አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክና ፖርቱጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
******
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲልቪ ባይፖ- ተሞን ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በተመሳሳይ ከፖርቱጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጃኦ ጎሜዝ ክራቪኝዎ ጋር በሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
አምባሳደር ታዬ ኢትዮጵያ ከፖርቱጋል ጋር በቱሪዝም ፣ትምህርት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ተባብራ መስራት ትፈልጋለች ብለዋል።
የፖርቹጋሉ ሚኒስትር በበኩላቸው አገራቸው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ትግበራን እንደምትደግፍ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የካቲት 06 ቀን 2016 ዓ.ም
******
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሲልቪ ባይፖ- ተሞን ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በተመሳሳይ ከፖርቱጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጃኦ ጎሜዝ ክራቪኝዎ ጋር በሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።
አምባሳደር ታዬ ኢትዮጵያ ከፖርቱጋል ጋር በቱሪዝም ፣ትምህርት፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ተባብራ መስራት ትፈልጋለች ብለዋል።
የፖርቹጋሉ ሚኒስትር በበኩላቸው አገራቸው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ትግበራን እንደምትደግፍ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የካቲት 06 ቀን 2016 ዓ.ም
37ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚታደሙ እንግዶች የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ
***************
(ኢ ፕ ድ)
በ37ኛው አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ለመታደም አዲስ አበባ የገቡ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ዲፕሎማቶችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ጎብኝተዋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች እንግዶችን በመቀበል ጉብኝቱን መርተዋል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ በኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በሳለፍነው እሑድ መመረቁ ይታወቃል።
የዓድዋ ድል መታሰብያ ሙዚየም ኢትዮጵያውያን ከ128 ዓመታት በፊት ለቅኝ ግዛት የመጣውን የጣልያን ወራሪ ኃይል በአንድነት መክተውና አሸንፈው ነፃነታቸውን ያስከበሩበት እና ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የነፃነት ምልክት መሆን ያስቻሉ የድሉ መሪዎች፣ የጦርነቱ ተሳታፊዎችና ሌሎች ታሪካዊ እውነታዎች በአንድ ላይ የተገለጡበት ነው።
በአዲሱ ገረመው
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
***************
(ኢ ፕ ድ)
በ37ኛው አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ለመታደም አዲስ አበባ የገቡ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ዲፕሎማቶችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ጎብኝተዋል።
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች እንግዶችን በመቀበል ጉብኝቱን መርተዋል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ በኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በሳለፍነው እሑድ መመረቁ ይታወቃል።
የዓድዋ ድል መታሰብያ ሙዚየም ኢትዮጵያውያን ከ128 ዓመታት በፊት ለቅኝ ግዛት የመጣውን የጣልያን ወራሪ ኃይል በአንድነት መክተውና አሸንፈው ነፃነታቸውን ያስከበሩበት እና ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የነፃነት ምልክት መሆን ያስቻሉ የድሉ መሪዎች፣ የጦርነቱ ተሳታፊዎችና ሌሎች ታሪካዊ እውነታዎች በአንድ ላይ የተገለጡበት ነው።
በአዲሱ ገረመው
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
ኢትዮጵያውያን ኅብረ ብሔራዊነታቸውን በዓድዋ ድል አስመስክረዋል
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያውያን ኅብረ ብሔራዊነታ ቸውን ጠላትን በአንድነት ቆመው ተዋግተው ባሸነፉበት የዓድዋ ድል ማስመስከራቸውን ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በከሪ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዓድዋ ድል ሕዝቦች ሀገራቸውን ለማዳን በመዘጋጀታቸው፣ በአንድነት በተከፈለ መስዋዕትነት የተመዘገበ የሚያስደንቅና በአርዓያነትም የሚጠቀስ ኅብረብሔራዊ ድል ነው፡፡
የየጁ፣ የወለጋና የሸዋ ፈረሰኞች እንዲሁም የጎንደር፣ የቤኒሻንጉልና የሸዋ ተዋጊዎች አንድም ሳይቀሩ ዓድዋ ላይ ተዋግተው ሲያሸንፉ ያስመሰከሩት ኅብረብሔራዊነታቸውን ነው ያሉት ተባባሪ ፕሮፌሰሩ፤ ዓድዋ ኅብረብሔራዊነት የኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ መሆን እንዳለበት ትምህርት የተሰጠበት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120864
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያውያን ኅብረ ብሔራዊነታ ቸውን ጠላትን በአንድነት ቆመው ተዋግተው ባሸነፉበት የዓድዋ ድል ማስመስከራቸውን ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በከሪ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዓድዋ ድል ሕዝቦች ሀገራቸውን ለማዳን በመዘጋጀታቸው፣ በአንድነት በተከፈለ መስዋዕትነት የተመዘገበ የሚያስደንቅና በአርዓያነትም የሚጠቀስ ኅብረብሔራዊ ድል ነው፡፡
የየጁ፣ የወለጋና የሸዋ ፈረሰኞች እንዲሁም የጎንደር፣ የቤኒሻንጉልና የሸዋ ተዋጊዎች አንድም ሳይቀሩ ዓድዋ ላይ ተዋግተው ሲያሸንፉ ያስመሰከሩት ኅብረብሔራዊነታቸውን ነው ያሉት ተባባሪ ፕሮፌሰሩ፤ ዓድዋ ኅብረብሔራዊነት የኢትዮጵያ የወደፊት አቅጣጫ መሆን እንዳለበት ትምህርት የተሰጠበት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120864
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
👉አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቶን ጭነት አጓጉዟል
በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሰባት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ።
አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቶን ገቢና ወጪ ጭነት እንዲሁም ከ115 ሺህ በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ማኅበሩ ጨምሮ ገልጿል፡፡
በማኅበሩ ከፍተኛ የእቅድና የፕሮግራም አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ፍስሐ መብራህቶም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ሁለት ቢሊዮን 256 ሚሊዮን 459 ሺህ ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡
በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ሁለት ቢሊዮን 158 ሚሊዮን 333 ሺህ ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እንደነበር ያነሱት አቶ ፍስሐ፤ የእቅዱን 104 በመቶ በማሳካት ከሚጠበቀው በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን አስረድተዋል፡፡
አቶ ፍስሐ አክለውም፤ ባለፉት ሰባት ወራት አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ቶን ጭነት ለማጓጓዝ ታቅዶ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120890
************
(ኢ.ፕ.ድ)
👉አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቶን ጭነት አጓጉዟል
በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሰባት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ።
አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቶን ገቢና ወጪ ጭነት እንዲሁም ከ115 ሺህ በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ማኅበሩ ጨምሮ ገልጿል፡፡
በማኅበሩ ከፍተኛ የእቅድና የፕሮግራም አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ፍስሐ መብራህቶም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ሁለት ቢሊዮን 256 ሚሊዮን 459 ሺህ ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡
በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ሁለት ቢሊዮን 158 ሚሊዮን 333 ሺህ ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ እንደነበር ያነሱት አቶ ፍስሐ፤ የእቅዱን 104 በመቶ በማሳካት ከሚጠበቀው በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን አስረድተዋል፡፡
አቶ ፍስሐ አክለውም፤ ባለፉት ሰባት ወራት አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ቶን ጭነት ለማጓጓዝ ታቅዶ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120890
በአማራ ክልል በሩዝ ሰብል ከለማው መሬት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተገኘ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራ ክልል በመኸር ወቅት በሩዝ ሰብል ከለማው መሬት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ አግደው ሞላ እንደገለጹት፤ ምርቱ የተገኘው በ2015/2016 የምርት ዘመን በሩዝ ሰብል ከለማ ከ82 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ነው።
ምርቱ የተሰበሰበው ለሩዝ ሰብል ልማት ተስማሚ በሆኑት ደቡብ፣ ማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ጃዊ ወረዳ በሩዝ ሰብል ከለማ መሬት መሆኑን ተናግረዋል።
የተሰበሰበው ምርት በቀዳሚው ዓመት ከተገኘው ጋር ሲነጻጸር ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ፤ በለማው መሬት ደግሞ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል።
በክልሉ የተሻሻሉ የሩዝ ምርጥ ዘሮችን ተደራሽ በማድረግ ልማቱ እንዲስፋፋ መደረጉ ከውጭ የሚገባን የሩዝ ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት የተያዘውን ግብ ለማሳካት እያገዘ መሆኑንም አቶ አግደው አስታውቀዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ ልማቱ አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን እንዲችል ከማድረግ ባለፈ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ በዘላቂነት እንዲያረጋገጥ የጎላ ሚና እንዳለው ነው ያስረዱት።
በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አርሶ አደር መልኬ መለሰ እንዳሉት፤ ባለፈው የመኸር ወቅት ''ሻጋ'' የተባለውን የሩዝ ምርጥ ዘር ተጠቅመው ካለሙት አንድ ሄክታር መሬት 60 ኩንታል ምርት አግኝተዋል።
የተሻሻሉና ምርታማ የሆኑ የሩዝ ዝርያዎች ተደራሽ መደረጋቸው የእሳቸውንና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርታማነት እያደገ እንዲመጣ ማገዙን ተናግረዋል።
በዚህም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ነው የገለጹት።
ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ተዋቸው ፈጠነ በበኩላቸው፤ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ ዕጥረት ቢያጋጥምም በሩዝ ሰብል ካለሙት አንድ ሄክታር ተኩል መሬት 65 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
‘‘ምርታማነትን ለማሳደግ በምናደርገው ጥረት ዋነኛ ችግራችን የማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦትና ጥራቱን የጠበቀ የሩዝ መፈልፈያ ማሽን አለመኖር ነው’’ ያሉት ደግሞ ሌላኛው የወረዳው አርሶ አደር ዘላለም አስፋው ናቸው።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ አርሶ አደሩ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት ገጥሟቸው የነበረ ቢሆንም በአንድ ሄክታር መሬት ካለሙት የሩዝ ሰብል ከ50 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ተናገረዋል።
በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በሩዝ ሰብል ከለማው 61 ሺህ ሄክታር መሬት 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራ ክልል በመኸር ወቅት በሩዝ ሰብል ከለማው መሬት ከ4 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ አግደው ሞላ እንደገለጹት፤ ምርቱ የተገኘው በ2015/2016 የምርት ዘመን በሩዝ ሰብል ከለማ ከ82 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ነው።
ምርቱ የተሰበሰበው ለሩዝ ሰብል ልማት ተስማሚ በሆኑት ደቡብ፣ ማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ጃዊ ወረዳ በሩዝ ሰብል ከለማ መሬት መሆኑን ተናግረዋል።
የተሰበሰበው ምርት በቀዳሚው ዓመት ከተገኘው ጋር ሲነጻጸር ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ፤ በለማው መሬት ደግሞ ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል።
በክልሉ የተሻሻሉ የሩዝ ምርጥ ዘሮችን ተደራሽ በማድረግ ልማቱ እንዲስፋፋ መደረጉ ከውጭ የሚገባን የሩዝ ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት የተያዘውን ግብ ለማሳካት እያገዘ መሆኑንም አቶ አግደው አስታውቀዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ ልማቱ አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን እንዲችል ከማድረግ ባለፈ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ በዘላቂነት እንዲያረጋገጥ የጎላ ሚና እንዳለው ነው ያስረዱት።
በደቡብ ጎንደር ዞን የፎገራ ወረዳ አርሶ አደር መልኬ መለሰ እንዳሉት፤ ባለፈው የመኸር ወቅት ''ሻጋ'' የተባለውን የሩዝ ምርጥ ዘር ተጠቅመው ካለሙት አንድ ሄክታር መሬት 60 ኩንታል ምርት አግኝተዋል።
የተሻሻሉና ምርታማ የሆኑ የሩዝ ዝርያዎች ተደራሽ መደረጋቸው የእሳቸውንና የአካባቢውን አርሶ አደሮች ምርታማነት እያደገ እንዲመጣ ማገዙን ተናግረዋል።
በዚህም ከቤት ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ነው የገለጹት።
ሌላው የወረዳው ነዋሪ አርሶ አደር ተዋቸው ፈጠነ በበኩላቸው፤ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ ዕጥረት ቢያጋጥምም በሩዝ ሰብል ካለሙት አንድ ሄክታር ተኩል መሬት 65 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
‘‘ምርታማነትን ለማሳደግ በምናደርገው ጥረት ዋነኛ ችግራችን የማዳበሪያ ግብዓት አቅርቦትና ጥራቱን የጠበቀ የሩዝ መፈልፈያ ማሽን አለመኖር ነው’’ ያሉት ደግሞ ሌላኛው የወረዳው አርሶ አደር ዘላለም አስፋው ናቸው።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ አርሶ አደሩ በምርት ዘመኑ የማዳበሪያ አቅርቦት እጥረት ገጥሟቸው የነበረ ቢሆንም በአንድ ሄክታር መሬት ካለሙት የሩዝ ሰብል ከ50 ኩንታል በላይ ምርት ማግኘታቸውን ተናገረዋል።
በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በሩዝ ሰብል ከለማው 61 ሺህ ሄክታር መሬት 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከቢሮው የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
የጉጂ አባገዳዎች ህገ ደንቦችን አሳወቁ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የጉጂ አባገዳዎች ለሚቀጥሉት ስምንት ዓመታት በሥርዓቱ መሠረት መተግበር ያለባቸውን የተለያዩ ድንጋጌዎችን አሳለፉ።
በጉጂ ዞን አዶላ ከተማ በተካሄደው ድንጋጌዎችን የማሳወቅ መርሐ ግብር ከተላለፉ ህገ ደንቦች መካከል፤ የሴቶች መብት የተከበረ ስለመሆኑና ምድር ላይ ያሉ ፍጥረታት ሁሉ ክብር የሚገባቸው መሆኑ ይጠቀሳሉ።
በገዳ ሥርዓት ሰው መግደል፣ ሙስና መስጠትና መቀበል፣ ፍትህ ማዛባት፣ ሠላም ማደፍረስ፣ ነባር የገዳ ሥርዓትና ባህል መበረዝ፣ በማንኛውም ፍጥረት ላይ ወንጀል መፈፀምና ሌሎች ሀገራዊ እሴትን መፈፀም የተወገዘ ሆኑን በድንጋጌው ወቅት አስገንዝበል።
ከዚህም በተጨማሪ ለሠላምና ለአንድነት ሁሉም ሊታጋ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በአዶላ ከተማ አቅራቢያ አርዳ ጂላ በሚባለው ቦታ 75ኛ የጉጂ አባ ገዳዎች የ"ባሊ" ስልጣን ርክክብ መርሐ ግብር እየተከናወነ ሲሆን፤ የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ክፍለዮሐንስ አንበርብር
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የጉጂ አባገዳዎች ለሚቀጥሉት ስምንት ዓመታት በሥርዓቱ መሠረት መተግበር ያለባቸውን የተለያዩ ድንጋጌዎችን አሳለፉ።
በጉጂ ዞን አዶላ ከተማ በተካሄደው ድንጋጌዎችን የማሳወቅ መርሐ ግብር ከተላለፉ ህገ ደንቦች መካከል፤ የሴቶች መብት የተከበረ ስለመሆኑና ምድር ላይ ያሉ ፍጥረታት ሁሉ ክብር የሚገባቸው መሆኑ ይጠቀሳሉ።
በገዳ ሥርዓት ሰው መግደል፣ ሙስና መስጠትና መቀበል፣ ፍትህ ማዛባት፣ ሠላም ማደፍረስ፣ ነባር የገዳ ሥርዓትና ባህል መበረዝ፣ በማንኛውም ፍጥረት ላይ ወንጀል መፈፀምና ሌሎች ሀገራዊ እሴትን መፈፀም የተወገዘ ሆኑን በድንጋጌው ወቅት አስገንዝበል።
ከዚህም በተጨማሪ ለሠላምና ለአንድነት ሁሉም ሊታጋ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በአዶላ ከተማ አቅራቢያ አርዳ ጂላ በሚባለው ቦታ 75ኛ የጉጂ አባ ገዳዎች የ"ባሊ" ስልጣን ርክክብ መርሐ ግብር እየተከናወነ ሲሆን፤ የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል።
ክፍለዮሐንስ አንበርብር
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
የኢትዮ-ቱርክ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ፕሮሞሽን መድረክ እየተካሄደ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ-ቱርክ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ፕሮሞሽን መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነርና የተርክየ ዛካርያ ከተማ 23 የንግድ ባለቤቶች ተገኝተዋል።
በፎረሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀና አርአያ ስላሴ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያና ተርክየ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው።
ከ100 በላይ የተርክየ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተሰማርተው ይገኛሉ። ውጤታማም ናቸው።
ተጨማሪ ኢንቨስተሮች ቢመጡ ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ኮሚሽነሯ፣ ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት አመታት የኢቨስትመንት ፖሊሲዋን አሻሽላለች። የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተካሄደ መሆኑንም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት አለት ያሉት ኮሚሽነር ሀና፣ የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የንግድ ልውውጥ ማደግ፣ የሰለጠነ ወጣት የሰው ሃይል መኖር፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለንግድና ኢንቨስትመንት የሰጠው ትኩረትና ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እንደ መግቢያ በር መሆኗ በኢትዮጵያ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ተጨማሪ እድሎች ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የተርክየ አምባሳደር እና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ በረክ ባራን በበኩላቸው፣ የተርክየ መርህ የጋራ ተጠቃሚነት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና ተርክየ የቆየና ትልቅ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው። የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት በንግድ ልውውጥ ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ጥንታዊ የዲፕሎማሲ መዲና ናት ያሉት አምባሳደሩ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የዲፕሎማሲ መዲና መሆኗን፤ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኤምባሲና አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ እ ንደሆነችም ገልጸዋል።
ይህም ተርክየ ከአፍሪካ ጋር ለመስራት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
***************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ-ቱርክ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ፕሮሞሽን መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነርና የተርክየ ዛካርያ ከተማ 23 የንግድ ባለቤቶች ተገኝተዋል።
በፎረሙ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀና አርአያ ስላሴ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያና ተርክየ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው።
ከ100 በላይ የተርክየ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ተሰማርተው ይገኛሉ። ውጤታማም ናቸው።
ተጨማሪ ኢንቨስተሮች ቢመጡ ተጠቃሚ ይሆናሉ ያሉት ኮሚሽነሯ፣ ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት አመታት የኢቨስትመንት ፖሊሲዋን አሻሽላለች። የመሰረተ ልማት ዝርጋታ እየተካሄደ መሆኑንም አንስተዋል።
ኢትዮጵያ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት አለት ያሉት ኮሚሽነር ሀና፣ የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የንግድ ልውውጥ ማደግ፣ የሰለጠነ ወጣት የሰው ሃይል መኖር፣ የኢትዮጵያ መንግስት ለንግድና ኢንቨስትመንት የሰጠው ትኩረትና ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እንደ መግቢያ በር መሆኗ በኢትዮጵያ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች ተጨማሪ እድሎች ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የተርክየ አምባሳደር እና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ በረክ ባራን በበኩላቸው፣ የተርክየ መርህ የጋራ ተጠቃሚነት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና ተርክየ የቆየና ትልቅ የዲፕሎማሲ ግንኙነት አላቸው። የሁለቱን ሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት በንግድ ልውውጥ ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ጥንታዊ የዲፕሎማሲ መዲና ናት ያሉት አምባሳደሩ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የዲፕሎማሲ መዲና መሆኗን፤ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኤምባሲና አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ እ ንደሆነችም ገልጸዋል።
ይህም ተርክየ ከአፍሪካ ጋር ለመስራት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው አንስተዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓም
በዞኑ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ብር የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጥቷል
***************
(ኢ ፕ ድ)
በዞኑ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ብር የኢንቨስትመንት ፈቃድ ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሥራ የማይገቡ ኢንቨስተሮች ለልማት የተሰጣቸውን መሬት እንደሚነጠቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙዔል ፎላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ በዞኑ ከ3 ቢሊዮን 680 ሚሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል፡፡
እነዚህ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ እንዲያገኙ ከሚመለከተው አካል ጋር በጋራ ተሠርቷል፡፡
ፈቃድ የተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 53 የሚደርሱ መሆናቸውን የተናገሩት አስተዳዳሪው፤ ከኢንቨስትመንቶቹ ውስጥ ወደሥራ የገቡ እና በሂደት ላይ የሚገኙ ስለመኖራቸውም አብራርተዋል፡፡ ወደ ዞኑ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍላጎት ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ኢንቨስትመንቶቹ በገጠር እርሻ፤ በከተማ አገልግሎት ዘርፍ፣ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች እና በከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ ጭምር የተሠማሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የአካባቢው ተወላጅ ዲያስፖራዎች አብዛኛውን የኢንቨስትመንት ክፍል እንደሚሸፍኑም
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120887
***************
(ኢ ፕ ድ)
በዞኑ ከ3 ነጥብ 6 ቢሊዮን በላይ ብር የኢንቨስትመንት ፈቃድ ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የወላይታ ዞን አስተዳደር አስታወቀ፡፡
በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደሥራ የማይገቡ ኢንቨስተሮች ለልማት የተሰጣቸውን መሬት እንደሚነጠቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙዔል ፎላ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ በዞኑ ከ3 ቢሊዮን 680 ሚሊዮን ብር በላይ ያስመዘገቡ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል፡፡
እነዚህ ኢንቨስትመንቶች ፈቃድ እንዲያገኙ ከሚመለከተው አካል ጋር በጋራ ተሠርቷል፡፡
ፈቃድ የተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 53 የሚደርሱ መሆናቸውን የተናገሩት አስተዳዳሪው፤ ከኢንቨስትመንቶቹ ውስጥ ወደሥራ የገቡ እና በሂደት ላይ የሚገኙ ስለመኖራቸውም አብራርተዋል፡፡ ወደ ዞኑ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍላጎት ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ኢንቨስትመንቶቹ በገጠር እርሻ፤ በከተማ አገልግሎት ዘርፍ፣ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች እና በከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ ጭምር የተሠማሩ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የአካባቢው ተወላጅ ዲያስፖራዎች አብዛኛውን የኢንቨስትመንት ክፍል እንደሚሸፍኑም
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120887
በአዲስ አበባ በስድስት ወራት ከሁለት ሺህ 800 በላይ የትዳር ፍቺ ተመዝግቧል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ሁለት ሺህ 813 ፍቺዎች እና 16 ሺህ 933 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ለኢፕድ በላኩት መግለጫ እንደገለጹት፤ ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ ከተመዘገበው ጠቅላላ ኩነት 181 ሺህ 983 ልደት፣ 16 ሺህ 933 ጋብቻ፣ 2 ሺህ 813 ፍቺ እና 8 ሺህ 761 ሞት ተመዝግቧል።
በሳሙኤል ወንድወሰን
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ሁለት ሺህ 813 ፍቺዎች እና 16 ሺህ 933 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ለኢፕድ በላኩት መግለጫ እንደገለጹት፤ ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ ከተመዘገበው ጠቅላላ ኩነት 181 ሺህ 983 ልደት፣ 16 ሺህ 933 ጋብቻ፣ 2 ሺህ 813 ፍቺ እና 8 ሺህ 761 ሞት ተመዝግቧል።
በሳሙኤል ወንድወሰን
የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም