በቢሾፍቱ የሚገነባውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ18 ወራት ለማጠናቀቅ ታቅዷል
***************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ የሚገነባውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሚቀጥሉት 18 ወራት ለማጠናቀቅ ማቀዱን አስታወቀ።
በአየር መንገዱ ላይ የቀረቡት ክሶች መሠረተ ቢስ መሆናቸውንም አስታውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸምን አስመልክተው ትናንት በሰጡት መግለጫ፣ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላለፉት በርካታ ዓመታት ማስፋፊያ እየተደረገለት ቢቆይም እየጨመረ የመጣውን ዓለም አቀፍ መንገደኛ ማስተናገድ ወደማይችልበት ደረጃ እየደረሰ ነው።
ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም አየር መንገዱ በቢሾፍቱ ተጨማሪ አየር ማረፊያ ለመገንባት እየሠራ ነው።
እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ፣ ተጨማሪ አየር ማረፊያው የሚገነባው ቢሾፍቱ አካባቢ ሲሆን አየር ማረፊያውን ዲዛይን የሚያደርግ ዓለም አቀፍ ተቋራጭ ተመርጧል። ዲዛይኑንና ግንባታውን የሚሠሩት ሥራ ተቋራጮች በሚቀጥሉት 18 ወራት እንዲያጠናቅቁ ስምምነት ላይ ተደርሶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
አየር ማረፊያው የሚገነባበት ቦታ ላይ ያረፉትን አርሶ አደሮች ወደ ሌላ ቦታ ለማዘዋወር የሚያስችል ቦታ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ተለይቶልናል ያሉት አቶ መስፍን፣ የተለየው ቦታ ላይ ኑሯቸውን የሚመሩበት መኖሪያ ቤት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133253
***************************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ የሚገነባውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሚቀጥሉት 18 ወራት ለማጠናቀቅ ማቀዱን አስታወቀ።
በአየር መንገዱ ላይ የቀረቡት ክሶች መሠረተ ቢስ መሆናቸውንም አስታውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸምን አስመልክተው ትናንት በሰጡት መግለጫ፣ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላለፉት በርካታ ዓመታት ማስፋፊያ እየተደረገለት ቢቆይም እየጨመረ የመጣውን ዓለም አቀፍ መንገደኛ ማስተናገድ ወደማይችልበት ደረጃ እየደረሰ ነው።
ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም አየር መንገዱ በቢሾፍቱ ተጨማሪ አየር ማረፊያ ለመገንባት እየሠራ ነው።
እንደ ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ፣ ተጨማሪ አየር ማረፊያው የሚገነባው ቢሾፍቱ አካባቢ ሲሆን አየር ማረፊያውን ዲዛይን የሚያደርግ ዓለም አቀፍ ተቋራጭ ተመርጧል። ዲዛይኑንና ግንባታውን የሚሠሩት ሥራ ተቋራጮች በሚቀጥሉት 18 ወራት እንዲያጠናቅቁ ስምምነት ላይ ተደርሶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
አየር ማረፊያው የሚገነባበት ቦታ ላይ ያረፉትን አርሶ አደሮች ወደ ሌላ ቦታ ለማዘዋወር የሚያስችል ቦታ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ተለይቶልናል ያሉት አቶ መስፍን፣ የተለየው ቦታ ላይ ኑሯቸውን የሚመሩበት መኖሪያ ቤት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133253
የወንጀል መከላከል፣ የምርመራና የመረጃ አሰባሰብ አሰራሮች በቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ እየተከናወኑ ይገኛሉ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የወንጀል መከላከል፣ የምርመራና የመረጃ አሰባሰብ አሰራሮች በቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ምክትል ዋና መምሪያ ኃላፊ ሙሊሳ አብዲሳ፤ በወንጀል መከላከልና በምርመራ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በወንጀል ምርመራና በመከላከል ረገድም በቴክኖሎጂ የተደገፉ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራሮች በስፋት እየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
የፖሊስና ህብረተሰቡ የወንጀል መከላከል ጠንካራ ቁርኝትም ሌላ ተጨማሪ እድል መሆኑን ጠቅሰው በዚሁ ቅንጅታዊ አሰራር ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል።
በአዲስ አበባ የተለያዩ የወንጀል ሙከራዎችን በማክሸፍ አጥፊዎችንም በፍጥነት በቁጥጥር ስር አውሎ ለህግ ማቀረብ የተቻለው በፖሊስና ህብረተሰቡ የተባበረ ስራ መሆኑን ተናግረዋል።
በወንጀል መከላከል፣ በምርመራና በመረጃ አሰባሰብ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮች በስፋት እየተተገበሩ መሆኑም የፖሊስን አሰራር ፈጣንና ዘመናዊ አድርጎታል ብለዋል።
በቀጣይነትም የፖሊስን አሰራር ይበልጥ የማዘመን ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው የሕብረተሰቡም ትብብርና ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
በወንጀል ተግባር ላይ የሚሰማሩ አካላትን በቁጥጥር ስር አውሎ በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ስራ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑንም ሃላፊው አረጋግጠዋል።
በሃሳብ የበላይነት በውይይትና በሰለጠነ መንገድ ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ ሰላም ማምጣት የሁሉም ሃላፊነት ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
********************
(ኢ ፕ ድ)
የወንጀል መከላከል፣ የምርመራና የመረጃ አሰባሰብ አሰራሮች በቴክኖሎጂ በታገዘ መንገድ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ምክትል ዋና መምሪያ ኃላፊ ሙሊሳ አብዲሳ፤ በወንጀል መከላከልና በምርመራ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በወንጀል ምርመራና በመከላከል ረገድም በቴክኖሎጂ የተደገፉ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራሮች በስፋት እየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
የፖሊስና ህብረተሰቡ የወንጀል መከላከል ጠንካራ ቁርኝትም ሌላ ተጨማሪ እድል መሆኑን ጠቅሰው በዚሁ ቅንጅታዊ አሰራር ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል።
በአዲስ አበባ የተለያዩ የወንጀል ሙከራዎችን በማክሸፍ አጥፊዎችንም በፍጥነት በቁጥጥር ስር አውሎ ለህግ ማቀረብ የተቻለው በፖሊስና ህብረተሰቡ የተባበረ ስራ መሆኑን ተናግረዋል።
በወንጀል መከላከል፣ በምርመራና በመረጃ አሰባሰብ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮች በስፋት እየተተገበሩ መሆኑም የፖሊስን አሰራር ፈጣንና ዘመናዊ አድርጎታል ብለዋል።
በቀጣይነትም የፖሊስን አሰራር ይበልጥ የማዘመን ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው የሕብረተሰቡም ትብብርና ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
በወንጀል ተግባር ላይ የሚሰማሩ አካላትን በቁጥጥር ስር አውሎ በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ስራ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑንም ሃላፊው አረጋግጠዋል።
በሃሳብ የበላይነት በውይይትና በሰለጠነ መንገድ ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ ሰላም ማምጣት የሁሉም ሃላፊነት ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት‼️
የፀሀፊን መንፈስ የሚያድሱ ሀይቆች፣ የተፈጥሮን ዚቅ አድምጦ ጥዑም ዜማ ለመቀመር የሚያስችል ድንቅ መልክዓ ምድር፣ የተፈጥሮን ስክነት ማሳያ ስፍራ፣ የውሀዋ ከተማ ቢሾፍቱ።
የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ" በሚል መሪ ቃል የጀመርነውን የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር በቢሾፍቱም ቀጥለናል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ተነሳሽነቶችን በማስተዋወቅ ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ተፈጥሮና ጤናማ ምድርን እናስረክባለን፡፡
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
የፀሀፊን መንፈስ የሚያድሱ ሀይቆች፣ የተፈጥሮን ዚቅ አድምጦ ጥዑም ዜማ ለመቀመር የሚያስችል ድንቅ መልክዓ ምድር፣ የተፈጥሮን ስክነት ማሳያ ስፍራ፣ የውሀዋ ከተማ ቢሾፍቱ።
የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ" በሚል መሪ ቃል የጀመርነውን የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐግብር በቢሾፍቱም ቀጥለናል፡፡ በአረንጓዴ ዐሻራ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ተነሳሽነቶችን በማስተዋወቅ ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ተፈጥሮና ጤናማ ምድርን እናስረክባለን፡፡
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
በአጥር መደርመስ ምክንያት በደረሰ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ ገልፀ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በድሬዳዋ ከተማ ወረዳ 4 በተለምዶ ገንደቦዬ ጋራ ላይ እየተባለ በሚጠራው አካበቢ በአጥር መደርመስ ምክንያት በአራት ግለሰቦች ላይ በደረሰ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ ገልፀ።
የግለሰብ ቤት ተከራይተው የሚኖሩ የድሬዳዋ መምህራን ኮሌጅ የክረምት ተማሪዎች ላይ የጎረቤት አጥር ተደርምሶ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሁለት ተጎጂዎች በድልጮራ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ አየተደረገላቸው መሆኑን በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ የታክቲክ ዳሬክቶሬት ኮማንደር መሀመድ ኢብራሂም ገልፀፀዋል።
ሰሞኑን በተደጋጋሚ እየጣለ የሚገኘው ዝናብ ጋር በተያያዘ በጋራ ላይ ሚገኙ መኖሪያ ቤቶች መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጉዳቱ በደረሰበት አካባቢ የሚኖሩ ቤተሰቦች ለአደጋ እንዳይጋለጡ ጊዜያዊ ማረፊያ ቦታ መሰጠቱን የከተማዋ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በድሬዳዋ ከተማ ወረዳ 4 በተለምዶ ገንደቦዬ ጋራ ላይ እየተባለ በሚጠራው አካበቢ በአጥር መደርመስ ምክንያት በአራት ግለሰቦች ላይ በደረሰ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ ገልፀ።
የግለሰብ ቤት ተከራይተው የሚኖሩ የድሬዳዋ መምህራን ኮሌጅ የክረምት ተማሪዎች ላይ የጎረቤት አጥር ተደርምሶ የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ሁለት ተጎጂዎች በድልጮራ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ አየተደረገላቸው መሆኑን በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ የታክቲክ ዳሬክቶሬት ኮማንደር መሀመድ ኢብራሂም ገልፀፀዋል።
ሰሞኑን በተደጋጋሚ እየጣለ የሚገኘው ዝናብ ጋር በተያያዘ በጋራ ላይ ሚገኙ መኖሪያ ቤቶች መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጉዳቱ በደረሰበት አካባቢ የሚኖሩ ቤተሰቦች ለአደጋ እንዳይጋለጡ ጊዜያዊ ማረፊያ ቦታ መሰጠቱን የከተማዋ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያና ኡጋንዳ በቀጣናዊ የደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች በጋራ እያከናወኗቸው ባሉ የትብብር ሥራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታወቁ
*******
(ኢ ፕ ድ)
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እና የኡጋንዳ የውጭ ደኅንነት ተቋማት በቀጣናዊ የደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የትብብር ሥራዎችን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ገምግመዋል፡፡
የኢትዮጵያና ኡጋንዳ የመረጃና ደኅንነት ተቋማት ቀደም ሲል በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የደኅንነትና የጸጥታ ስጋት የሆኑትን ሽብርተኝነት፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን፣ ሕገወጥ ታጣቂዎችንና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የደረሱትን የሁለትዮሽ ስምምነት በመተግበር የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ መጠናከር ባሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በኩል የውጭ መረጃ ዘርፍ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ታዜር ገብረ እግዚአብሔር እንዲሁም በኡጋንዳ በኩል ደግሞ የውጭ ደኅንነት ተቋም ዳይሬክተር ጀነራል ጆሴፍ ኦኬሎ የጋራ ውይይቱን መርተዋል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ታዜር ገብረ እግዚአብሔር ኡጋንዳ ቀጣናዊና አካባቢያዊ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር በመሥራት ታሪካዊ ወዳጅ መሆኗን ገልፀው፤ የሀገሪቱ የውጭ አቻ የመረጃ ተቋም ከመረጃ ልውውጥና ከደኅንነት አኳያ ከአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ጋር የጀመረውን አጋርነት አጠናክሮ ለመቀጠል እያሳያ ያለው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡
የኡጋንዳ የውጭ ደኅንነት ተቋም ዳይሬክተር ጀነራል ጆሴፍ ኦኬሎ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በጎረቤት ሀገራት እና በቀጣናው ዘለቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እየሠራች መሆኑ፤ የሁለቱ ሀገራት የመረጃ ተቋማት ሕገወጦችን ተከታትለውና ለይተው ተጠያቂ በማድረግ ለዘላቂ ሰላም ምቹ መደላድል ለመፍጠር የጀመሩትን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መረጃ ፤ ሁለቱ አቻ የመረጃ ተቋማት የዛሬ ሁለት ዓመት በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን አስታውሷል፡፡
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እና የኡጋንዳ የውጭ ደኅንነት ተቋማት በቀጣናዊ የደኅንነትና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የትብብር ሥራዎችን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ገምግመዋል፡፡
የኢትዮጵያና ኡጋንዳ የመረጃና ደኅንነት ተቋማት ቀደም ሲል በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የደኅንነትና የጸጥታ ስጋት የሆኑትን ሽብርተኝነት፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን፣ ሕገወጥ ታጣቂዎችንና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የደረሱትን የሁለትዮሽ ስምምነት በመተግበር የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ መጠናከር ባሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በኩል የውጭ መረጃ ዘርፍ ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ታዜር ገብረ እግዚአብሔር እንዲሁም በኡጋንዳ በኩል ደግሞ የውጭ ደኅንነት ተቋም ዳይሬክተር ጀነራል ጆሴፍ ኦኬሎ የጋራ ውይይቱን መርተዋል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ታዜር ገብረ እግዚአብሔር ኡጋንዳ ቀጣናዊና አካባቢያዊ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር በመሥራት ታሪካዊ ወዳጅ መሆኗን ገልፀው፤ የሀገሪቱ የውጭ አቻ የመረጃ ተቋም ከመረጃ ልውውጥና ከደኅንነት አኳያ ከአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ጋር የጀመረውን አጋርነት አጠናክሮ ለመቀጠል እያሳያ ያለው ቁርጠኝነት የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡
የኡጋንዳ የውጭ ደኅንነት ተቋም ዳይሬክተር ጀነራል ጆሴፍ ኦኬሎ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በጎረቤት ሀገራት እና በቀጣናው ዘለቂ ሰላም እንዲረጋገጥ እየሠራች መሆኑ፤ የሁለቱ ሀገራት የመረጃ ተቋማት ሕገወጦችን ተከታትለውና ለይተው ተጠያቂ በማድረግ ለዘላቂ ሰላም ምቹ መደላድል ለመፍጠር የጀመሩትን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መረጃ ፤ ሁለቱ አቻ የመረጃ ተቋማት የዛሬ ሁለት ዓመት በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን አስታውሷል፡፡
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለመደገፍ የሚውል ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ አጸደቀ
***
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓለም ባንክ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባው ኢትዮጵያ የጀመረችውን ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ለመደገፍ የሚረዳ ውሳኔን አጽድቋል።
ባንኩ ዛሬ ማምሻውን ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረትም ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር የ1 ቢሊዮን ዶላር ዕርዳታና 500 ሚሊዮን ዶላር የብድር ድጋፍ ለኢትዮጵያ ለመስጠት ወስኗል።
ይህ ውሳኔ የኢትዮጵያ መንግስት ድህነት ቅነሳን ለማፋጠን እና ሁሉን አሳታፊና ዘላቂ የሆነ እድገትን ለማረጋገጥ በጀመረው እርምጃ ወቅት የተሰጠ ወሳኝ ድጋፍ መሆኑን ባንኩ አስታውቋል።
የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ትልቁ የልማት አጋር መሆኑን የጠቀሰው የባንኩ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በየአመቱ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ የምታገኝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉ በእርዳታ መልክ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጿል።
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓ.ም
***
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓለም ባንክ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ዛሬ ባካሄደው ስብሰባው ኢትዮጵያ የጀመረችውን ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ለመደገፍ የሚረዳ ውሳኔን አጽድቋል።
ባንኩ ዛሬ ማምሻውን ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረትም ከዓለም አቀፉ የልማት ማህበር የ1 ቢሊዮን ዶላር ዕርዳታና 500 ሚሊዮን ዶላር የብድር ድጋፍ ለኢትዮጵያ ለመስጠት ወስኗል።
ይህ ውሳኔ የኢትዮጵያ መንግስት ድህነት ቅነሳን ለማፋጠን እና ሁሉን አሳታፊና ዘላቂ የሆነ እድገትን ለማረጋገጥ በጀመረው እርምጃ ወቅት የተሰጠ ወሳኝ ድጋፍ መሆኑን ባንኩ አስታውቋል።
የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ትልቁ የልማት አጋር መሆኑን የጠቀሰው የባንኩ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በየአመቱ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ የምታገኝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉ በእርዳታ መልክ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጿል።
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓ.ም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‼️
በምስሎቹ የምንመለከተው በመልማት ላይ ያለ የሻይ ተክል ማሳ ነው። በቡና ያሳካነውን አመርቂ ድል በሻይ ምርትም እንደግመዋለን።
በምስሎቹ የምንመለከተው በመልማት ላይ ያለ የሻይ ተክል ማሳ ነው። በቡና ያሳካነውን አመርቂ ድል በሻይ ምርትም እንደግመዋለን።