Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ሀገራዊ መረጃዎች እንዳይጠፉ ተቋማት ለሰነድ አያያዝና አወጋገድ ትኩረት እንዲሰጡ ተጠየቀ
******************
(ኢ ፕ ድ)

ሀገራዊ መረጃዎችን የያዙ ሰነዶች በእርጅና ምክንያት እንዳይጠፉ ተቋማት ለሰነድ አያያዝና አወጋገድ ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጽሐፍት አገልግሎት ጠየቀ፡፡

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጽሐፍት አገልግሎት ዋና ዳሬክተር አቶ ይኩኑአምላክ መዝገቡ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የተለያዩ ተቋማት ለሥራ የሚያመነጯቸው ሰነዶች ከጊዜ በኋላ ሀገራዊ መዛግብት በመሆናቸው ተቋማት ለሰነድ አያያዝና አወጋገድ ልዩ ትኩረት ሊሠጡ ይገባል፡፡

እንደ አቶ ይኩኑአምላክ ገለጻ፤ በርካታ ተቋማት የቦታ ጥበት አጋጥሞናል በሚል ምክንያት መዛግብቶችን በጆንያ እያከማቹና ከሕግ አግባብ ውጪ ጥቅም አይሰጥም በሚል እስከማቃጠል የደረሱ አሉ፡፡

የሰነዶችን አያያዝ በሚመለከት የወጡ ጥብቅ ሕጎች ቢኖሩም ከግንዛቤ ማነስና በሌሎች ምክንያቶች አስፈላጊ ሰነዶች እየጠፉ.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131309
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
የህዝብን ቅሬታ በመስማት የኢሚግሬሽን ስራ ማስተካከያ የሚሹ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት እና ተቋማዊ ለውጦችን በማከናወን በጥቂት ወራት ውስጥ ብዙ ማሻሻያዎች እየተተገበሩ ይገኛሉ። ለምሳሌ ያህል፤
👉 በቀን 900 ፓስፖርት መስጠት የነበረውን አገልግሎት ወደ 1700 ማድረስ ተችሏል፣
👉 ቀደም ብለው የተጠራቀሙ ጥያቄዎችን አስተናግዶ ለመጨረስ በተሰራ ስራ አንድ ሚሊየን ፓስፓርት ታትሞ ገብቶ እስከ 87 በመቶ ተሰራጭቷል፣
👉 የተከማቹ ቅሬታዎች 100% ተፈትተዋል፣
👉 በኢትዮዽያ በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ 10,467 ሰዎችን መመዝገብ ተችሏል፣
👉 ሃሰተኛ ማስረጃ የያዙ 18,000 ሰዎች ቅጣት እንዲከፍሉ ተደርጓል፣
👉 በ88 ሀገሮች የቪዛ አገልግሎት በመክፈት ለ819 278 ተስተናጋጆች e-visa ጨምሮ የቪዛ አገልግሎት ተሰጥቷል
👉 ለ4,276,474 ግለሰቦች በአየርና በየብስ መዳረሻ ጣቢያዎች አገልግሎት ተሰጥቷል
በአሁኑ ወቅትም ተቋሙን የዘመነ እና አገልግሎቱን በጥራት የሚሰጥ ተቋም ለማድረግ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ ነው።
ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓም
በፓሪስ ኦሊምፒክ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች‼️

በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ጨዋታዎች በአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው መለየታቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።

ማራቶን በሴቶችና በወንዶች
✍️ አትሌት ትዕግስት አሰፋ፣አትሌት አማኔ በሪሶ፣አትሌት መገርቱ ዓለሙ፣አትሌት ጎይቶቶም ገ/ስላሴ (ተጠባባቂ)

✍️ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ፣አትሌት ሲሳይ ለማ፣አትሌት ዴሬሳ ገለታ፣ አትሌት ታምራት ቶላ (ተጠባባቂ)

800 ሜትር በሴቶች

✍️ አትሌት ፅጌ ድጉማ፣አትሌት ሐብታም ዓለሙ፣አትሌት ወርቅነሽ መለሰ፣ አትሌት ንግስት ጌታቸው (ተጠባባቂ)

1500 ሜትር በወንዶችና በሴቶች

✍️ አትሌት አብዲሳ ፈይሳ፣አትሌት ሳሙኤል ተፈራ፣አትሌት ኤርሚያስ ግርማ፣አትሌት ታደሰ ለሚ (ተጠባባቂ)

✍️ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣አትሌት ብርቄ ሃየሎም፣አትሌት ድርቤ ወልተጂ፣አትሌት ሂሩት መሸሻ (ተጠባባቂ)

5ሺህ ሜትር ወንዶችና በሴቶች

✍️አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት፣አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ፣አትሌት አዲሱ ይሁኔ፣አትሌት ሰሞን ባረጋ (ተጠባባቂ)

✍️ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣አትሌት መዲና ኢሳ፣አትሌት እጅጋየሁ ታዬ፣አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ (ተጠባባቂ)

10ሺህ ሜትር ወንዶችና በሴቶች

✍️ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ፣አትሌት በሪሁ አረጋዊ፣አትሌት ሰለሞን በረጋ፣አትሌት ቢኒያም መሀሪ (ተጠባባቂ)

✍️ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣አትሌት ፎቴን ተስፋዬ፣አትሌት ፅጌ ገ/ሰላማ፣አትሌት አይናዲስ መብራቱ (ተጠባባቂ)

3ሺህ ሜትር መሠናክል በወንዶች
✍️ አትሌት ለሜቻ ግርማ፣አትሌት ሳሙኤል ፍሬው፣አትሌት ጌትነት ዋለ፣አትሌት አብርሃም ስሜ (ተጠባባቂ)

20 ኪሎ ሜትር ርምጃ በወንድ አትሌት ምስጋና ዋቁማ ናቸው።

ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓም
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
በአርባምንጭ የመስክና ከተማ ጉብኝት እንዲሁም የ#አረንጓዴዓሻራ መርሐ ግብር በምስል‼️
"የምትተክል ሃገር፣ የሚያጸና ትውልድ!"

የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️

ዛሬ ማለዳ የ5ኛ ዙር አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብርን በከተማችን ከሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፣ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች፣ የዓለምአቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አትሌቶች፣ የተለያዩ ስፖርት ቤተሰቦች እንዲሁም ከከተማችን ነዋሪዎች ጋር በመሆን አስጀምረናል።

አረንጓዴና ውብ አካባቢን ለመፍጠር፣ በተፈጥሮ የበለጸገችና ከአየር ብክለት የፀዳች አዲስ አበባን ለትውልዱ ለማዉረስ ቃላችንን በተግባር መንዝረን ከነዋሪዎቻችን ጋር በመሆን ባለፉት የለውጥ ዓመታት ባደረግነው ርብርብ የከተማችንን አረንጓዴ ሽፋን ከነበረበት 2.8 በመቶ ወደ 17 በመቶ ከፍ ማድረግ ችለናል።

በኮሪደር ልማታችንም አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ ለማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን ስንተክል ከርመናል።

ባለፉት የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻዎቻችን የከተማችን ነዋሪዎች ፆታ፣ እድሜ፣ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት እንዲሁም ሃይማኖት ሳይገድባቸው የከተማዋን ተፈጥሯዊ ሚዛን መጠበቅ የሚችሉ ሀገር በቀል ዛፎችን፣ ለገፅታ ድምቀት የሚሆኑ የውበት እፅዋቶችን እንዲሁም የአትክልትና የፍራፍሬ ችግኞችን ተክለዋል።

ዘንድሮም በከተማችን 20 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ታሪክ ለመስራት የተዘጋጀን ሲሆን መላው የከተማችን ነዋሪዎች እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በዚህ ታላቅ ሃገራዊ ጥሪ ላይ በመሳተፍ ለትውልድ የሚሆን አሻራችሁን እንድታኖሩ ጥሪ አቀርባለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓም