አቶ ደመቀ መኮንን በቤጂንግ የተገነባውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መርቀው ከፈቱ
*********************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ መንግስት በቻይና ርዕሰ መዲና ቤጂንግ ያስገነባውን አዲስ ኤምባሲ እና የመኖሪያ ህንጻ በዛሬው ዕለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተገኙበት አስመርቋል።
አቶ ደመቀ መኮንን በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኤምባሲው አዲስ ገጽታ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የአጋርነት ጠቀሜታ የበለጠ ለማጠናከር የተወሰደ እርምጃ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያና የቻይና የቀደመ ግንኙኑት በሁለቱ አገሮች ማካከል ላለው ጥልቅ የሆነ ኢኮኖሚያዊ፣ በባህላዊ እና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር መሠረት የጣለ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ለቻይና-አፍሪካ ትብብር ስኬት ተምሳሌት ለመሆን ተግታ ትሰራለች ብለዋል።
አያይዘውም፣ ኢትዮጵያና ቻይና የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት በሁለትዮሽ በክልላዊና በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ በጋራ እንደሚቆሙ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋን፣ አዲሱ ኤምባሲ መገንባቱ የኢትዮጵያ እና የቻይና ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።
የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በበኩላቸው፣ የኤምባሲው ህንጻ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ቻይና ላደረገላቸው ያላሰለሰ ትብብር አመስግነው፣ አጅግ በረቀቀ መልኩ የተገነቡት የኤምባሲው እና የመኖሪያ ቤቱ ህንጻዎች ለትውልድ የሚተርፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም፣ በቻይና የኢፌዲሪ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ባደረጉት ንግግር፣ የኤምባሲው ግንባታ የኢትዮጵያና ቻይና ወዳጅነት ሃውልት ነው ማለታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢፕድ የላከው መረጃ ያመለክታል።
*********************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ መንግስት በቻይና ርዕሰ መዲና ቤጂንግ ያስገነባውን አዲስ ኤምባሲ እና የመኖሪያ ህንጻ በዛሬው ዕለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተገኙበት አስመርቋል።
አቶ ደመቀ መኮንን በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኤምባሲው አዲስ ገጽታ ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የአጋርነት ጠቀሜታ የበለጠ ለማጠናከር የተወሰደ እርምጃ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያና የቻይና የቀደመ ግንኙኑት በሁለቱ አገሮች ማካከል ላለው ጥልቅ የሆነ ኢኮኖሚያዊ፣ በባህላዊ እና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር መሠረት የጣለ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ለቻይና-አፍሪካ ትብብር ስኬት ተምሳሌት ለመሆን ተግታ ትሰራለች ብለዋል።
አያይዘውም፣ ኢትዮጵያና ቻይና የጋራ ተጠቃሚነታቸውን ለማጎልበት በሁለትዮሽ በክልላዊና በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ በጋራ እንደሚቆሙ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋን፣ አዲሱ ኤምባሲ መገንባቱ የኢትዮጵያ እና የቻይና ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።
የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በበኩላቸው፣ የኤምባሲው ህንጻ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ቻይና ላደረገላቸው ያላሰለሰ ትብብር አመስግነው፣ አጅግ በረቀቀ መልኩ የተገነቡት የኤምባሲው እና የመኖሪያ ቤቱ ህንጻዎች ለትውልድ የሚተርፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም፣ በቻይና የኢፌዲሪ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ባደረጉት ንግግር፣ የኤምባሲው ግንባታ የኢትዮጵያና ቻይና ወዳጅነት ሃውልት ነው ማለታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢፕድ የላከው መረጃ ያመለክታል።
በኢትዮጵያና ቻይና ከፍተኛ ተቋማት መካከል ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያና ቻይና ከፍተኛ ተቋማት መካከል ጉድኝት መፍጠርና በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገልጸዋል፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በመገኘት ለቻይናውያን ተማሪዎች የተዘጋጁ መጽሃፍት መረቃ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከቻይና የምርምር ተቋማት ጋር የእውቀት ልውውጥ ማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲተና በቤጂንግ የውጭ ጥናቶች ዩኒቨርሲት መካከል ያለው የአማርኛ ቋንቋ ትብብር የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን የበለጠ ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ጂያ ዌንጂያን (GIA WENGIAN) በበኩላቸው ቋንቋው በቻይና መሰጠቱ የኢትዮጵያን በህልና ታሪክ ለማስተዋወቅ ትልቅ ጠቀቤታ አለው ብለዋል፡፡
በስነስርዓቱ ሶስት የአማርኛ መመሪያ መጽሃፍቶች የተመረቁ ሲሆን ቻይናውያን የአማርኛ ቋንቋ ተማሪዎች ግጥም አቅርበዋል፡፡
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያና ቻይና ከፍተኛ ተቋማት መካከል ጉድኝት መፍጠርና በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገልጸዋል፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በመገኘት ለቻይናውያን ተማሪዎች የተዘጋጁ መጽሃፍት መረቃ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከቻይና የምርምር ተቋማት ጋር የእውቀት ልውውጥ ማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲተና በቤጂንግ የውጭ ጥናቶች ዩኒቨርሲት መካከል ያለው የአማርኛ ቋንቋ ትብብር የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን የበለጠ ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ጂያ ዌንጂያን (GIA WENGIAN) በበኩላቸው ቋንቋው በቻይና መሰጠቱ የኢትዮጵያን በህልና ታሪክ ለማስተዋወቅ ትልቅ ጠቀቤታ አለው ብለዋል፡፡
በስነስርዓቱ ሶስት የአማርኛ መመሪያ መጽሃፍቶች የተመረቁ ሲሆን ቻይናውያን የአማርኛ ቋንቋ ተማሪዎች ግጥም አቅርበዋል፡፡
በአፍሪካ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ዴሞክራሲን ከአህጉሪቱ ነባር እሴቶች አንጻር ቃኝቶ መተግበር ያስፈልጋል
********************
(ኢ ፕ ድ)
በአፍሪካ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ዴሞክራሲን ከራሳችን ከአፍሪካውያን ማንነትና እሴት አንጻር ቃኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ሲሉ በኢትዮጵያ የአንጎላ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚጉኤል ዶሚንጎስ ቤምቤ (ዶክተር) ገለጹ።
በርካታ የአፍሪካ አገራት የሚጠበቅባቸውን የአባልነት መዋጮ በአግባቡ ባለመክፈላቸው የህብረቱ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓልም ብለዋል።
አምባሳደር ሚጉኤል ዶሚንጎስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኅብረቱና...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100525
********************
(ኢ ፕ ድ)
በአፍሪካ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ዴሞክራሲን ከራሳችን ከአፍሪካውያን ማንነትና እሴት አንጻር ቃኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ሲሉ በኢትዮጵያ የአንጎላ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚጉኤል ዶሚንጎስ ቤምቤ (ዶክተር) ገለጹ።
በርካታ የአፍሪካ አገራት የሚጠበቅባቸውን የአባልነት መዋጮ በአግባቡ ባለመክፈላቸው የህብረቱ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓልም ብለዋል።
አምባሳደር ሚጉኤል ዶሚንጎስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኅብረቱና...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100525
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መልዕክት‼️
የዚህ ዓመት የበጋ ስንዴ ምርታማነት በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል።
የዚህ ዓመት የበጋ ስንዴ ምርታማነት በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል።
👉“በአፈር ማዳበሪያ እጥረት ምክንያት መሬታችን ፆም እንዳያድር እየሰጋን ነው” -የአማራ ክልል አርሶ አደሮች
👉“በክልሉ የተከሰተውን የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ እየሰራን ነው” -የክልሉ ግብርና ቢሮ
************************
(ኢ ፕ ድ)
በአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ምክንያት ቀድመው መዘራት ያለባቸው ምርቶችን መዝራት ባለመቻላችን መሬታችን ፆም እንዳያድር ከፍተኛ ስጋት ገብቶናል ሲሉ የአማራ ክልል አርሶ አደሮች ገለጹ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ በበኩሉ የተከሰተውን የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ እየሰራሁ ነው ብሏል።
በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ደምበጫ ወረዳ አርሶ አደር አቶ ገደፍ ደሳለኝ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በደምበጫ ወረዳ የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት በመኖሩ ምክንያት ቀድመው የሚዘሩ ምርቶችን መዝራት አልቻልንም፤ በመሆኑም መሬታችን ፆም እያደረ ነው ብለዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100567
ፎቶ ከፋይል
👉“በክልሉ የተከሰተውን የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ እየሰራን ነው” -የክልሉ ግብርና ቢሮ
************************
(ኢ ፕ ድ)
በአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ምክንያት ቀድመው መዘራት ያለባቸው ምርቶችን መዝራት ባለመቻላችን መሬታችን ፆም እንዳያድር ከፍተኛ ስጋት ገብቶናል ሲሉ የአማራ ክልል አርሶ አደሮች ገለጹ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ በበኩሉ የተከሰተውን የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ እየሰራሁ ነው ብሏል።
በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ደምበጫ ወረዳ አርሶ አደር አቶ ገደፍ ደሳለኝ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በደምበጫ ወረዳ የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት በመኖሩ ምክንያት ቀድመው የሚዘሩ ምርቶችን መዝራት አልቻልንም፤ በመሆኑም መሬታችን ፆም እያደረ ነው ብለዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100567
ፎቶ ከፋይል
ምክረ ሃሳቦቹ ለሀገር ኢኮኖሚ ማንሰራራት ትልቅ ሚና አላቸው
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ምክር ቤት የሚያቀርባቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክርና ሀሳቦች ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ግብአት በመሆን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ምክር ቤት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ‹የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክር ጥበብና ሳይንስ› በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው አውደ ጥናት ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ዶክተር ፍጹም አሰፋ እንደገለጹት፤ ይህ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100534
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ምክር ቤት የሚያቀርባቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክርና ሀሳቦች ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ግብአት በመሆን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ምክር ቤት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ‹የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክር ጥበብና ሳይንስ› በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው አውደ ጥናት ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ዶክተር ፍጹም አሰፋ እንደገለጹት፤ ይህ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100534
የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት ከህወሃት ታጣቂ ሀይሎች የቡድን መሳሪያዎችን ተረከበ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች በፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ዛሬ መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች ዛሬ አስረክበዋል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።
በርክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንዳሉት፤ ርክክብቡ የሰላም ስምምነቱ አንዱ አካል ነው።
የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጀነራል ምግበይ ሃይለ በበኩላቸው ርክክቡ በሰላም ስምምነት መሰረት መሰረት መፈጸሙን ተናግረዋል። ሰላም የመጀመሪያና የመጨረሻ ግባችን ነውም ብለዋል።
ርክክቡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተከናውነናል።
ከቡድን መሳሪያዎቹ ርክክብ በኋላ መግለጫ የሰጡት በአፍሪካ ሕብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዴር ጀነራል ቴፎ ሰኮሌ የርክክብ ሂደቱ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ መልኩ እየሄደ መሆኑን አንዱ ማሳያ ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች በፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ዛሬ መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች ዛሬ አስረክበዋል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።
በርክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንዳሉት፤ ርክክብቡ የሰላም ስምምነቱ አንዱ አካል ነው።
የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጀነራል ምግበይ ሃይለ በበኩላቸው ርክክቡ በሰላም ስምምነት መሰረት መሰረት መፈጸሙን ተናግረዋል። ሰላም የመጀመሪያና የመጨረሻ ግባችን ነውም ብለዋል።
ርክክቡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተከናውነናል።
ከቡድን መሳሪያዎቹ ርክክብ በኋላ መግለጫ የሰጡት በአፍሪካ ሕብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዴር ጀነራል ቴፎ ሰኮሌ የርክክብ ሂደቱ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ መልኩ እየሄደ መሆኑን አንዱ ማሳያ ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ