በተጎዱ አካባቢዎች ላሉ ህፃናት ትምህርት ለመስጠት ያለመ አለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ እየተካሄደ ነው
***********************
(ኢ ፕ ድ)
"የአደጋ ጊዜ ትምህርት እና በችግር በተጎዱ አካባቢዎች ላሉ ህፃናት በጨዋታ ላይ የተመሰረተ የመማር አቀራረቦች" በሚል መሪ ሀሳብ አለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ላይ በትምህርት ሚኒስትር የከፍተኛ ትምህርት ዴኤታ አቶ ኮራ ቶሹኔ እንደገለፁት፤ ኮንፍረንሱ በሀገሪቱ ጦርነት ላለባቸው አካባቢዎች ያሉበትን ሁኔታ በማገናዘብ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ነው።
በተጨማሪም ከማስተማር ባለፈ የጨዋታ ትምህርት ስርአት በመፍጠር ከደረሰባቸው የስነልቦና እና አካል ጉዳት እንዲያገግሙ የሚረዳ ነው ብለዋል።
የኮተቤ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሀነመስቀል ጠና በበኩላቸው፤ መድረኩ በጦርነት አካባቢ የሚገኙ ህፃናት ከትምህርት ውጪ የሚሆኑበትን ሁኔታ የማስቀረት ያለመ ነው ብለዋል።
ለዚህም በፀጥታ ችግር ያለበት አካባቢ የሚገኙ መምህናንን ስልጠና የመስጠት ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል።
በዚህ ተግባርም ከሀገር ውስጥና ውጭ የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ዶ/ር ብርሀነመስቀል አስታውቀዋል።
የኮተቤ የትምሀርት ዩኒቨርስቲ ከኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር እና ከፕለይማተርስ ኢትዮጵያ የተዘጋጀው የምርምር ኮንፍረንስ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ነው።
በማህሌት ብዙነህ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
"የአደጋ ጊዜ ትምህርት እና በችግር በተጎዱ አካባቢዎች ላሉ ህፃናት በጨዋታ ላይ የተመሰረተ የመማር አቀራረቦች" በሚል መሪ ሀሳብ አለም አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ላይ በትምህርት ሚኒስትር የከፍተኛ ትምህርት ዴኤታ አቶ ኮራ ቶሹኔ እንደገለፁት፤ ኮንፍረንሱ በሀገሪቱ ጦርነት ላለባቸው አካባቢዎች ያሉበትን ሁኔታ በማገናዘብ ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ነው።
በተጨማሪም ከማስተማር ባለፈ የጨዋታ ትምህርት ስርአት በመፍጠር ከደረሰባቸው የስነልቦና እና አካል ጉዳት እንዲያገግሙ የሚረዳ ነው ብለዋል።
የኮተቤ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሀነመስቀል ጠና በበኩላቸው፤ መድረኩ በጦርነት አካባቢ የሚገኙ ህፃናት ከትምህርት ውጪ የሚሆኑበትን ሁኔታ የማስቀረት ያለመ ነው ብለዋል።
ለዚህም በፀጥታ ችግር ያለበት አካባቢ የሚገኙ መምህናንን ስልጠና የመስጠት ስራ እንደሚሰራም ገልጸዋል።
በዚህ ተግባርም ከሀገር ውስጥና ውጭ የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ዶ/ር ብርሀነመስቀል አስታውቀዋል።
የኮተቤ የትምሀርት ዩኒቨርስቲ ከኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር እና ከፕለይማተርስ ኢትዮጵያ የተዘጋጀው የምርምር ኮንፍረንስ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ነው።
በማህሌት ብዙነህ
የኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባልነት ጥያቄዎች እንዲፋጠኑ ከተለያዩ አገሮች ድጋፍ ተገኝቷል
- አምባሳደር ነብዩ ተድላ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት:-ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባልነት ጥያቄዎች እንዲፋጠኑ የፖለቲካ ድጋፍ ከተለያዩ አገሮች ተገኝቷል።
የኢትዮጵያ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በሩሲያ የብሪክስ ስብሰባዎችና ተጎዳኝ መድረኮች ላይ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጓን ጠቅሰው የብሪክስ አገራት የብሔራዊ ተወካዮችና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ተሳትፎ ማድረጓን ገልጸዋል።
በመድረኩ ኢትዮጵያን ጨምሮ አዳዲስ የብሪክስ አባል አገራት የብሪክስ አዲሱ የልማት ባንክ አባል እንዲሆኑ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ተቀምጧል ያሉት አምባሳደር ነብዩ ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባልነት ጥያቄዎች እንዲፋጠኑ የፖለቲካ ድጋፍ ከተለያዩ አገሮች ተገኝቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኩል እንደአገር በብሪክስ ተሳትፎዋ ያላትን የጎላ ሚና ለማሳደግ የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ መቆየቷን ማብራራታቸውን ገልጸዋል።
በመድረኩ ኢትዮጵያን ጨምሮ አዳዲስ አባል አገራት በብሪክስ ውስጥ በተሳለጠ መልኩ ወደ ማዕቀፉ እንዲገቡ ድጋፍ እንዲደረግ የጋራ መግለጫ መሰጠቱን ጠቅሰው ኢትዮጵያን ጨምሮ አዳዲስ የብሪክስ አባል አገራት የብሪክስ አዲሱ የልማት ባንክ አባል እንዲሆኑ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ተቀምጧል ብለዋል።
ከቻይና ከብራዚል ከደቡብ አፍሪካና ሩሲያ ጋር የተደረጉ የተናጠል ውይይቶች ተደርገዋል ያሉት ቃል አቀባዩ ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባል ለመሆን ያቀረበችውን ጥያቄ እንዲፋጠን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል ብለዋል።
በተጨማሪም በሳምንቱ የተካሄደ አንኳር ዲፕሎማሲያዊ ሁነቶችንም አብራርተው ውጤታማ የሁለትዩሽ ውይይቶች መካሄዳቸውን ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓም
- አምባሳደር ነብዩ ተድላ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት:-ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባልነት ጥያቄዎች እንዲፋጠኑ የፖለቲካ ድጋፍ ከተለያዩ አገሮች ተገኝቷል።
የኢትዮጵያ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በሩሲያ የብሪክስ ስብሰባዎችና ተጎዳኝ መድረኮች ላይ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጓን ጠቅሰው የብሪክስ አገራት የብሔራዊ ተወካዮችና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ተሳትፎ ማድረጓን ገልጸዋል።
በመድረኩ ኢትዮጵያን ጨምሮ አዳዲስ የብሪክስ አባል አገራት የብሪክስ አዲሱ የልማት ባንክ አባል እንዲሆኑ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ተቀምጧል ያሉት አምባሳደር ነብዩ ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባልነት ጥያቄዎች እንዲፋጠኑ የፖለቲካ ድጋፍ ከተለያዩ አገሮች ተገኝቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኩል እንደአገር በብሪክስ ተሳትፎዋ ያላትን የጎላ ሚና ለማሳደግ የተለያዩ እርምጃዎችን ስትወስድ መቆየቷን ማብራራታቸውን ገልጸዋል።
በመድረኩ ኢትዮጵያን ጨምሮ አዳዲስ አባል አገራት በብሪክስ ውስጥ በተሳለጠ መልኩ ወደ ማዕቀፉ እንዲገቡ ድጋፍ እንዲደረግ የጋራ መግለጫ መሰጠቱን ጠቅሰው ኢትዮጵያን ጨምሮ አዳዲስ የብሪክስ አባል አገራት የብሪክስ አዲሱ የልማት ባንክ አባል እንዲሆኑ ድጋፍ እንዲሰጣቸው ተቀምጧል ብለዋል።
ከቻይና ከብራዚል ከደቡብ አፍሪካና ሩሲያ ጋር የተደረጉ የተናጠል ውይይቶች ተደርገዋል ያሉት ቃል አቀባዩ ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲሱ ልማት ባንክ አባል ለመሆን ያቀረበችውን ጥያቄ እንዲፋጠን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል ብለዋል።
በተጨማሪም በሳምንቱ የተካሄደ አንኳር ዲፕሎማሲያዊ ሁነቶችንም አብራርተው ውጤታማ የሁለትዩሽ ውይይቶች መካሄዳቸውን ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓም
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበለትን የ275 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት አፀደቀ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር መካከል ለሁለተኛው የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል የ275 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት አዋጅን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 3ኛ ዓመት 33ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ በከተማ ውስጥ በሚገኝ መሬት፤ በመሬት ማሻሻያና በህንጻ ላይ የንብረት ታክስ እንዲሰበሰብ የሚያደርግ የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡
በከተሞች ውስጥ ከሚገኘው ሀብት ውስጥ እያደገ የመጣውን የመንግስት የወጪ ፍላጎት በተወሰነ ደረጃ ለመሸፈን የሚያስችል ሃብት ማሰባሰብ እንዲቻል ዘመናዊ የንብረት ታክስ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
የምክር ቤት አባል አወቀ አምባዬ (ዶ/ር)፣ የጸደቀውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅን ጨምሮ ሰሞኑን እያጸደቅናቸው የሚገኙ አዋጆች ደሃው ህዝብ ላይ ጫና የሚፈጥሩ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ህብረተሰቡ ችግር ውስጥ ባለበት ሁኔታ ተጨማሪ ክፍያ ማስከፈል አግባብነት የለውም ብለዋል፡፡
ጫናው የሚበረታው ደሃው ህብረተሰብ ላይ በመሆኑ ባግባቡ ሊታይ ይገባል ብለዋል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ላይ ስጋት አለኝ ያሉት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ህብረተሰቡ ቤት ለመስራት ከ15 እስከ 20 ዓመታት ከፍሎ ለመጨረስ የሚፈጅ እዳ ገብቶ ነው፡፡
ንብረት ለማፍራት ዕድሜ ልኩን ዕዳ ከሚከፍል ህዝብ ታክስ መሰብሰብ ይከብዳል ሲሉ አዋጁ ባግባቡ እንዲታይ ተጠይቀዋል፡፡
የአዋጁን አጭር መግለጫ ለምክር ቤት አባላት ያቀረቡት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር አቶ ተስፋዬ በልጅጌ፤ በአብዛኞቹ የአለም አገራት በከተማና በገጠር በሚገኝ መሬት ላይ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ‹‹የመሬት ታክስ›› በሚል ስያሜ ሲሰበሰብ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
በኢትዮጵያም ከ1937 ዓ.ም ጀምሮ ከንብረት ላይ በተለያዩ መጠሪያዎች መጠነኛ ክፍያ በመሰብሰብ ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅ እና የአካባቢና ማህበራዊ ተጽህኖ ግምገማ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል፡፡
በዘላለም ግዛው
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር መካከል ለሁለተኛው የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል የ275 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት አዋጅን በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡
ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 3ኛ ዓመት 33ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ በከተማ ውስጥ በሚገኝ መሬት፤ በመሬት ማሻሻያና በህንጻ ላይ የንብረት ታክስ እንዲሰበሰብ የሚያደርግ የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ተመራ፡፡
በከተሞች ውስጥ ከሚገኘው ሀብት ውስጥ እያደገ የመጣውን የመንግስት የወጪ ፍላጎት በተወሰነ ደረጃ ለመሸፈን የሚያስችል ሃብት ማሰባሰብ እንዲቻል ዘመናዊ የንብረት ታክስ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
የምክር ቤት አባል አወቀ አምባዬ (ዶ/ር)፣ የጸደቀውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅን ጨምሮ ሰሞኑን እያጸደቅናቸው የሚገኙ አዋጆች ደሃው ህዝብ ላይ ጫና የሚፈጥሩ ናቸው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ህብረተሰቡ ችግር ውስጥ ባለበት ሁኔታ ተጨማሪ ክፍያ ማስከፈል አግባብነት የለውም ብለዋል፡፡
ጫናው የሚበረታው ደሃው ህብረተሰብ ላይ በመሆኑ ባግባቡ ሊታይ ይገባል ብለዋል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ላይ ስጋት አለኝ ያሉት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ህብረተሰቡ ቤት ለመስራት ከ15 እስከ 20 ዓመታት ከፍሎ ለመጨረስ የሚፈጅ እዳ ገብቶ ነው፡፡
ንብረት ለማፍራት ዕድሜ ልኩን ዕዳ ከሚከፍል ህዝብ ታክስ መሰብሰብ ይከብዳል ሲሉ አዋጁ ባግባቡ እንዲታይ ተጠይቀዋል፡፡
የአዋጁን አጭር መግለጫ ለምክር ቤት አባላት ያቀረቡት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር አቶ ተስፋዬ በልጅጌ፤ በአብዛኞቹ የአለም አገራት በከተማና በገጠር በሚገኝ መሬት ላይ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ‹‹የመሬት ታክስ›› በሚል ስያሜ ሲሰበሰብ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
በኢትዮጵያም ከ1937 ዓ.ም ጀምሮ ከንብረት ላይ በተለያዩ መጠሪያዎች መጠነኛ ክፍያ በመሰብሰብ ላይ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅ እና የአካባቢና ማህበራዊ ተጽህኖ ግምገማ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል፡፡
በዘላለም ግዛው
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓም
በ224 ሚሊየን ብር ወጪ የተከናወነው የኤረር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ሊመረቅ ነው
****
(ኢ ፕ ድ)
በሀረሪ ክልል በ224 ሚሊየን ብር ወጪ የተከናወነው የኤረር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በመጪው ቅዳሜ ይመረቃል።
ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ከተማ ከሚገባው አጠቃላይ የውሃ መጠን በእጥፍ ይበልጣል ተብሏል። የህዝቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግርን በማቃለል ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑ የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
በሀረሪ ክልል በ224 ሚሊየን ብር ወጪ የተከናወነው የኤረር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በመጪው ቅዳሜ ይመረቃል።
ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ከተማ ከሚገባው አጠቃላይ የውሃ መጠን በእጥፍ ይበልጣል ተብሏል። የህዝቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግርን በማቃለል ረገድ ፋይዳው የላቀ መሆኑ የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓም
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ለ2016/17 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የአረንጓዴ አሻራ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች መዘጋጀታቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በአንድ ጀንበር 150 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ መያዙም ተመላክቷል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ለ2016/17 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ስድስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞችን በማዘጋጀት ከእቅድ በላይ ማከናወን ተችሏል፡፡
አጠቃላይ ከተዘጋጁት ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች መካከል 56 በመቶ የሚሆኑት ብዝሀ ጥቅም ያላቸው የፍራፍሬና የማገዶ ችግኞች ሲሆኑ፤ 44 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የአካባቢ ጥበቃና የደን ሽፋንን የሚጨምሩ ችግኞች መሆናቸውን.......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130384
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ለ2016/17 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የአረንጓዴ አሻራ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች መዘጋጀታቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በአንድ ጀንበር 150 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ መያዙም ተመላክቷል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ለ2016/17 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ስድስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞችን በማዘጋጀት ከእቅድ በላይ ማከናወን ተችሏል፡፡
አጠቃላይ ከተዘጋጁት ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች መካከል 56 በመቶ የሚሆኑት ብዝሀ ጥቅም ያላቸው የፍራፍሬና የማገዶ ችግኞች ሲሆኑ፤ 44 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የአካባቢ ጥበቃና የደን ሽፋንን የሚጨምሩ ችግኞች መሆናቸውን.......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130384
ቴክኒክና ሙያ – የኢኮኖሚ ዕድገት ሞተር
******************
(ኢ ፕ ድ)
ቴክኒክና ሙያ የአዕምሮና እጅ ጥበብ ውጤቶች የሚፈልቁበት ዘርፍ ነው፡፡
ይህን ዘርፍ የሀገርን ኢኮኖሚ በተገቢው ልክ እንዲደግፍ ለማስቻል የተለያዩ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡
ዜጎችን በተለያየ መስክ የሙያ ባለቤት እና የፈጠራ ምንጭ ያደረገ የስልጠና ዘርፍ እንደመሆኑ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የዕድገት ሞተር ለማድረግ የተሠሩ ሥራዎችን መዳሰስ ተገቢ ይሆናል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) የስልጠና ዘርፉ ለአንድ ሀገር ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወት፤ ለኢንዱስትሪው መስክ ደግሞ ቀኝ እጅ ነው ይላሉ፡፡
ዘርፉ የሚያፈራው የሰው ኃይል ከኢንዱስትሪው ጋር ቀጥታ ግንኙነት እያለው እንኳን ይህን ሚናውን ያገናዘበ ትኩረት ሲሰጠው አልነበረም ባይ ናቸው፡፡
የመንግሥት ትኩረት በተለያዩ ጊዜያት እየተሻሻለ መምጣቱን የሚገልጹት ዳይሬክተሩ፤ በተለይ ከጣሊያን ወረራ ወዲህ ተግባረ ዕድ የቴክኒክ ትምህርት ቤት 1942 ላይ እንዲከፈት መደረጉን ይናገራሉ። ከትምህርት ቤቱ መቋቋም በኋላ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130385
******************
(ኢ ፕ ድ)
ቴክኒክና ሙያ የአዕምሮና እጅ ጥበብ ውጤቶች የሚፈልቁበት ዘርፍ ነው፡፡
ይህን ዘርፍ የሀገርን ኢኮኖሚ በተገቢው ልክ እንዲደግፍ ለማስቻል የተለያዩ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡
ዜጎችን በተለያየ መስክ የሙያ ባለቤት እና የፈጠራ ምንጭ ያደረገ የስልጠና ዘርፍ እንደመሆኑ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የዕድገት ሞተር ለማድረግ የተሠሩ ሥራዎችን መዳሰስ ተገቢ ይሆናል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) የስልጠና ዘርፉ ለአንድ ሀገር ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወት፤ ለኢንዱስትሪው መስክ ደግሞ ቀኝ እጅ ነው ይላሉ፡፡
ዘርፉ የሚያፈራው የሰው ኃይል ከኢንዱስትሪው ጋር ቀጥታ ግንኙነት እያለው እንኳን ይህን ሚናውን ያገናዘበ ትኩረት ሲሰጠው አልነበረም ባይ ናቸው፡፡
የመንግሥት ትኩረት በተለያዩ ጊዜያት እየተሻሻለ መምጣቱን የሚገልጹት ዳይሬክተሩ፤ በተለይ ከጣሊያን ወረራ ወዲህ ተግባረ ዕድ የቴክኒክ ትምህርት ቤት 1942 ላይ እንዲከፈት መደረጉን ይናገራሉ። ከትምህርት ቤቱ መቋቋም በኋላ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130385
❤1
ወደ ውጭ በሚላኩ የግብርና ምርቶች ላይ ዘመናዊ የቁጥጥርና ደህንነት ሥርዓት እየተገነባ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)
ወደ ውጭ በሚላኩ የግብርና ምርቶች ላይ ዘመናዊ የቁጥጥርና ደህንነት ሥርዓት እየተገነባ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
በኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራችና ላኪዎች ማህበር እና በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የተዘጋጀው የግብርና ውጤቶች ቁጥጥርና ደህንነት ላይ ያተኮረ ጉባኤ ትናንት ተካሂዷል፡፡
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ባለስልጣኑ ወደ ውጪ የሚላኩና ከውጭ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የግብርና ምርቶችን የደህንነትና ቁጥጥር አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡
እስካሁን የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ በአብዛኛው ወረቀት ላይ የተመሰረተ እንደሆነና አሁን ላይ አገልግሎቱን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር ከአውሮፓ ኅብረትና ከትሬድ ማርክ አፍሪካ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130447
***************
(ኢ ፕ ድ)
ወደ ውጭ በሚላኩ የግብርና ምርቶች ላይ ዘመናዊ የቁጥጥርና ደህንነት ሥርዓት እየተገነባ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
በኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራችና ላኪዎች ማህበር እና በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የተዘጋጀው የግብርና ውጤቶች ቁጥጥርና ደህንነት ላይ ያተኮረ ጉባኤ ትናንት ተካሂዷል፡፡
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ባለስልጣኑ ወደ ውጪ የሚላኩና ከውጭ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የግብርና ምርቶችን የደህንነትና ቁጥጥር አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡
እስካሁን የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ በአብዛኛው ወረቀት ላይ የተመሰረተ እንደሆነና አሁን ላይ አገልግሎቱን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር ከአውሮፓ ኅብረትና ከትሬድ ማርክ አፍሪካ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130447