Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በኢትዮጵያና ቻይና ከፍተኛ ተቋማት መካከል ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አቶ ደመቀ መኮንን ገለጹ
*****
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያና ቻይና ከፍተኛ ተቋማት መካከል ጉድኝት መፍጠርና በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ምኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገልጸዋል፡፡

አቶ ደመቀ መኮንን በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በመገኘት ለቻይናውያን ተማሪዎች የተዘጋጁ መጽሃፍት መረቃ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከቻይና የምርምር ተቋማት ጋር የእውቀት ልውውጥ ማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲተና በቤጂንግ የውጭ ጥናቶች ዩኒቨርሲት መካከል ያለው የአማርኛ ቋንቋ ትብብር የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን የበለጠ ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝዳንት ጂያ ዌንጂያን (GIA WENGIAN) በበኩላቸው ቋንቋው በቻይና መሰጠቱ የኢትዮጵያን በህልና ታሪክ ለማስተዋወቅ ትልቅ ጠቀቤታ አለው ብለዋል፡፡

በስነስርዓቱ ሶስት የአማርኛ መመሪያ መጽሃፍቶች የተመረቁ ሲሆን ቻይናውያን የአማርኛ ቋንቋ ተማሪዎች ግጥም አቅርበዋል፡፡
በአፍሪካ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ዴሞክራሲን ከአህጉሪቱ ነባር እሴቶች አንጻር ቃኝቶ መተግበር ያስፈልጋል
********************
(ኢ ፕ ድ)
በአፍሪካ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ዴሞክራሲን ከራሳችን ከአፍሪካውያን ማንነትና እሴት አንጻር ቃኝቶ መተግበር ያስፈልጋል ሲሉ በኢትዮጵያ የአንጎላ ሪፐብሊክ አምባሳደር ሚጉኤል ዶሚንጎስ ቤምቤ (ዶክተር) ገለጹ።
በርካታ የአፍሪካ አገራት የሚጠበቅባቸውን የአባልነት መዋጮ በአግባቡ ባለመክፈላቸው የህብረቱ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓልም ብለዋል።
አምባሳደር ሚጉኤል ዶሚንጎስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኅብረቱና...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100525
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መልዕክት‼️
የዚህ ዓመት የበጋ ስንዴ ምርታማነት በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል።
👉“በአፈር ማዳበሪያ እጥረት ምክንያት መሬታችን ፆም እንዳያድር እየሰጋን ነው” -የአማራ ክልል አርሶ አደሮች
👉“በክልሉ የተከሰተውን የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ እየሰራን ነው” -የክልሉ ግብርና ቢሮ
************************
(ኢ ፕ ድ)
በአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ምክንያት ቀድመው መዘራት ያለባቸው ምርቶችን መዝራት ባለመቻላችን መሬታችን ፆም እንዳያድር ከፍተኛ ስጋት ገብቶናል ሲሉ የአማራ ክልል አርሶ አደሮች ገለጹ።
የክልሉ ግብርና ቢሮ በበኩሉ የተከሰተውን የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት ለመቅረፍ እየሰራሁ ነው ብሏል።
በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ደምበጫ ወረዳ አርሶ አደር አቶ ገደፍ ደሳለኝ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በደምበጫ ወረዳ የአፈር ማዳበሪያ ግብዓት እጥረት በመኖሩ ምክንያት ቀድመው የሚዘሩ ምርቶችን መዝራት አልቻልንም፤ በመሆኑም መሬታችን ፆም እያደረ ነው ብለዋል።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100567
ፎቶ ከፋይል
ምክረ ሃሳቦቹ ለሀገር ኢኮኖሚ ማንሰራራት ትልቅ ሚና አላቸው
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ምክር ቤት የሚያቀርባቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክርና ሀሳቦች ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ግብአት በመሆን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ተገለጸ።
የኢትዮጵያ ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ምክር ቤት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ‹የኢኮኖሚ ፖሊሲ ምክር ጥበብና ሳይንስ› በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው አውደ ጥናት ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ዶክተር ፍጹም አሰፋ እንደገለጹት፤ ይህ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100534
የግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም የስራ ማስታወቂያ፣ መልካም ዕድል‼️
የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት ከህወሃት ታጣቂ ሀይሎች የቡድን መሳሪያዎችን ተረከበ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች በፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ዛሬ መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች ዛሬ አስረክበዋል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።
በርክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንዳሉት፤ ርክክብቡ የሰላም ስምምነቱ አንዱ አካል ነው።
የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጀነራል ምግበይ ሃይለ በበኩላቸው ርክክቡ በሰላም ስምምነት መሰረት መሰረት መፈጸሙን ተናግረዋል። ሰላም የመጀመሪያና የመጨረሻ ግባችን ነውም ብለዋል።
ርክክቡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተከናውነናል።
ከቡድን መሳሪያዎቹ ርክክብ በኋላ መግለጫ የሰጡት በአፍሪካ ሕብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዴር ጀነራል ቴፎ ሰኮሌ የርክክብ ሂደቱ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ መልኩ እየሄደ መሆኑን አንዱ ማሳያ ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
#ከኢፕድ_ማህደር

ሁለት ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው 2 ዓመት እስራት ተፈረደበት

ሊጠጣ ገብቶ ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው መላኩ ምህረቴ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡

በሌብነት ወንጀል ተከሶ ስምንት ጊዜ የተቀጣው መላኩ ምህረቴ ዘጠነኛውን የስርቆት ወንጀል ሲፈጽም የተያዘው በደሴ ከተማ ባለፈው ሐምሌ 27 ቀን 1962 ዓ.ም ነው፡፡

ተከሳሹ በዚሁ ቀን እመት የሺ ነዋይ ከተባሉት ሴት መጠጥ ቤት ገብቶ ሁለት ጠርሙስ አረቄ ስረቆ መውሰዱን እራሱም ከማመኑም በላይ በማስረጃም ተረጋግጦበታል፡፡

በዚህ አድራጎቱ ተከሶ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ የደሴ ዙሪያ አውራጃ ፈርድ ቤት በዋለው ችሎት ወስኖበታል፡፡

መስከረም 7 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የታተመ