የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት !!
የከተማችንን የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ለመመልከት እና ለመደገፍ ከፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዢን ቡድን ጋር ውይይት ጀምረናል፡፡
ቡድኑ ለተከታታይ 10 ቀናት ወደ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ወርዶ የሱፐርቪዢን ስራ ያካሂዳል።
የሰራናቸው ስራዎች ብዙ፣ የሔድንበት ርቀት ረጅም ቢሆንም በከተማችን ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን መፍታት ከፍተኛ ጥረት እና በርካታ ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ የፌደራል መንግስት ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተገቢ እና አስፈላጊ ነው።
እየፈጠርንና እየፈጠንን አዲስ አበባን እንደስሟ ውብ፤ ለኑሮና ለስራ ምቹ ከተማ ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን!
የከተማችንን የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ለመመልከት እና ለመደገፍ ከፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዢን ቡድን ጋር ውይይት ጀምረናል፡፡
ቡድኑ ለተከታታይ 10 ቀናት ወደ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ወርዶ የሱፐርቪዢን ስራ ያካሂዳል።
የሰራናቸው ስራዎች ብዙ፣ የሔድንበት ርቀት ረጅም ቢሆንም በከተማችን ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን መፍታት ከፍተኛ ጥረት እና በርካታ ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ የፌደራል መንግስት ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተገቢ እና አስፈላጊ ነው።
እየፈጠርንና እየፈጠንን አዲስ አበባን እንደስሟ ውብ፤ ለኑሮና ለስራ ምቹ ከተማ ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን!
በአፋር ክልል ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ አገልግሎት ተመለሰ
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞችና በአካባቢያቸው በተነሳ ከባድ ነፋስ ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ዛሬ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::
አገልግሎቱ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ የተመለሰው የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጎዱትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት በመጠገናቸው መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል።
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞች በተነሳ ከባድ ነፋስ በኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ጉዳት መድረሱን መገለጹ ተጠቅሷል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞችና በአካባቢያቸው በተነሳ ከባድ ነፋስ ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ዛሬ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::
አገልግሎቱ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ የተመለሰው የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጎዱትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት በመጠገናቸው መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል።
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞች በተነሳ ከባድ ነፋስ በኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ጉዳት መድረሱን መገለጹ ተጠቅሷል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግም ተከራይ ማስወጣትም እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የኑሮ ውድነቱ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማችን ነዋሪዎች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ የቤት ኪራይ ጭማሪ እንዳይደረግ በተለያዩ ተከታታይ ጊዜያት ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል::
አሁንም በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት የማይቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የኑሮ ውድነቱ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማችን ነዋሪዎች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ የቤት ኪራይ ጭማሪ እንዳይደረግ በተለያዩ ተከታታይ ጊዜያት ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል::
አሁንም በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት የማይቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አካሄደ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ከአቃቂ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አምስት ሺህ ችግኞች ተከለ።
"ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2015 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ጽ/ቤቱ ከ50ሺህ በላይ ችግኞችን ለክፍለከተማው ያበረከተ ሲሆን በዛሬው እለትም አምስት ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
በመርሀግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደቦ ቱንካ እንደገለፁት፤ ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከተማዋ ያላትን 15 በመቶ የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ የሚረዳ ነው።
ጽ/ቤቱ ከሚያከናውነው የአካባቢ ልማት የማሳደግ ተግባር በተጨማሪ ሀገራዊ በሆነው መርሀግብር በመሳተፍና ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በመርሀግብሩ የአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የአቃቂ ክ/ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በማህሌት ብዙነህ
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ከአቃቂ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አምስት ሺህ ችግኞች ተከለ።
"ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2015 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ጽ/ቤቱ ከ50ሺህ በላይ ችግኞችን ለክፍለከተማው ያበረከተ ሲሆን በዛሬው እለትም አምስት ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
በመርሀግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደቦ ቱንካ እንደገለፁት፤ ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከተማዋ ያላትን 15 በመቶ የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ የሚረዳ ነው።
ጽ/ቤቱ ከሚያከናውነው የአካባቢ ልማት የማሳደግ ተግባር በተጨማሪ ሀገራዊ በሆነው መርሀግብር በመሳተፍና ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በመርሀግብሩ የአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የአቃቂ ክ/ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በማህሌት ብዙነህ
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
በአዲስ አበባ እስካሁን ከአራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል
👉ኅብረተሰቡ በችግኝ ተከላ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
*********************
(ኢ.ፕ.ድ)
በቅርቡ በተጀመረው የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ በአዲስ አበባ እስካሁን ከአራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች መተካላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አስታወቀ::
የከተማው ነዋሪ በአረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እያሳየ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበትም ተመልክቷል::
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=588664780123648&id=100069403920568
👉ኅብረተሰቡ በችግኝ ተከላ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል
*********************
(ኢ.ፕ.ድ)
በቅርቡ በተጀመረው የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ በአዲስ አበባ እስካሁን ከአራት ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች መተካላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አስታወቀ::
የከተማው ነዋሪ በአረጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እያሳየ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚኖርበትም ተመልክቷል::
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=588664780123648&id=100069403920568
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን በመጠቀም የሥራ ዕድልን ማስፋፋት ይገባል
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢንተርፕራይዞች የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ገበያን በመጠቀም የሥራ ዕድል ፈጠራቸውን ማስፋፋት እንደሚኖርባቸው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች፣ አገልግሎት ሰጪዎችና ኢንዱስትሪዎች የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን የገበያ አማራጭን በስፋት በመጠቀም የሥራ ዕድል ፈጠራቸውን ማጠናከር አለባቸው።
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=588654936791299&id=100069403920568
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢንተርፕራይዞች የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ገበያን በመጠቀም የሥራ ዕድል ፈጠራቸውን ማስፋፋት እንደሚኖርባቸው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች፣ አገልግሎት ሰጪዎችና ኢንዱስትሪዎች የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣናን የገበያ አማራጭን በስፋት በመጠቀም የሥራ ዕድል ፈጠራቸውን ማጠናከር አለባቸው።
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=588654936791299&id=100069403920568
የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዓመታዊ ክብረ በዓል እየተካሄደ ነው
**************
(ኢ ፕ ድ)
የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዓመታዊ ክብረ በዓል እና የእውቅና ሥነሥርዓት በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በበዓሉ አከባበር ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል አበባው ታደሰን ጨምሮ የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮችና መኮንኖች ተገኝተዋል፡፡
"ምንጊዜም ለመዘመን እና ለድል አድራጊነት እንዘጋጅ" በሚል መሪ ሐሳብ ነው በዓሉ እየተከበረ የሚገኘው፡፡
የበዓሉ አከባበር ለሕግ የበላይነት መከበር የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የሠራዊት አባላት መዘጋጀቱ ተመላክቷል፡፡
በአከባበሩ ላይ የዕዙን ሁለንተናዊ ገጽታ የሚያንጸባርቁ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚስተናገዱ ይጠበቃል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
**************
(ኢ ፕ ድ)
የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ዓመታዊ ክብረ በዓል እና የእውቅና ሥነሥርዓት በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በበዓሉ አከባበር ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል አበባው ታደሰን ጨምሮ የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮችና መኮንኖች ተገኝተዋል፡፡
"ምንጊዜም ለመዘመን እና ለድል አድራጊነት እንዘጋጅ" በሚል መሪ ሐሳብ ነው በዓሉ እየተከበረ የሚገኘው፡፡
የበዓሉ አከባበር ለሕግ የበላይነት መከበር የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የሠራዊት አባላት መዘጋጀቱ ተመላክቷል፡፡
በአከባበሩ ላይ የዕዙን ሁለንተናዊ ገጽታ የሚያንጸባርቁ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚስተናገዱ ይጠበቃል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም