በወላይታ ዞን በዘንድሮ ዓመት 162 ሺህ ኩንታል እሸት ቡና ተሰብስቧል
***************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ከመስከረም ወር 2016 ዓ.ም ጀምሮ 162 ሺህ ኩንታል እሸት ቡና መሰብሰቡን የዞኑ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት ገለጸ። ከዞኑ ስድስት ሺህ ኩንታል የቡና ምርት ለውጭ ገበያ መቅረቡን ተጠቁሟል።
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ክፍሌ ካውሌ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት፤ በዘንድሮ ዓመት የምርት ዘመን ከዞኑ 162 ሺህ ኩንታል እሸት ቡና ተሰብስቧል።
የዞኑን የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተለያዩ የግብርና ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ አምራች አርሶ አደሮች ጥራት ያለው ቡና እንዲያዘጋጁ የሚረዱ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ከቡና ወጪ ንግድ ጋር በተያያዘ ከዞኑ ስድስት ሺህ ኩንታል ምርት ለውጭ ገበያ መላክ ተችሏል ሲሉ አስረድተዋል።
ከዓለም የቡና ገበያ መውረድ ጋር ተያይዞ የዞኑ የቡና ገበያም የመቀነስ አዝማሚያ እንዳለው አመላክተው፤ በቀጣይ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ ወደተለያዩ......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129825
***************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ከመስከረም ወር 2016 ዓ.ም ጀምሮ 162 ሺህ ኩንታል እሸት ቡና መሰብሰቡን የዞኑ ቡናና ቅመማ ቅመም ጽህፈት ቤት ገለጸ። ከዞኑ ስድስት ሺህ ኩንታል የቡና ምርት ለውጭ ገበያ መቅረቡን ተጠቁሟል።
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ክፍሌ ካውሌ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት፤ በዘንድሮ ዓመት የምርት ዘመን ከዞኑ 162 ሺህ ኩንታል እሸት ቡና ተሰብስቧል።
የዞኑን የቡና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተለያዩ የግብርና ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው፤ አምራች አርሶ አደሮች ጥራት ያለው ቡና እንዲያዘጋጁ የሚረዱ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ከቡና ወጪ ንግድ ጋር በተያያዘ ከዞኑ ስድስት ሺህ ኩንታል ምርት ለውጭ ገበያ መላክ ተችሏል ሲሉ አስረድተዋል።
ከዓለም የቡና ገበያ መውረድ ጋር ተያይዞ የዞኑ የቡና ገበያም የመቀነስ አዝማሚያ እንዳለው አመላክተው፤ በቀጣይ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ ወደተለያዩ......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129825
የኦሮሚያ ክልል ከ413 ሚሊዮን በላይ የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት አደረገ
**************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል በመጪው ክረምት ወቅት ከ413 ሚሊዮን በላይ የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ።
ሀገሪቱ በዘርፉ ከምታገኘው ገቢ 70 በመቶ ያህሉ የሚሸፈነው በክልሉ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የቡናና ሻይ ዘርፍ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐመድሳኒ አሚን በክልሉ ያለውን የሻይ ቅጠል ልማት ያለበትን ሁኔታ አስመልክተው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት ማብራሪያ፤ ክልሉ የሻይ ቅጠል ልማትን ጨምሮ በግብርና ውጤቶች ካለው አቅም አንጻር የተለያዩ የግብርና ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
በክልሉ በክረምት ወቅት ከ413 ሚሊዮን በላይ የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል።
በተለይ የሻይ ቅጠልን እንደ አቮካዶና ሌሎች ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የግብርና ምርቶች በስፋት አልምቶ ለሀገር ኢኮኖሚ ለማዋል በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፤የሻይ ቅጠል ልማት ከተጀመረብት 2013 ዓ.ም ጀምሮ አንደ ሀገር ሁለት ሺህ ሄክታር ብቻ እየለማ ከነበረበት አሁን ላይ አርሶ አደሩን ከኢንቨስተሩ ጋር በማስተሳሰር አቅምን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129805
**************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል በመጪው ክረምት ወቅት ከ413 ሚሊዮን በላይ የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ማድረጉን አስታወቀ።
ሀገሪቱ በዘርፉ ከምታገኘው ገቢ 70 በመቶ ያህሉ የሚሸፈነው በክልሉ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የቡናና ሻይ ዘርፍ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሐመድሳኒ አሚን በክልሉ ያለውን የሻይ ቅጠል ልማት ያለበትን ሁኔታ አስመልክተው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በሰጡት ማብራሪያ፤ ክልሉ የሻይ ቅጠል ልማትን ጨምሮ በግብርና ውጤቶች ካለው አቅም አንጻር የተለያዩ የግብርና ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
በክልሉ በክረምት ወቅት ከ413 ሚሊዮን በላይ የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል።
በተለይ የሻይ ቅጠልን እንደ አቮካዶና ሌሎች ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የግብርና ምርቶች በስፋት አልምቶ ለሀገር ኢኮኖሚ ለማዋል በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፤የሻይ ቅጠል ልማት ከተጀመረብት 2013 ዓ.ም ጀምሮ አንደ ሀገር ሁለት ሺህ ሄክታር ብቻ እየለማ ከነበረበት አሁን ላይ አርሶ አደሩን ከኢንቨስተሩ ጋር በማስተሳሰር አቅምን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129805
የአማራ ክልል የ2016 የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር በባህርዳር ከተማ ተጀመረ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የአማራ ክልል የ2016 የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሐግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በባህርዳር ከተማ አስጀምረዋል።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፣ የብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማውን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደገለጹት የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የበኩሉን መወጣት አለበት።
ዛሬ በባህር ዳር ከተማ የተጀመረው የአቅመ ደካማ ቤቶችን የማደስና የመጠገን ተግባር ሌሎች የልማት ተግባራትን አካቶ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ያለው ለሌለው በማካፈል እርስ በርስ መረዳዳት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ያሉት አቶ አረጋ፣ ለክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባር ስኬታማነት የሁሉም አስተዋጾ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም ባለሃብቱ በገንዘቡ፣ ባለሙያው በእውቀቱ፣ ወጣቱ በጉልበቱ እንዲሁም የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ህዝቡን የማስተባበር የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት ከማደስ፣ ከመጠገንና በአዲስ መልክ ከመስራት ባለፈ የተለያዩ የልማት ተግባራት ይከናወናሉ ሲሉም ገልጸዋል።
በዋናነት የአካባቢ ጽዳት፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር፣ የወባ መከላከል እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው የልማት ሥራዎች በትኩረት እንደሚሰሩ አመልክተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የአማራ ክልል የ2016 የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሐግብር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ በባህርዳር ከተማ አስጀምረዋል።
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ፣ የብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ፣ የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማውን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አረጋ ከበደ በማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደገለጹት የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የበኩሉን መወጣት አለበት።
ዛሬ በባህር ዳር ከተማ የተጀመረው የአቅመ ደካማ ቤቶችን የማደስና የመጠገን ተግባር ሌሎች የልማት ተግባራትን አካቶ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ያለው ለሌለው በማካፈል እርስ በርስ መረዳዳት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ያሉት አቶ አረጋ፣ ለክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባር ስኬታማነት የሁሉም አስተዋጾ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም ባለሃብቱ በገንዘቡ፣ ባለሙያው በእውቀቱ፣ ወጣቱ በጉልበቱ እንዲሁም የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች ህዝቡን የማስተባበር የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት ከማደስ፣ ከመጠገንና በአዲስ መልክ ከመስራት ባለፈ የተለያዩ የልማት ተግባራት ይከናወናሉ ሲሉም ገልጸዋል።
በዋናነት የአካባቢ ጽዳት፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር፣ የወባ መከላከል እና ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው የልማት ሥራዎች በትኩረት እንደሚሰሩ አመልክተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
ዛሬ ጠዋት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ አሊ ዩሱፍ ከፕሬዚዳንት እስማኤል ዑማር ጉሌ መልዕክት ይዘው መጥተዋል፤ በጽሕፈት ቤታችን ተቀብያለሁ። እንዲህ ያሉት ግንኙነቶች በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ለንግግርና ትብብር አውታር በመሆን የጋራ መግባባትን ያሳድጋሉ።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
ዛሬ ጠዋት የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ አሊ ዩሱፍ ከፕሬዚዳንት እስማኤል ዑማር ጉሌ መልዕክት ይዘው መጥተዋል፤ በጽሕፈት ቤታችን ተቀብያለሁ። እንዲህ ያሉት ግንኙነቶች በሁለትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ለንግግርና ትብብር አውታር በመሆን የጋራ መግባባትን ያሳድጋሉ።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
ግብርና ሚኒስቴር ለአየር ላይ አስሳና ጸረ ለተባይ ኬሚካል ለመርጨት የሚያስችሉ አውሮፕላንኖችን ገዛ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የግብርና ሚኒስቴር የአንበጣ መንጋና የግሪሳ ወፍ በሰብል ምርት ላይ የሚያደረሱትን ጉዳት ለመከላከል፣ ለአየር ላይ አስሳና ጸረ ተባይ ኬሚካል ለመርጨት የሚያስችሉ አምሰት አውሮፕላንኖችን መግዛቱን አስታወቀ።
በሚኒስቴሩ የእጽዋት ጥበቃ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ በላይነህ ንጉሴ እንደገለጹት፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የገዛቸው ኤርትራክተር 802 በመባል የሚታወቁ ዘመናዊ አውሮፕላኖች የበረሃ አንበጣና የግሪሳ ወፍን መከላከል ያስችላሉ።
ለአውሮፕላንኖቹ ግዢ 10 ሚሊየን ዶላር ወጪ እንደተደረገባቸው ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ጊዜያት በቂ የርጭት አውሮፕላንኖች ባለመኖራቸው የአንበጣ መንጋና የግሪሳ ወፍን መከላከል አዳጋች እንደነበር ጠቅሰው፣ በምርት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል፡፡
የተገዙት አውሮፕላንኖች የምርት ብክነትን በመቀነስ ምርትና ምርታማነትንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለሚደረገው እንቅስቃሴ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው፡፡ አውሮፕላን የማስተዳደሩ ተግባር በብሔራዊ አየር መንገድ ኃ/የተ/የግል ማህበር የሚመራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም አውሮፕላንኖቹ ከላቸው አቅም የተነሳ ፀረ- አረም ና ፀረ-ተባይ የመርጨትና የሰደድ እሳት የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ላይ እንደሚሰማሩም ገልጸዋል፡፡
የብሔራዊ አየር መንገድ ኃ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ ካፒቴን አበራ ለሚ በበኩላቸው፤ በግብርና ሚኒስቴር የተገዙት አውሮፕላንኖች በግብርናው ዘርፍ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ገልጸው ማህበሩ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የአየር ኦፕሬተር ፈቃድ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አግኝቶ በሥራ ላይ ተሰማርቶ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
አውሮፕላኖቹን የማስተዳደር፣ የሚያበሩ ባለሞያዎችንና ቴክኒሻኖችን እንዲሁም አስፈላጊውን የሰው ሀይል የማሟላት ስራን እንደሚሰራ ካፒቴን አበራ ገልጸዋል፡፡
በአማን ረሺድ
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የግብርና ሚኒስቴር የአንበጣ መንጋና የግሪሳ ወፍ በሰብል ምርት ላይ የሚያደረሱትን ጉዳት ለመከላከል፣ ለአየር ላይ አስሳና ጸረ ተባይ ኬሚካል ለመርጨት የሚያስችሉ አምሰት አውሮፕላንኖችን መግዛቱን አስታወቀ።
በሚኒስቴሩ የእጽዋት ጥበቃ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ በላይነህ ንጉሴ እንደገለጹት፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የገዛቸው ኤርትራክተር 802 በመባል የሚታወቁ ዘመናዊ አውሮፕላኖች የበረሃ አንበጣና የግሪሳ ወፍን መከላከል ያስችላሉ።
ለአውሮፕላንኖቹ ግዢ 10 ሚሊየን ዶላር ወጪ እንደተደረገባቸው ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ጊዜያት በቂ የርጭት አውሮፕላንኖች ባለመኖራቸው የአንበጣ መንጋና የግሪሳ ወፍን መከላከል አዳጋች እንደነበር ጠቅሰው፣ በምርት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል፡፡
የተገዙት አውሮፕላንኖች የምርት ብክነትን በመቀነስ ምርትና ምርታማነትንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለሚደረገው እንቅስቃሴ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው፡፡ አውሮፕላን የማስተዳደሩ ተግባር በብሔራዊ አየር መንገድ ኃ/የተ/የግል ማህበር የሚመራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም አውሮፕላንኖቹ ከላቸው አቅም የተነሳ ፀረ- አረም ና ፀረ-ተባይ የመርጨትና የሰደድ እሳት የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ላይ እንደሚሰማሩም ገልጸዋል፡፡
የብሔራዊ አየር መንገድ ኃ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ ካፒቴን አበራ ለሚ በበኩላቸው፤ በግብርና ሚኒስቴር የተገዙት አውሮፕላንኖች በግብርናው ዘርፍ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ገልጸው ማህበሩ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የአየር ኦፕሬተር ፈቃድ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አግኝቶ በሥራ ላይ ተሰማርቶ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
አውሮፕላኖቹን የማስተዳደር፣ የሚያበሩ ባለሞያዎችንና ቴክኒሻኖችን እንዲሁም አስፈላጊውን የሰው ሀይል የማሟላት ስራን እንደሚሰራ ካፒቴን አበራ ገልጸዋል፡፡
በአማን ረሺድ
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በጅቡቲ የዶራሌ ሁለገብ ወደብ የገቢ-ወጪ ሂደቱን ጎበኙ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በጅቡቲ የዶራሌ ሁለገብ ወደብ ተገኝተው አጠቃላይ የገቢ-ወጪ ሂደቱን ጎበኝተዋል።
የአፈር ማዳበሪያን አስመልክቶ ወደ ሃገር ቤት የሚደረገው ማጓጓዝ እንዲጠናከር ሁለት አዳዲስ የማዳበሪያ ከረጢት መስፊያ ማሽኖች ወደ ኦፕሬሽን እንዲገቡ ሚኒስትሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ይህ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡና የሚወጡ አጠቃላይ ምርቶች የሚስተናገዱበት ነው።
በጉብኝቱም ላይ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ጨምሮ የወደብ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና በጅቡቲ የኢትዮጵያ ተቋማት አመራሮች መገኘታቸው ኤምባሲው አስታውቋል።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
********************
(ኢ ፕ ድ)
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜ በጅቡቲ የዶራሌ ሁለገብ ወደብ ተገኝተው አጠቃላይ የገቢ-ወጪ ሂደቱን ጎበኝተዋል።
የአፈር ማዳበሪያን አስመልክቶ ወደ ሃገር ቤት የሚደረገው ማጓጓዝ እንዲጠናከር ሁለት አዳዲስ የማዳበሪያ ከረጢት መስፊያ ማሽኖች ወደ ኦፕሬሽን እንዲገቡ ሚኒስትሩ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
ይህ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡና የሚወጡ አጠቃላይ ምርቶች የሚስተናገዱበት ነው።
በጉብኝቱም ላይ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ጨምሮ የወደብ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና በጅቡቲ የኢትዮጵያ ተቋማት አመራሮች መገኘታቸው ኤምባሲው አስታውቋል።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
ባለፉት አስር ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጭ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል - ሙፈሪያት ካሚል
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በ2016 በጀት ዓመት ያለፉት አስር ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጭ የሥራ ዕድል መፈጠሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ።
ሚኒስትሯ እንደተናገሩት፤ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች ተፈላጊውን ክህሎት እንዲጨብጡ የማብቃት ተግባር ትኩረት ተሰጥቶታል።
በተለይም የሰለጠነ የሰው ኃይል ወደ ውጭ ለማሰማራት አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው፥ ስልጠና ከመስጠት ባለፈ ብቁ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ በበጀት ዓመቱ አስር ወራት 314 ሺህ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ሆነዋል።
የሥራ ስምሪቱ ዜጎች ደህንነታቸው፣ የሚያገኙት ጥቅምና መብታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ በሚያስችል መልኩ መከናወኑንም አብራርተዋል።
በሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው በጥቅሉ ለ3 ሚሊዮን 77 ሺህ ዜጎች የሀገር ውስጥና የውጭ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።
ሚኒስትሯ እንዳሉት የዲጂታል ሥርዓት በመዘርጋት ዜጎች ተመዝግበው ወደ ሥራ ገበያው እንዲገቡ ለማድረግ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ላይም በትኩረት እየተሰራ ነው።
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍም ወጣቶች ያላቸውን የፈጠራ ሀሳብ ወደ ቴክኖሎጂ ምርት መቀየር የሚችሉበት ስልጠና እና ምቹ ምህዳር መፈጠሩንም አክለዋል።
በዚህም የስራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶችን በማወዳደር ምርቶቻቸውን ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት እንዲጠቀሙ በተጀመረው ሂደት 76 ቴክኖሎጂዎች ወደ ምርት መሸጋገራቸውን አብራርተዋል።
ስታርትአፖችና ኢንተርፕራይዞችን በማጎልበት ተጨማሪ የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ በመንግስት ትኩረት መደረጉን አስረድተዋል።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በ2016 በጀት ዓመት ያለፉት አስር ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በሀገር ውስጥና በውጭ የሥራ ዕድል መፈጠሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ተናገሩ።
ሚኒስትሯ እንደተናገሩት፤ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ለሥራ የሚሰማሩ ዜጎች ተፈላጊውን ክህሎት እንዲጨብጡ የማብቃት ተግባር ትኩረት ተሰጥቶታል።
በተለይም የሰለጠነ የሰው ኃይል ወደ ውጭ ለማሰማራት አስፈላጊው ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው፥ ስልጠና ከመስጠት ባለፈ ብቁ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብለዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ በበጀት ዓመቱ አስር ወራት 314 ሺህ ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ሆነዋል።
የሥራ ስምሪቱ ዜጎች ደህንነታቸው፣ የሚያገኙት ጥቅምና መብታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ በሚያስችል መልኩ መከናወኑንም አብራርተዋል።
በሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው በጥቅሉ ለ3 ሚሊዮን 77 ሺህ ዜጎች የሀገር ውስጥና የውጭ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።
ሚኒስትሯ እንዳሉት የዲጂታል ሥርዓት በመዘርጋት ዜጎች ተመዝግበው ወደ ሥራ ገበያው እንዲገቡ ለማድረግ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ላይም በትኩረት እየተሰራ ነው።
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍም ወጣቶች ያላቸውን የፈጠራ ሀሳብ ወደ ቴክኖሎጂ ምርት መቀየር የሚችሉበት ስልጠና እና ምቹ ምህዳር መፈጠሩንም አክለዋል።
በዚህም የስራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶችን በማወዳደር ምርቶቻቸውን ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት እንዲጠቀሙ በተጀመረው ሂደት 76 ቴክኖሎጂዎች ወደ ምርት መሸጋገራቸውን አብራርተዋል።
ስታርትአፖችና ኢንተርፕራይዞችን በማጎልበት ተጨማሪ የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ በመንግስት ትኩረት መደረጉን አስረድተዋል።
ሰኔ 6 ቀን 2016 ዓም