ቢሮው የሴቶች ቀን 'ማርች 8' ን በተለያዩ ኹነቶች እንደሚያከብር ገለጸ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የዘንድሮው የአለም ሴቶች ቀን(ማርች 8)በተለያዩ ኹነቶች ሊያከብር ዝግጅት ላይ መሆኑን የኦሮሚያ ሴቶች እና ሕጻናት ቢሮ ገለጸ።
የዘንድሮው ማርች 8 በአለም ለ113ኛ፣በኢትዮጵያ ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ" በሴቶች ላይ መሥራት እድገት ያፋጥናል" በሚል መሪ ቃል ይከበራል።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ የክልሉን ሴቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሴቶችን በተለያዩ ማሕበራት የማደራጀት ሥራ ተሰርቷል።
የሴቶች የቁጠባ ባህል ለማዳበር 3.1 ሚሊዮን ሴቶች በሲንቄ ባንክ ከ 5.3 ቢሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ተደርጓል።
በኦሮሞ ባሕል መሰረት 541 ሕጻናት በጉዲፈቻ ሕጋዊ ወላጅ እንዲያገኙ መደረጉን የገለጹት ኃላፊዋ፤ 15ሺህ የሚሆኑት ደግሞ በተለያዩ ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያገኙ መደረጉን አመላክተዋል።
ወይዘሮ መብራት፣ የዘንድሮው የሴቶች ቀን ሲከበር ሶስት ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ቁጠባ ከሴቶች ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመው፤ ለችግር የጋለጡ ሴቶችና ሕጻናት ድጋፍ ማድረግ፣ የሴቶች ሰላም ኮንፈረንስ ማካሄድ፣ሴት ተማሪዎችና ሴት ፋብሪካ ሰራተኞች ጋር ውይይት ማድረግና ማስ ስፖርት የአከባበሩ ኹነቶች መሆናቸውን አብራርተዋል።
በዋቅሹም ፈቃዱ
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የዘንድሮው የአለም ሴቶች ቀን(ማርች 8)በተለያዩ ኹነቶች ሊያከብር ዝግጅት ላይ መሆኑን የኦሮሚያ ሴቶች እና ሕጻናት ቢሮ ገለጸ።
የዘንድሮው ማርች 8 በአለም ለ113ኛ፣በኢትዮጵያ ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ" በሴቶች ላይ መሥራት እድገት ያፋጥናል" በሚል መሪ ቃል ይከበራል።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ መብራት ባጫ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ የክልሉን ሴቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሴቶችን በተለያዩ ማሕበራት የማደራጀት ሥራ ተሰርቷል።
የሴቶች የቁጠባ ባህል ለማዳበር 3.1 ሚሊዮን ሴቶች በሲንቄ ባንክ ከ 5.3 ቢሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ተደርጓል።
በኦሮሞ ባሕል መሰረት 541 ሕጻናት በጉዲፈቻ ሕጋዊ ወላጅ እንዲያገኙ መደረጉን የገለጹት ኃላፊዋ፤ 15ሺህ የሚሆኑት ደግሞ በተለያዩ ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያገኙ መደረጉን አመላክተዋል።
ወይዘሮ መብራት፣ የዘንድሮው የሴቶች ቀን ሲከበር ሶስት ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ቁጠባ ከሴቶች ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመው፤ ለችግር የጋለጡ ሴቶችና ሕጻናት ድጋፍ ማድረግ፣ የሴቶች ሰላም ኮንፈረንስ ማካሄድ፣ሴት ተማሪዎችና ሴት ፋብሪካ ሰራተኞች ጋር ውይይት ማድረግና ማስ ስፖርት የአከባበሩ ኹነቶች መሆናቸውን አብራርተዋል።
በዋቅሹም ፈቃዱ
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
#ዲፕሎማሲያችን_ለብሔራዊ_ጥቅማችን
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት ጋር በመተባበር "ዲፕሎማሲያችን ለብሔራዊ ጥቅማችን" በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም ያዘጋጀው የፎቶግራፍ አውደርዕይ በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መጎብኘቱን ቀጥሏል።
በዛሬው ዕለት ከሆለታ ከተማ ሳደሞ ቀበሌ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተወጣጡ ተማሪዎች፣ ከከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስተባባሪነት ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተወከሉ ሰራተኞች አውደርዕዩን እየጎበኙ ይገኛሉ።
በተስፋ ፈሩ
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት ጋር በመተባበር "ዲፕሎማሲያችን ለብሔራዊ ጥቅማችን" በሚል መሪ ሀሳብ በሳይንስ ሙዚየም ያዘጋጀው የፎቶግራፍ አውደርዕይ በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መጎብኘቱን ቀጥሏል።
በዛሬው ዕለት ከሆለታ ከተማ ሳደሞ ቀበሌ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የተወጣጡ ተማሪዎች፣ ከከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስተባባሪነት ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የተወከሉ ሰራተኞች አውደርዕዩን እየጎበኙ ይገኛሉ።
በተስፋ ፈሩ
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም