ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ አገኘ
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተቋሙን አፈጻጸም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ ተቋሙ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጸዋል።
ገቢው ካለፈ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ21 በመቶ ወይም 16 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳይቷል። ገቢው ከእቅድ በላይ 103 ነጥብ 6 በመቶ ሆኗል። በዚህም 21 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘትም ችሏል ብለዋል።
ከገቢው 39 ነጥብ 4 በመቶው ከድምጽ አገልግሎት የተገኘ መሆኑን ገልጸው፤ 27 ነጥብ 7 በመቶው ከዳታና ኢንተርኔት የተገኘ ነው። ገቢው ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።
የተቋሙ ደንበኞች ቁጥር 78 ነጥብ 3 ሚሊዮን መድረሱን ገልጸው፤ ከዚህ ውስጥ 75 ነጥብ 6 ሚሊዮኑ የሞባይል ድምጽ ተጠቃሚ ናቸው። የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥርም ም 40 ነጥብ 4 ሚሊዮን ደርሰዋል።
በዚህም የደንበኞች ቁጥርን ካለፈው ዓመት በ8 ነጥብ 9 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል።
የቴሌብር ደንበኞት ቁጥርም 47 ነጥብ 55 ሚሊዮን መድረሱን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ አንድ ነጥብ 81 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር ተከናውኗል።
አገልገሎቱ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ 2ነጥብ55 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ማንቀሳቀስ መቻሉንም ጠቁመዋል።
በፋንታነሽ ክንዴ
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተቋሙን አፈጻጸም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ ተቋሙ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 93 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገልጸዋል።
ገቢው ካለፈ በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ21 በመቶ ወይም 16 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ጭማሪ አሳይቷል። ገቢው ከእቅድ በላይ 103 ነጥብ 6 በመቶ ሆኗል። በዚህም 21 ነጥብ 79 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘትም ችሏል ብለዋል።
ከገቢው 39 ነጥብ 4 በመቶው ከድምጽ አገልግሎት የተገኘ መሆኑን ገልጸው፤ 27 ነጥብ 7 በመቶው ከዳታና ኢንተርኔት የተገኘ ነው። ገቢው ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።
የተቋሙ ደንበኞች ቁጥር 78 ነጥብ 3 ሚሊዮን መድረሱን ገልጸው፤ ከዚህ ውስጥ 75 ነጥብ 6 ሚሊዮኑ የሞባይል ድምጽ ተጠቃሚ ናቸው። የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥርም ም 40 ነጥብ 4 ሚሊዮን ደርሰዋል።
በዚህም የደንበኞች ቁጥርን ካለፈው ዓመት በ8 ነጥብ 9 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል።
የቴሌብር ደንበኞት ቁጥርም 47 ነጥብ 55 ሚሊዮን መድረሱን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ አንድ ነጥብ 81 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር ተከናውኗል።
አገልገሎቱ ወደ ሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ 2ነጥብ55 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ማንቀሳቀስ መቻሉንም ጠቁመዋል።
በፋንታነሽ ክንዴ
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት‼️
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ከፌደራል መንግስት በተመደበ አንድ ቢሊዮን 168 ሚሊዮን ብር ወጪ ግንባታው እየተከናወነ ይገኛል።
የመንገዱ መገንባት ወደ ደረቅ ወደብ የሚገቡና የሚወጡ ከባድ ተሽከርካሪዎች ተለዋጭ መንገዱን ተጠቅመው ወደ መዳረሻቸው በፍጥነት እንዲደርሱ ያስችላል። ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ ተሸከርካሪዎች ወደ ከተማው መግባት ሳይጠበቅባቸው አቋርጠው ማለፍ እንደሚያስችል የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር ገልጿል።
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ከፌደራል መንግስት በተመደበ አንድ ቢሊዮን 168 ሚሊዮን ብር ወጪ ግንባታው እየተከናወነ ይገኛል።
የመንገዱ መገንባት ወደ ደረቅ ወደብ የሚገቡና የሚወጡ ከባድ ተሽከርካሪዎች ተለዋጭ መንገዱን ተጠቅመው ወደ መዳረሻቸው በፍጥነት እንዲደርሱ ያስችላል። ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ ተሸከርካሪዎች ወደ ከተማው መግባት ሳይጠበቅባቸው አቋርጠው ማለፍ እንደሚያስችል የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር ገልጿል።
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሚዲያዎች የተዘጋጀውን የዕውቅና ሽልማት አበረከቱ
****
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የተዘጋጀውን የዕውቅና ሽልማቱን አበርክተዋል።
በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተዘጋጀው የሚዲያ ዕውቅና መርሐግብር በዓድዋ ሙዚየም ተካሂዷል።
በወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ፣ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬት ዕውቅና ከተሰጣቸው መካከል ይገኙበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያና ድሬ ቲዩብ ደግሞ በሌላ መድረክ ዕውቅና እንደሚሰጣቸው ተገልጿል።
በሽልማቱ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሽልማት ውስጥ ባይካተቱም በተለይ የ “ኪንግ ኦፍ ዓባይ ሚዲያ” ባለቤትና የዓባይ ግድብ ተሟጋች ዑስታዝ ጀማል በሽር ለሚያከናውኑት ስራ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።
ሚዲያዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ባስከበረ መልኩ የኢትዮጵያን ልክ ሊያሳዩ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በጌትነት ተስፉማሪያም
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የተዘጋጀውን የዕውቅና ሽልማቱን አበርክተዋል።
በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተዘጋጀው የሚዲያ ዕውቅና መርሐግብር በዓድዋ ሙዚየም ተካሂዷል።
በወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ፣ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬት ዕውቅና ከተሰጣቸው መካከል ይገኙበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያና ድሬ ቲዩብ ደግሞ በሌላ መድረክ ዕውቅና እንደሚሰጣቸው ተገልጿል።
በሽልማቱ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሽልማት ውስጥ ባይካተቱም በተለይ የ “ኪንግ ኦፍ ዓባይ ሚዲያ” ባለቤትና የዓባይ ግድብ ተሟጋች ዑስታዝ ጀማል በሽር ለሚያከናውኑት ስራ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።
ሚዲያዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ባስከበረ መልኩ የኢትዮጵያን ልክ ሊያሳዩ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በጌትነት ተስፉማሪያም
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
ኢትዮጵያ ለሁለንተናዊ ጉዳዮች ጥንቃቄ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች። በሚዲያ ሥራ ጥረቶቻችን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላም እና ፍቅር ቅድሚያ ሰጥተን መሥራት ይገባናል። ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር ምን ጠቃሚ ሥራ እየሠራን ነው ብለን ራሳችንን ሳናሰልስ መጠየቅ አለብን። በዛሬው ዕለት ሀገራዊ ልማት እና ኅብረትን በማስተዋወቅ ብሎም ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ጥረት ረገድ ከፍ ያለ ሥራ በመሥራት ሽልማት ለተበረከተላቸው የሚዲያ ተቋማት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እፈልጋለሁ።
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያ ለሁለንተናዊ ጉዳዮች ጥንቃቄ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች። በሚዲያ ሥራ ጥረቶቻችን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላም እና ፍቅር ቅድሚያ ሰጥተን መሥራት ይገባናል። ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር ምን ጠቃሚ ሥራ እየሠራን ነው ብለን ራሳችንን ሳናሰልስ መጠየቅ አለብን። በዛሬው ዕለት ሀገራዊ ልማት እና ኅብረትን በማስተዋወቅ ብሎም ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ጥረት ረገድ ከፍ ያለ ሥራ በመሥራት ሽልማት ለተበረከተላቸው የሚዲያ ተቋማት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እፈልጋለሁ።
ሐምሌ 3 ቀን 2016 ዓም