Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የአራት ኪሎ-ቀበና-ኬንያ ኤምባሲ ኮሪደር ሥራ ተጠናቋል፤ የአራት ኪሎ-ቀበና-ኬንያ ኤምባሲ የኮሪደር ልማት በፎቶ‼️

ሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓም
ቢያዳፍኑት፤ በይርጋ የማያልፈው ሕገወጥነት
****
(ኢ ፕ ድ)

ከሰሞኑ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለቋሚ ኮሚቴ መርቷል። ረቂቅ አዋጁ ማንኛውም ሰው ያፈራውን ገንዘብ ከሕጋዊ ምንጭ ስለመገኘቱ ማረጋገጫ እንዲኖረው የሚያስገድድ ነው።

ከዚህ በፊት በነበሩ ድንጋጌዎች ምንጩ ያልታወቀ ንብረት የሙስና ወንጀል በመሰኘት ለመንግሥት እና ሕዝባዊ ድርጅቶች ሠራተኞች ብቻ የወንጀል ተጠያቂነትን ያስከትል እንደነበር ረቂቅ አዋጁ ጠቅሷል። ሆኖም አሁን በተሻሻለው ረቂቅ አዋጅ ማንኛውም ግለሰብ እና ሕጋዊ ሰውነት ያለው ተቋም ምንጩ ያልታወቀ ገንዘብ ሲገኝባቸው ተጠያቂ የሚደረጉ መሆኑን ያትታል።

ይህን አዋጅ ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱና ዋንኛው ምንጩ ያልታወቀ ሀብትን የመውረስ ድንጋጌው እስከ 10 ዓመታት ወደኋላ ተመልሶ ተፈጻሚ እንደሚሆን መደንገጉ ነው።

ታዲያ ይህ አዋጅ በዘርፉ ምሁራን ዘንድ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡበት ይገኛል። በአንደኛው ጎራ ያሉ የዘርፉ ምሁራን ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ምንም ያህል ጊዜ ወስዶ ቢደረስበት ከተጠያቂነት መዳን የለበትም ይላሉ። በሌላኛው ጎራ ያሉት የሕግ አዋቂዎች ደግሞ ከረቂቁ ወደኋላ 10 ዓመታትን ተመልሶ ተጠያቂ ያደርጋል የሚለውን ድጋጌን በማንሳት አንድ ሕግ ወደ ኋላ ሄዶ አይተረጎምም፤ ይህም ከሕግ አሠራር....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131599
የበረሃውን ፍሬ ለሕዝብ ያቋደሱት አርሶ አደር
******
(ኢ ፕ ድ)

ከበረሃው ተወዳጅተው ፍሬውን መቅመስ ችለዋል። ከራሳቸውም አልፈው ለሌሎች ተርፈዋል። በርሃው ለዘመናት በጉያው የሸሸገውን ፍሬ ሕዝቡ እንዲቋደስ ምክንያትም ሆነዋል። አርሶ አደር ሲሳይ ኢብሬን ይባላሉ። በቦረና ዞን ያቤሎ ወረዳ አሮ በኬ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪ ናቸው።

በአትክልትና ፍራፍሬ፣ የበቆሎ ሰብል በማልማት እንዲሁም በንብ ማነብና ክብት በማደለብ በጥቅሉ በጥምር ግብርናው ዘርፍ ተሰማርተዋል። መሬታቸውን በተገቢው መንገድ ማረስና ማለስለስ፤ ከብቶቻቸውን መቀለብና መንከባከብ የማይታክቱ ጎልማሳ ናቸው።

ቦረና ሲታሰብ ቀድሞ ከተፍ የሚለው በምርታማነታቸው የሚታወቁት አርብቶ አደሮችና ከብቶቻቸው አለፍ ሲልም በድርቅ መጎዳቱን ቢሆንም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በእርሻው ዘርፍ አበረታች እምርታ እየታየበት ይገኛል።

በተለይ በጥምር ግብርናው ዘርፍ አትክልትና ፍራፍሬ ማልማት ቀርቶ ሳይታሰብ ብዙ ዓመታት ነጉደዋል። የአካባቢው የአየር ሁኔታ በረሃማ ነው። አትክልትና ፍራፍሬ ቀርቶ እርሻን በቅጡ ማረስ የተለመደው.....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131581
በየቤተ እምነቱ ጸያፍ የሆነው የተረጂነት ዕሳቤ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ስንፍናና ተረጂነት በሁሉም ቤተ እምነቶች የተጠላና ጸያፍ እሳቤ ነው።ተረጂነትም ከስንፍና እሳቤ የሚመነጭ ነው።

ሁሉም ቤተ እምነቶች ተከታዮቻቸው ከስንፍና ተላቀው በወዝ በላባቸው፣ በእውቀት ጥበባቸው ጥረው ግረው እንዲኖሩ ያዛሉ።

ምድር ፍሬዋን ለመስጠት ሁሌም ምክንያታዊ ናት።ለብልሆችና ለትጉዎች የምትሰጠውን ያህል፤ ምርኩዟን አጥብቀው ለሚሹ ተለጋሾች፣ ለሰነፎችና ሀኬተኞች ደግሞ ንፉግ ትሆናለች።

ነገር ግን ሚዛናዊነት ስለሚጎድላትም አይደለም። ምርታማነት፣ ምድርን ማበልጸግና ማልማት ከፈጣሪ የተሰጠ ትዕዛዝ እንጂ የራስ መልካም ፈቃድ ሆኖ አያውቅም፡፡

የተረጂነት ስነልቦና የሀገር ሁለንተናዊ እድገት እንዳይኖር መሰናክል ሆኖ ከመቆየቱም በላይ የዜጎችን ክብር በመንካት ሉዓላዊነት አረንቋ ውስጥ የሚጥል እኩይ ተግባር ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

ፈጣሪ ሰማይና ምድር፣ ቀንና ሌሊትን፣ ፀሐይና ጨረቃን፣ ወንዝና አፍላጋትን፣ ለሰው ልጅ የሚበጀውን ሁሉ ሲያዘጋጅ በሰጠው መክሊት ፍሬ እንዲያፈራ ነው።

ሀገር የዜጎች የትጋት፣ የቁርጠኝነት፣ የበሳል አስተሳሰብና የአኗኗር ድምር ውጤት ናት።የዜጎቿ ክብር በተሻሻለና አኗኗራቸው በዘመነ ቁጥር ተሰሚነቷም ሆነ በዓለም መድረክ ተጽእኖ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131597
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ሀብት 1 ነጥብ 7 ትሪሊዮን ደርሷል
**********************
(ኢ ፕ ድ )
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የሚያስተዳድራቸው ተቋማት ሀብት 1 ነጥብ 7 ትሪሊዮን ብር መድረሱን አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ ስምንት ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገባቸውም ተነግሯል።

የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል የተቋሙን ዓመታዊ አፈፃፀም አስመልክቶ እንደገለፁት፤ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሀብት በየጊዜው አጓጊ ለውጥ እያስመዘገበ ነው።

በዚህም የድርጅቶቹ ይዞታና አስተዳደር ሀብት 1 ነጥብ 7 ትሪሊዮን ደርሷል።

በኪሣራ ውስጥ የነበሩ ተቋማት ወደ ትፋማነት እየተቀየሩ እና ሀገራዊ ኃላፊነትን በአግባቡ እየተወጡ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተቋማቱ ካገኙት ትርፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ገበታ ለሀገር ጨምሮ 604 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የኦፕሬሽ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ትዕግስቱ አምሳሉ በበኩላቸው፤ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የሀብት መጠን 1 ጥብ 7 ትሪሊዮን የደረሰ መሆኑን.......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131621
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
በ32 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ የባህር ዛፍ ተክል እንዲመነጠር ውሳኔ ተላለፈ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በሲዳማ ክልል 32 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ የባህርዛፍ ተክል በሦስት ዓመት ውስጥ እንዲመጠነር ውሳኔ መተላለፉን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለጸ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ እንደገለጹት፤ ካለው የመሬት ጥበት አኳያ ለሰብል ልማት የሚውሉ የተለያዩ የመሬት አማራጮችን ተጠቅሞ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሠራ ነው።

በዚህም ለግብርና ልማት መዋል የሚገባው 32 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ የባህርዛፍ ተክል በሦስት ዓመት ውስጥ ተመንጥሮ ለሰብል ልማት እንዲውል የክልሉ ምክር ቤት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

አዋጅ ወጥቶ ወደ ምንጠራ ሥራም ተገብቷል ብለዋል።

በክልሉ ካለው የሕዝብ ጥግግትና የመሬት ሥሪት አኳያ ሰፊ ያልታረሰ ወይም ያልለማ መሬት የለም የሚሉት አቶ መምሩ፤ ያለውን የመሬት አማራጭ አሟጦ ለመጠቀምና አዳዲስ ለግብርና ልማት የሚውል መሬት ማግኘት የሚያስችል......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131607
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ውብ_አዲስ‼️

አራት ኪሎ ተኳኩሎ፣ ቀበናም ጠረኑ ተቀይሮ፣ ፈካ ብሎ፣ ለህዝብ አገልግሎት ውሎ፣ በማየታችን ደስ ብሎናል"

እኛ ጥረናል፣ ፈጣሪ አከናውኖልናል!

- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#ኦሮሚያ

በኦሮሚያ ክልል በ2016 የበጀት ዓመት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ከ79 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 20 ሺህ 664 ፕሮጀክቶች ለምረቃ ተዘጋጅተዋል።

መንግስት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን በተገባደደዉ የበጀት አመት ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።

ሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓም