈናቅለናል ስለዚህ ሕዝበ ውሳኔ ቢፈጸም እንጎዳለን ብለዋል። ነገር ግን፣ ወልቃይቴ የትም ቢሄድ ይታወቃል።