በጎንደርን የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄ መመለሱን ምክንያት በማድረግ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
በጎንደር ከተማ መንግሥት ለልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ያሳየውን ቁርጠኝነት የሚደግፍ እና ያሉ ችግሮች ተሻሽለው አስተማማኝ ሰላም እንዲመጣ የሚጠይቅ ሰልፍ ተካሄደ።
"ለሰላም ዘብ እንቆማለን፤ የተጀመሩ ልማቶችን እናስቀጥላለን" በሚል መሪ ሃሳብ በድጋፍ ሰልፉ ሕዝቡ ዘላቂ ሰላም እና ልማትን ለማምጣት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚያስቀጥል ተመላክቷል።
በሰላማዊ ሰልፉ "የጎንደር እና አካባቢው የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን፣ እሳቸው የሚመሩት ፖርቲ እና መንግሥት ያሳዩንን ቁርጠኝነት እውቅና እንሰጣለን" የሚሉና ሌሎች ሃሳቦች መገለጻቸውን ከአሚኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
በጎንደር ከተማ መንግሥት ለልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ያሳየውን ቁርጠኝነት የሚደግፍ እና ያሉ ችግሮች ተሻሽለው አስተማማኝ ሰላም እንዲመጣ የሚጠይቅ ሰልፍ ተካሄደ።
"ለሰላም ዘብ እንቆማለን፤ የተጀመሩ ልማቶችን እናስቀጥላለን" በሚል መሪ ሃሳብ በድጋፍ ሰልፉ ሕዝቡ ዘላቂ ሰላም እና ልማትን ለማምጣት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚያስቀጥል ተመላክቷል።
በሰላማዊ ሰልፉ "የጎንደር እና አካባቢው የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን፣ እሳቸው የሚመሩት ፖርቲ እና መንግሥት ያሳዩንን ቁርጠኝነት እውቅና እንሰጣለን" የሚሉና ሌሎች ሃሳቦች መገለጻቸውን ከአሚኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በመሬት ናዳ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 75 ቶን ምግብ ነክና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገች
****
(ኢ.ፕ.ድ)
- አደጋው ከደረሰ ጀምሮ 60 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል
የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በመሬት ናዳ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 75 ቶን ምግብ ነክና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጓን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
አደጋው ከደረሰ ጀምሮ 60 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ መደረጉም ተመላክቷል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በመሬት ናዳ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችን ለመደገፍ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫውም የመሬት ናዳ አደጋው መድረሱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የማጽናናት፣ ድጋፍ የማድረግ እና ሌሎች ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውቀዋል።
በዛሬው ዕለት የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በመሬት ናዳ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ የሚሆን 75 ቶን ምግብ ነክና ሌሎች ቁሳቁሶችን መላኩንና ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ መድረሱን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ኮሚሽን ተረክቦ በቀጥታ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ይላካል ብለዋል።
በሌላ በኩል በክልሎች፣ በከተማ አስተዳድሮች፣ በአጋር ድርጅቶች፣ በባለሀብቶች፣ በግለሰቦች እና በሌሎች ባለድርሻ አካላት ያደረጉት ድጋፍ በዓይነትና በገንዘብ ሲተመን 60 ሚሊዮን መሆኑን ተናግረዋል።
በሔለን ወንድምነው
ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
****
(ኢ.ፕ.ድ)
- አደጋው ከደረሰ ጀምሮ 60 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል
የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በመሬት ናዳ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 75 ቶን ምግብ ነክና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጓን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
አደጋው ከደረሰ ጀምሮ 60 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ መደረጉም ተመላክቷል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ቀበሌ በመሬት ናዳ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችን ለመደገፍ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫውም የመሬት ናዳ አደጋው መድረሱ ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የማጽናናት፣ ድጋፍ የማድረግ እና ሌሎች ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውቀዋል።
በዛሬው ዕለት የተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ በመሬት ናዳ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ የሚሆን 75 ቶን ምግብ ነክና ሌሎች ቁሳቁሶችን መላኩንና ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ መድረሱን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ኮሚሽን ተረክቦ በቀጥታ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ይላካል ብለዋል።
በሌላ በኩል በክልሎች፣ በከተማ አስተዳድሮች፣ በአጋር ድርጅቶች፣ በባለሀብቶች፣ በግለሰቦች እና በሌሎች ባለድርሻ አካላት ያደረጉት ድጋፍ በዓይነትና በገንዘብ ሲተመን 60 ሚሊዮን መሆኑን ተናግረዋል።
በሔለን ወንድምነው
ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እስካሁን የ231 ዜጎችን ሕይወት እንደቀጠፈ በተረጋገጠው የጎፋ ዞን የመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ቤተሰቦችና ማኅበረሰብ በአካል ለማፅናናት በስፍራው ተገኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ከቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ ከቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዲሁም ከሌሎች ከፍተኛ የፌደራል መንግሥት አመራሮች ጋር በስፍራው ሲገኙ በክልል ሃላፊዎች እና በማህበረሰቡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ከቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ ከቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዲሁም ከሌሎች ከፍተኛ የፌደራል መንግሥት አመራሮች ጋር በስፍራው ሲገኙ በክልል ሃላፊዎች እና በማህበረሰቡ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
የጎርጎራ ፕሮጀክት ለሀገር የሀብት ምንጭ መሆን በሚችል መልኩ ተሠርቷል
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
ጣናን ተንተርሶ የተሠራው የጎርጎራ ፕሮጀክት ለሀገርና ለአካባቢው ሕዝብ የገቢ ምንጭ መሆን በሚችል መልኩ ተሠርቷል ሲሉ የአማራ ክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ገለጹ።
የአማራ ክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፡- ጣናን ተንተርሶ የተሠራው የጎርጎራ ፕሮጀክት ለአካባቢው ሕዝብና ለሀገር ከፍተኛ የሆነ የሀብት ምንጭ መሆን በሚችል መልኩ ተሠርቷል።
በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ተካተው በሀገሪቱ ከተሠሩ ፕሮጀክቶች የጎርጎራ ፕሮጀክት በጥራቱ፣ በውበቱ፣ በስፋቱ፣ ባሉት ፀጋዎች አንዱ ነው ያሉት ኃላፊው፤ ፕሮጀክቱ ጣናን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=133112
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
ጣናን ተንተርሶ የተሠራው የጎርጎራ ፕሮጀክት ለሀገርና ለአካባቢው ሕዝብ የገቢ ምንጭ መሆን በሚችል መልኩ ተሠርቷል ሲሉ የአማራ ክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ገለጹ።
የአማራ ክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፡- ጣናን ተንተርሶ የተሠራው የጎርጎራ ፕሮጀክት ለአካባቢው ሕዝብና ለሀገር ከፍተኛ የሆነ የሀብት ምንጭ መሆን በሚችል መልኩ ተሠርቷል።
በገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ተካተው በሀገሪቱ ከተሠሩ ፕሮጀክቶች የጎርጎራ ፕሮጀክት በጥራቱ፣ በውበቱ፣ በስፋቱ፣ ባሉት ፀጋዎች አንዱ ነው ያሉት ኃላፊው፤ ፕሮጀክቱ ጣናን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=133112