የኢትዮጵያ እና የግብጽ ግንኙነት ላይ በጋራ የተሰጠ መግለጫ‼️
ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም የአረብ ሪፐብሊክ ግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ተቀብለው አነጋግረዋል።
መሪዎቹ ባደረጉት ምክክር የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች የጋራ ጥቅም ባስጠበቀና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህልና የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
የመሪዎቹ ቁርጠኝነት በቀጠናው ሰላምና ደህንነትን ለማስፈንና መረጋጋትን ለማስጠበቅ ከሚያበረክተው አስተዋፅኦ ባሻገር ሃገራቱ የሚያጋጥሟቸውን የጋራ ፈተናዎች ለመሻገርም ያስችላል።
ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት ምክክር የታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ በተከታዮቹ ሁለት ነጥቦች ላይ ተስማምተዋል፤
👉 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትንና የአሰራር ደንቦችን በተመለከተ በግብፅ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የሚካሄደውን ንግግር በፍጥነት ለማስጀመር እንዲሁም ንግግሩን በአራት ወራት ውስጥ አጠናቆ ከመግባባት ላይ ለመድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ጥረት እንደሚያደርጉ ተስማምተዋል።
👉 ንግግሩ በሚካሄድበት ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ በ2015-2016 ዓ.ም የግድቡ የውሃ ሙሌት ወቅት ግብፅና ሱዳን ከወንዙ በሚያገኙት የውሃ አቅርቦት ላይ የጎላ ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ ኢትዮጵያ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጣለች።
ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ.ም የአረብ ሪፐብሊክ ግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ተቀብለው አነጋግረዋል።
መሪዎቹ ባደረጉት ምክክር የሁለቱን ሃገራት ህዝቦች የጋራ ጥቅም ባስጠበቀና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የባህልና የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
የመሪዎቹ ቁርጠኝነት በቀጠናው ሰላምና ደህንነትን ለማስፈንና መረጋጋትን ለማስጠበቅ ከሚያበረክተው አስተዋፅኦ ባሻገር ሃገራቱ የሚያጋጥሟቸውን የጋራ ፈተናዎች ለመሻገርም ያስችላል።
ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት ምክክር የታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድርን በተመለከተ በተከታዮቹ ሁለት ነጥቦች ላይ ተስማምተዋል፤
👉 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌትንና የአሰራር ደንቦችን በተመለከተ በግብፅ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የሚካሄደውን ንግግር በፍጥነት ለማስጀመር እንዲሁም ንግግሩን በአራት ወራት ውስጥ አጠናቆ ከመግባባት ላይ ለመድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ጥረት እንደሚያደርጉ ተስማምተዋል።
👉 ንግግሩ በሚካሄድበት ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ በ2015-2016 ዓ.ም የግድቡ የውሃ ሙሌት ወቅት ግብፅና ሱዳን ከወንዙ በሚያገኙት የውሃ አቅርቦት ላይ የጎላ ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ ኢትዮጵያ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጣለች።
ኮሚሽኑ በጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተሳታፊ ልየታ ሥራ በዚህ ወር ይጀምራል
👉 ከአራት ክልሎች ሁለት ሺህ 603 ተሳታፊዎች ተለይተዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተሳታፊ ልየታ ሥራ በተያዘው የሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም እንደሚጀምር ገለጸ።
የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ አስተባባሪ ወይዘሮ ቤተልሔም ኪሮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተባባሪ አካላት ....
https://www.facebook.com/100069403920568/posts/pfbid02A6fkzmgHVefB8i6sdHx7yFoZ2U1dygcDJvmXwhMkWuguJXwwTDby5vJpmiGfQHHgl/?mibextid=Nif5oz
👉 ከአራት ክልሎች ሁለት ሺህ 603 ተሳታፊዎች ተለይተዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተሳታፊ ልየታ ሥራ በተያዘው የሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም እንደሚጀምር ገለጸ።
የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን እና ሚዲያ አስተባባሪ ወይዘሮ ቤተልሔም ኪሮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተባባሪ አካላት ....
https://www.facebook.com/100069403920568/posts/pfbid02A6fkzmgHVefB8i6sdHx7yFoZ2U1dygcDJvmXwhMkWuguJXwwTDby5vJpmiGfQHHgl/?mibextid=Nif5oz
አቶ ደመቀ መኮንን ከጋምቢያና ማላዊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከጋምቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማመዱ ታንጋራ (ዶ/ር) እና ከማላዊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናንሲ ቴምቦ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ውይይቱ በኬንያ እየተካሄደ ከሚገኘው 43ኛው የአፍሪካ ኀብረት የስራ አስፈፃሚ መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን የተካሔደ ነው።
አቶ ደመቀ መኮንን ከጋምቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማመዱ ታንጋራ (ዶ/ር) እንዲሁም ከማላዊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናንሲ ቴምቦ ጋር ባደረጉት ውይይት በሀገራቱ መካከል የሁለትዮሽና ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል፡፡
ሚኒስትሮቹ በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ መስማማታቸው ተገልጿል፡፡
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከጋምቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማመዱ ታንጋራ (ዶ/ር) እና ከማላዊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናንሲ ቴምቦ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ውይይቱ በኬንያ እየተካሄደ ከሚገኘው 43ኛው የአፍሪካ ኀብረት የስራ አስፈፃሚ መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን የተካሔደ ነው።
አቶ ደመቀ መኮንን ከጋምቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማመዱ ታንጋራ (ዶ/ር) እንዲሁም ከማላዊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናንሲ ቴምቦ ጋር ባደረጉት ውይይት በሀገራቱ መካከል የሁለትዮሽና ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ዙሪያ መክረዋል፡፡
ሚኒስትሮቹ በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ መስማማታቸው ተገልጿል፡፡
ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም